Get Mystery Box with random crypto!

The words of eternal life

የቴሌግራም ቻናል አርማ zilivingword — The words of eternal life T
የቴሌግራም ቻናል አርማ zilivingword — The words of eternal life
የሰርጥ አድራሻ: @zilivingword
ምድቦች: ያልተመደበ
ቋንቋ: አማርኛ
ተመዝጋቢዎች: 1.85K
የሰርጥ መግለጫ

በዚህ ቻናል
#አጫጭር አስተማሪ videoዎች
#መንፈሳዊ ግጥሞች
#መንፈሳዊ ትምህርቶች
#መንፈሳዊ መጽሐፍት
#መዝሙሮች ወዘተ.... ያገኛሉ
ይቀላቀሉን ይጠቀማሉ!!!
📌 አጋር ቻናላችንን ይቀላቀላሉ
🔰 አስተያየት ካሎት
🔰 ለማስታወቂያ ስራ @Channels_promot1

Ratings & Reviews

4.00

3 reviews

Reviews can be left only by registered users. All reviews are moderated by admins.

5 stars

1

4 stars

1

3 stars

1

2 stars

0

1 stars

0


የቅርብ ጊዜ መልዕክቶች

2022-08-24 22:34:26 ..........I saw Jesus and The False Messiah/በጉንና አየሁት !!

ከጥቂት ቀናት በፊት ነበር እግዚአብሔር አይኖቼን ከፍቶአቸው ከዘመናት በፊት የነበረውን ታላቁን የMarthin Luther King ዘመን Reformation በBlack and White ያሳየኝ ነበር። ስለነበረው እንቅስቃሴ ፤ እናም ስለነበረው ተቃውሞ እንድሁም ስለነበረው ስለ ክርስቶስ ጥዑም ስብከቶች ፤ እንድሁም በዚህ በክርስቶስ ፍቅር ስብከት ሰለባ የሆኑ ከልባቸው ኢየሱስን የወደዱትን ህዝቦቸሰ አየኋቸው። ምንኛ እድግ ግሩምና ድንቅ ምያስቀና ዜማ ያለው ህይወት ነው የሚኖሩት !? ሁሉምያስቀናሉ !!

ነገር ግን ከምነው ቅጽበት እንደሆነ ባላውቅም እራሴን ከበጉ ፊትና ከኢየሱስ አጠገብ እራሴን በሰማይ አየሁት። ኢየሱስ ከጎኔ ይቆማል ፤ ከፊታችንም አንድ በግ በዙፋን ልክ ነበር የቆመው። ዙፋን ሳለው ግን ቆሟል ፤ ኢየሱስም በሀሳብ ልውውጥ እንድመለከተው ያዘኝ ነበር። አየሁት ከበላዩ በጉ ልጫንለት ያለ ልጠልቅለት ያለ አክሊል አለው። አክልሉን ይጠብቀዋል። ወዲያው እያየሁት አክሊል ጠለቀለት ግና አክሊሉ ሲጠልቅለት በጉ መልኩን ይቀይራል። ከአክልሉ መጫን የተነሳ ትክክለኛው መልኩ ይገለጥና የHindiዋ ጣዖት Krishnaን መስሎ ይገለጣል። 6 እጆችም ተገለጡበት። ይህም ሁሉ የተገለጠው በአክሊሉ መጥለቅ መንሥኤ ነው።

አጠገቤ የቆመውም ኢየሱስ አንገቱን ይነቀንቅና እንደቀድሞው በሀሳብ ልውውጥ ንግግር "ይህ የእኔ መልክ ምሳሌ አይደለም" ይላል አንገቱን በመነቅነቅ በሀዘን።

ከዚያም ሌላ በግ አየን። በጉ ትንሽዬ ጠቦት እናም በደስታ የሚፍለቀለቅ ፤ የሚጠባበቀው ተስፋ ያለው አይነት ደስ የሚል ጠቦት ነው። ዙፋን አለው ግን ይቆማል። እርሱም እንደቀድሞው አክሊል ከበላዩ ሊጠልቅለት የተዘጋጀ ነው። አክሊሉ በገድሉ የተወለደ ከውስጡ ከከበሩ ድንጋዮች ብቻ የሚወጣ አይነት የብርሃን ነጸብራቅ ያለው ፤ እጅግ ያማረ ነበር። ይህ ጠቦት በግም ከበላዩ ይህን አክሊል እንደሚገባው እያሰበ ፤ ስለተገባውም በፍጹም እርጋታ ይጠብቀዋል።

በመጨረሻም ለበጉ ይህ አክሊል እያየሁት ተጫነለት። በጉ እጅግ ተደሰተ ፤ ተፍለቀለቀ ፤ ደስታው ከተስፋ ወደ ፍጹምነት ገባ። ኢየሱስም ከጎኔ ቆሞ "ትክክለኛው የእኔ መልክ ይህ ነው። " አለኝ። ፈገግም አለ !!

እኔም በውስጤ ይህ ቃል ትዝ አለኝ !!
“ሰባተኛው መልአክ ነፋ፤ በሰማይም፦ የዓለም መንግሥት ለጌታችንና ለእርሱ ለክርስቶስ ሆነች፥ ለዘላለምም እስከ ዘላለም ይነግሣል የሚሉ ታላላቅ ድምፆች ሆኑ።”
— ራእይ 11፥15

ሀሌሉያ !! ከእውነተኛው መሢህና መሥዋዕታችን ጋር እንነግሳለን።

#Be_aware of The False Messiah !!
#ትልቁ የመጨረሻው ዘመን ችግር Satanism ፤ Lesbian, Gay አይምሰላችሁ ሐሰተኛው ክርስቶስ እንጅ !! በቻለው አቅም እራሱን በመሢህአችን ይመስላል። ነገር ግን ሰዓቱ ሲያልቅ ክፋቱም ይገለጣል። “ታላቅንም ነገርና ስድብን የሚናገርበት አፍ ተሰጠው፥ በአርባ ሁለት ወርም እንዲሠራ ሥልጣን ተሰጠው።”
— ራእይ 13፥5
42ወር/12ወር(1yr)=3.5 አመት

ኢየሱስም 3.6/3.5 አመት ነበር በምድር አገልግሎት የተገለጠው እርሱም ለ3.5አመት ይገለጣል። በቻለው በመሢሀችን ራሱን ይመስላል። ነገር ግን እርሱ ድባቅ ይመታዋል።
አብረነው እንነግሣለን ከመሢሀችን ጋር።
በእግዚአብሔር ጥበብ ልቃችሁ እንድትገኙ እጸልይላቿለሁኝ።
Seer Enbakom
@Christ_Sermons
235 views., edited  19:34
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-08-22 19:43:10
"፤ እርስ በርሳችሁም ቸሮችና ርኅሩኆች ሁኑ፥ እግዚአብሔርም ደግሞ በክርስቶስ ይቅር እንዳላችሁ ይቅር ተባባሉ።"

(ወደ ኤፌሶን ሰዎች 4: 32)



@zilivingword
@zilivingword
@zilivingword
255 views., 16:43
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-08-18 22:20:07 የእግዚአብሔር  ቃል ጉልበት
                  ▷▻▹◈◈◈◃◅◁

አልችልም ስትል  
◉ በሰው ዘንድ የማይቻል በእኔ ዘንድ ይቻላል ይልሃል። (ሉቃስ 18፥27)

ደክሞኛል ስትል፦
◉ አሳርፍሃለው ይልሃል። (ማቴዎስ 11፥28-30)

ማንም አይወደኝም ስትል፦
◉ እወድሃለሁ ይልሃል። (ዮሐንስ 3፥16)

አቅቶኛል መቀጠል አልችልም ስትል፦  
◉ጸጋዬ ይበቃሃል ይልሃል። ( 2ኛ ቆሮንቶስ 12፥9)

መንገድ መለየት ከብዶኛል ስትል ፦                                     ◉በምትሄድበት መንገድ እመራሃለሁ ይልሃል። (መዝሙር 32፥8)

ምንም ማድረግ አልችልም ስትል ፦      
◉ኃይልን በምሰጥህ በእኔ ሁሉን ትችላለህ ይልሃል። (ፊሊጵስዩስ 4፥13)

ብቃት የለኝም ስትል  
◉ብቃት አለህ ይልሃል። (2ኛ ቆሮንቶስ 9፥8-9)

ይሄ ለእኔ አይገባኝም ነበር፣ ለምን እኔ ላይ ሆነ ስትል
◉ነገር ሁሉ ለበጎ ነው ይልሃል። (ሮሜ 8፥28)

ራሴን ይቅር ማለት አልችልም ስትል፦
◉እኔ ይቅር እልሃለሁ ይልሃል። (1ኛ ዮሐንስ 1፥9)

      ꜱʜᴀʀᴇ ꜱʜᴀʀᴇ ꜱʜᴀʀᴇ
              𝐉𝐎𝐈𝐍 𝐔𝐒
          @zilivingword
          @zilivingword
571 views., 19:20
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-08-09 15:18:50 ተሻገሩ ፡ ብሎ ፡ አዞ ፡ በውኃ ፡ ሚያስበላ
ኧረ ፡ እስቲ ፡ ንገሩኝ ፡ ኢየሱስ ፡ ክርስቶስ ፡ ይሆን ፡ ወይስ ፡ ሌላ
መፈጸም ፡ አቅቶት ፡ ከአፉ ፡ የወጣውን ፡ ቃል
ይቅርታ ፡ ጠይቆ ፡ ወይ ፡ ረዳት ፡ ፈልጐ ፡ እርሱ ፡ መች ፡ ያውቃል
ይሄ ፡ ግን ፡ የማውቀው ፡ ጀምሮ ፡ ፈጻሚ
ጠላት ፡ የመጣ ፡ እንደው ፡ እራሱን ፡ አስቀዳሚ
እነርሱን ፡ ተዉአቸው ፡ እኔን ፡ ያዙኝ ፡ የሚል
ከአውሬም ፡ መንጋጋ ፡ በጐቹን ፡ የሚያስጥል

አዝ፦ አሁንስ ፡ ተስፋዬ ፡ ማነው
ድጋፍ ፡ ምሶሶዬ ፡ ማነው
አለኝታ ፡ ጋሻዬ ፡ ማነው
መከታ ፡ አንባዬ ፡ ማነው
ማነው (፫x) ፡ እግዚአብሔር ፡ ነው

ለአብርሃም ፡ ተናግሮ ፡ ነግሮ ፡ ለይሳቅ ፡ አጸና
ለይሳቅ ፡ ተናግሮ ፡ ለያቆብ ፡ ፈጸመ ፡ እርሱ ፡ አይዋሽምና
ዮሴፍ ፡ በግብጽ ፡ ምድር ፡ ቢወርድ ፡ ቢገባም ፡ ተሽጦ
የፈርዖን ፡ መንግሥት ፡ ገዢ ፡ አደረገው ፡ ስርአት ፡ ለውጦ
እግዚአብሔር ፡ ደክሟል ፡ አረጀ ፡ ያለ ፡ ማነው
እኔስ ፡ እስከሚገባኝ ፡ ዛሬም ፡ ኤልሻዳይ ፡ ነው
የእኔ ፡ እምነት ፡ ቢፈተን ፡ ቢለዋወጥበት
እግዚአብሔር ፡ ግን ፡ ታምኖ ፡ አለ ፡ እዚያው ፡ ባለበት

አዝ፦ አሁንስ ፡ ተስፋዬ ፡ ማነው
ድጋፍ ፡ ምሶሶዬ ፡ ማነው
አለኝታ ፡ ጋሻዬ ፡ ማነው
መከታ ፡ አንባዬ ፡ ማነው
ማነው (፫x) ፡ እግዚአብሔር ፡ ነው

በልዑል ፡ መጠጊያ ፡ አንባ ፡ መሽጐ ፡ ሚኖር
ሁሉንም ፡ በሚችል ፡ አምላክ ፡ ጥላ ፡ ያድራል ፡ ከቶ ፡ አይሸበርም
ከአዳኞች ፡ ወጥመድ ፡ ከሚያስደነግጥም ፡ ነገር
ከክፉ ፡ ከልሎ ፡ ይታደገው ፡ የለ ፡ ሕያው ፡ እግዚአብሔር
የቀኑ ፡ ፍላጻ ፡ የሌሊቱ ፡ ግርማ ፡ አደጋና ፡ ጋኔል ፡ ተጓዥ ፡ በጨለማ
ሺ ፡ በሺ ፡ ሲያረግፈው ፡ ሲያስረግጠኝ ፡ ኖርኩኝ
@astemiren


@zilivingword
719 viewsBINU, 12:18
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-08-08 20:58:27 የዲያቢሎስ ሽንገላ/የሀጢአት ሽንገላ

(ክፍል 1)

"የዲያቢሎስን ሽንገላ ትቃወሙ ዘንድ እን
ዲቻላችሁ የእግዚአብሄርን እቃ ጦር ሁሉ
ልበሱ" (ኤፌሶን 6፥11)

ሁላችንም እንደምናውቀው ሽንገላ ማ
ለት ምላስና ልብ አንደበትና ውስጥ ለየቅ
ል ሆነው አንደበት መልካምን ነገር ሲናገር
ልብ ተቃራኒውን ሌላ ነገር ወይም ሌላ አ
መለካከት ይይዛል። ሰይጣንም ለፈለገው
እኛን ከዘላለም ሩጫ የማሰናከል እቅዱን
ለማስፈፀም ከሚጠቀምበት መንገድ አን
ዱ ሽንገላ ነው። በአጠቃላይ ሽንገላ ማታ
ለል መሸወድ ነው! እግዚአብሄርም ከሚጸ
የፋቸው ነገሮች አንዱ ነው።

ዲያቢሎስ በዘመናችን እኛን አማኞች
ን በዋነኝነት በአንድ መንገድ እየሸነገለን ይገኛል! ተሳክቶለታልም!! የምድርን ብል
ጭልጭ ዛሬ ታይቶ የሚጠፋ ንዋይን ባለ
ጠግነትን እንድንጎመጅ አይምሮአችንን በ
ዚ ተቆጣጥሮታል! ይሳካልሀል ይሆንልሀ
ትበለጽጋለህ ትጠረምሳለህ ትወልዳለህ ትከብዳለህ የሚለው ስብከት ቤተክርስቲ
ያናችንን ሞልቷል ቢባል ውሸት አይሆንም
እነዚህ የገንዘብ አገልጋዮች በሽንገላ ነፍ
ሳትን ያታልላሉ "ስኬት ብቻ ከጌታ ጋር ሆ
ነህ ውድቀት የሚባል አያጋጥምህም" የ
ሚል የአልጋ በአልጋ ኑሮ ስብከትን በልዩ
ወንጌል መልክ ይሰብካሉ በእውኑ ቃሉ ከ
ዚህ ጋር ይስማማል?? እንደውም መስቀ
ሌን ተሸከሙ ይላል እንጂ ማነው እስኪ
በምቾት ጌታን ያገለገለ ቃሉን እንያ! ይሆን
ልሀል ይሳካልሀል የሚለው ስብከት የጠ
ላት ሽንገላ ነው ጠላት ከቻለ በስጋም በነ
ፍስም ሊጎዳህ አጥብቆ ይሻል ሁኔታዎች
ካልተመቻቹለት ደሞ ለስጋህ መሸንገያ እ
ና መደለያን በማጉረስ ጥቅማ ጥቅም በ
መስጠት ዋነኛ አላማው የሆነውን ዘላለ
ምህን ሊያስጥልህ ያለ የሌለ ሀይሉን መ
ጠቀም ይጀምራል ያን ጊዜ አንተ ነቃ በል
በቃሉ ራስህን አበርታ!

በሰማያዊ ስፍራ በመንፈሳዊ በረከት
መባረክህን አጉልቶ ሳይነግርህ ማገልገል
እንደሚገባው መጠን ጌታን ሳያገለግል የ
አንተን ምድራዊ ችግር አስታኮ ሰበብ አር
ጎ የአንተ ዘመን ነው ትበለጽጋለህ በሚል
ህ አገልጋይ ውስጥ ጠላት የሽንገላን አን
ደበት እንዳስቀመጠ ያለጥርጥር እነግር
ሀለሁ!! ፍላጎትህ ስኬትም ከሆነ እንደእግ
ዚአብሄር ፈቃድና አላማ መሆን አለበት ስ
ኬት ሁሉ መልሚያህ አይምሰልህ መጥፊ
ያህም ሊሆን ይችላልና ስኬትን ለማግኘት
ብዙ ደክመህ ሊሆን ይችላል ግን ያለ ጌታ
ፈቃድ ስኬቱ ወደአንተ ቢመጣም የሰመረ
ህይወትን ማጣጣም አትችል ይሆናል።ስ
ለዚህ የእግዚአብሄርን ቀን ጠብቅ እንጂ ስኬት ለማግኘት ብለህ ባልተገባ መንገድ
አትሂድ አንተ ዘላለምህ የተሳካልህ ማን
ም ያልተሳካለት ነገር የተሳካልህ ማንም
ያላየውን ክብር ያየህ ጎረቤት የሰፈር ሰው
ያላየውን ያላመነ ያላየውን ሀይማኖተኛ ሀብታም ያላየውን የዘላለም ህይወት በክ
ርስቶስ ያገኘህ ስለሆንክ ብቻ በጌታ በጣ
ም ደስስስስ ሊልህ ይገባል እርግጥ ነው
ደሀ ከሰው በታች ሆነህ ሊሆን ይችላል ግ
ን ጠላት ደካማ ጎንህን ተጠቅሞ በሽንገላ
አታልሎ ጠልፎ እንዳይጥልህ መጀመሪያ
የቃሉን ጉልበት ታጠቅ!! አንተ በክርስቶስ
በሰማያዊ ስፍራ የተባረክ ዘላለማዊ ህይ
ወት ያለህ ከማንም በላይ ባለጠጋ ነህ!!!
ጠላት ነፍስህን አጥብቆ ሲፈልጋት የስጋ
ኑሮህን አመቻችቶ በትበለጽጋለህ ስብከት
እየሸነገለ አደንዝዞ አፍዝዞ ይጥልሀል!
ጠላት ኢየሱስን በምድራዊ ብልጥግና እ
ንደፈተነው አትዘንጋ!


በኢየሱስ ስም የዲያቢሎስ ሽንገላ እንዳ
ይጠልፈን የአንተን እቃ ጦር ሁሉ መጠቀ
ም መፈለግ እንድንጀምር ማስተዋልንና እ
ውቀትን እንድትሰጠን እጸልያለሁ!!

@ christology_GC

@astemiren

@zilivingword
583 viewsBINU, 17:58
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-08-07 20:42:54 የእብራውያን መጽሀፍ ጥናት ተከታታይ
ትምህርት ነው! ስሙት የቃሉን መገለጥ
በመንፈስ ቅዱስ በኩል ትሞላላችሁ



በወንድም ቢኒያም



@christology_GC

@astemiren

@zilivingword
531 viewsBINU, 17:42
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-08-07 08:16:17
513 viewsBINU, 05:16
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-08-06 11:24:16
"ሙሽራዬ"

ዘማሪት ሰናይት እንግዳ


ኢየሱስ ክርስቶስ የእኛ ሙሽራ ነው ሊወ
ስደን የሚመጣ ያውም በደም የገዛን እስ
ከሞት ድረስ ያፈቀረን ሙሽራችን ማራናታ
በቶሎ ይመጣል አሜንንን



@zilivingword

@astemiren
790 viewsBINU, edited  08:24
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-08-05 17:13:02 የሀጢአት ደመወዝ ሞት ነውና የእግዚአ
ብሄር የጸጋ ስጦታ ግን በክርስቶስ ኢየሱ
ስ ጌታችን የዘላለም ህይወት ነው። (ሮሜ
6፥23)
ሀጢአት የሚገባህን የስራህን የመተ
ላለፍህን ውጤት የዘላለምን ሞት ይሰጥ
ሀል ጸጋ ግን ባልተገባህ ነገር ላይ የልጅ
ነትን ስልጣን ይሰጥሀል! በማይገባህ ነገ
ር ላይ ይሾምሀል! ሀጢአት ፍርድን/ቅጣ
ትን ይዛ ትመጣለች ከእግዚአብሄር የሆነ
ው ጸጋ ግን ይቅርታን ምህረትን ይሰጥሀ
ል!

ሀጢአት ህጉንና ትእዛዛቱን አመካኝቶ
ይፈርድብሀል!ጸጋው ግን በክርስቶስ መስ
ዋእትነት አማካኝነት ከኩነኔ ነጻ ያወጣሀል
(ሮሜ8፥1) ሀጢአት ያለህን 9 መልካም ነ
ገር አይቆጥርልህም ይልቁንም በአንዷ ስ
ህተትህ ጽድቅን ያስቀርብሀል! በክርስቶ
ስ ያገኘኸው ጸጋ ግን የጎደለህን ጽድቅ በ
ኢየሱስ ይሞላልሀል! ይልቁንም ጭራሽ የ
ሌለህን ጽድቅ ይቆጥርልሀል!

ሀጢአት ከእግዚአብሄር ጋር ጠላት ያ
ደርግሀል! ጸጋው ግን በልጁ ደም ያስታር
ቅሀል! (ሮሜ5፥11) ሀጢአት በአንድ ሰው
ምክንያት ወደአለም ገባ ጸጋው ደግሞ በ
አንዱ በክርስቶስ ለአለሙ ሁሉ ተትረፈረፈ
(ሮሜ 5፥15) ሀጢአት ቀንበር ይጭናል!
የጌታችን ጸጋ ግን በነጻነት እንድትኖር ፈት
ቶ ይለቅሀል!(ግን ያለሀጢአት እንድትኖር)
(ገላትያ 5፥1)
ጢአት በደልን ይቆጥርብሀል! ጸጋ ግን
በኢየሱስ ደም በምህረት ያልፍሀል!(ግን
በመንፈስ ቅዱስ እየወቀሰህ) ጸጋ ይልቁን
ም ያልደከምክበትን የጌታን ስጦታ ወይ
ም ጸጋውን ያለብስሀል! ሀጢአት ከጌታ ያ
ርቃል ጸጋ ግን ወደኢየሱስ ያቀርባል!(ሮ
ሜ 5፥2)


ሀጢአት ለጨለማው ስልጣን አሳል
ፎ ይሰጥሀል! ጸጋ ግን ወደሚደነቀው ብ
ርሀን ወደ ኢየሱስ ያሻግርሀል! ሀጢአት ነ
ፍስህን ይገድላል! ጸጋ ግን ህይወትን ይሰ
ጥሀል! ሀጢአት የህሊና እረፍት ይነሳሀል!
ጸጋ ግን በክርስቶስ በተሰራልህ ስራ ሰላ
ምን እረፍትን ይሰጥሀል!(ሮሜ 5፥1-2)
ሀጢአት ለሀሰት አሰራር አሳልፎ ይሰጥሀ
ል ጸጋ ግን ወደ ወንጌል እውነት ይጠራሀ
ል(ገላትያ 1፥6)። ሀጢአት በስጋ የመሆን
ህ ውጤት ነው ጸጋ ግን በእግዚአብሄር
መንፈስ ህልውና ውስጥ እንዳለህ የሚ
መሰክር ማስረጃ ነው!!(ገላትያ 5፥17-22
) ሀጢአት ያለርህራሄ መቅጣትን ያውቅበ
ል ጸጋ ግን ከኢየሱስ ፍቅር የተነሳ ለምህረ
ትና ለይቅርታ ይቸኩላል!


@christology_GC
@christology_GC

@astemiren
@astemiren

@zilivingword
@zilivingword

መንፈሳዊ ተከታታይ ትምህርት መማርን
በጣም ስትፈልጉ ለነበራችሁ መልካም ዜ
ና አለኝ በinbox እንድታስተምረኝ ፈልጋ
ለሁ ብቻ በሉኝ የእግዚአብሄርን ቃል እንከ
ፋፈላለን! @wbinu @wbinu
480 viewsBINU, 14:13
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-08-04 16:49:02 -የህያው አምላክ ባሪያ ዳንኤል-


ደካማ ጎን ሲጠፋብህ ጠንካራ ጎንህን እን
ደ ደካማ ጎን በመቁጠር ጠላትህ ሊፈትን
ህ ቀዳዳ መፈለግ ይጀምራል ያንጊዜ በእ
ምነትና በተስፋ የማይሻገሩት የለምና ጉዞ
ህን ወደፊት በጽናት ተጓዝ!ጸሎትህን ጠላ
ት ባወጣው አዋጅ አትሻር! ዳንኤል ጠንካ
ራ ጎኑ መጸለይ ነበርና ለንጉሱ ዳርዮስ ከአ
ንተ ከንጉሱ በቀር ለ30 ቀን ለአምላኩ ማ
ንም ልመና እንዳያቀርብ ብለህ የማይለወ
ጥ የማይሻር ህግ አውጣ አሉት ህጉንም የሻረ በአንበሶች ጉድጓድ እንዲጣል ተስ
ማሙ። ባሉት መሰረት ንጉሱ ህጉን አወ
ጣላቸው ዳንኤልም ይሄን በሰማ ጊዜ መ ጸለዩን አላቆመም ቀድሞም እንደሚያደር
ገው እንደወትሮው ጭራሽ መስኮቱን ከፍ
ቶ ይፀልይ ጀመረ። ጠላት ጦሩን በአንተ
ላይ ቢያሰልፍም ከአንተ ጋር ያለው ከሁ
ሉም ይበልጣልና ጠላትህ ከአምላክህ ጋ
ር እንዳትነጋገር ጸሎት እንድታቆም ቢፈት
ንህም ከታማኙ ጌታ ጋር የጀመርከውን ግ
ንኙነት አታቋርጥ! ውድቀት በጠላት የፈተ
ና ብዛት ሳይሆን በእግዚአብሄር ካለመተ
ማመን የሚመጣ ነው። በፈጣሪህ ላይ አ
ለመተማመን የውድቀት ውድቀት ነው!!

ጠላቶቹ በበረቱበት ጊዜ እሱም በአም
ላኩ ብርታትን ጨመረ እንጂ እጅ አልሰጠ
ም! መሳፍንቱ ሊጥሉት ባሰቡት ነገር እሱ
ጸንቶ ተገኘ! ምንም እንዳልተፈጠረ ያለስጋ
ት ሁሌም የሚያደርገውን ያደርጋል። በህ
ጉም መሰረት ንጉሱ የምታመልከው አም
ላክ ያድንህ ብሎ ወደአንበሶች ጉድጓድ
ጣለው። ንጉሱም በነጋታው ወደጉድጓዱ
ቀርቦ (ዳን.6፥20) ላይ የህያው አምላ
ክ ባርያ ዳንኤል ሆይ ሁልጊዜ የምታመል
ከው አምላክህ ከአንበሶች ያድንህ ዘንድ
ችሎአልን? አለው እሱም አምላኩ መላእ
ክቱን ልኮ የአንበሶቹን አፍ እንደዘጋ ነገረ
ው።

ንጉሱ ራሱ የዳንኤል አምላክ የዋዛ እንዳልሆነ ይገምታል ማለትም ምን አልባ
ት ከአንበሶች መንጋጋ ሊያስጥለው እንደ
ሚችል ሙሉ በሙሉ ባይሆንም በከፊል ያ
ምናል ለዛም ነው አንበሶቹ ዳንኤልን በል
ተው ይጨርሳሉ በሚባልበት ጊዜ በነጋታ
ው መጥቶ አምላኩ እንዳዳነው የጠየቀ
ው "የህያው አምላክ ባሪያ" ብሎ ጠር
ቶታል። ስለዚህ የዳንኤልን አምላክ በህያ
ውነቱ አዳኝነቱ በጥቂቱም ቢሆን ይታመና
ል። (ቁ.23 ላይ በአምላኩ ታምኖ ነበርና
አንዳች ጉዳት አልተገኘበትም ይላል) ንጉ
ሱም በመንግስቱ ግዛት ለሚኖሩት ህዝቦ
ች ሁሉ በተለያዩ ቋንቋዎች ለዳንኤል አም
ላክ እንዲገዙና እንዲንቀጠቀጡ እሱ ህያ
ው አምላክ ግዛቱም እስከመጨረሻ የሚ
ኖር ነው ያድናል ይታደግማል ድንቅን ያደ
ርጋል ብሎ መሰከረ።በመጀመሪያ እምነቱ
ከአንበሶች አዳነው በዚ የተነሳ ንጉሱ የእ
ግዚአብሄር ሀይል ተገለጠለት እምነቱ በ
2 ነገሮች ውጤት አመጣ አንድም መዳን
ሌላው ደሞ የእግዚአብሄር ማዳን ለሰዎ ች ሁሉ መታወቅ ቻለ የተሰራው ስራ በአ
ለም ተመሰከረ። እምነት ራሳችንን ብቻ ሳይሆን
የሚያድነው የጸና እምነት ካለን አምላክ ለ
እኛ በሚሰራው ነገር ውስጥ ማዳኑን ለሰ
ዎች ሁሉ ይገልጣል! አምላክነቱን ዘላለማ
ዊነቱን በእኛ በኩል ለህዝብ ሁሉ ይገልጣ
ል።

ዳንኤል የአምላኩን ህግ ከማክበር ውጪ
ሌላ ምንም ደካማ ጎን አልተገኘበትም! በ
ኢየሱስ ስም እንደ ዳንኤል ስህተት ተፈል
ጎ የማይገኝብን አምላካችንን የምንፈራ በ
ጸሎት የተጋን ታማኝ አገልጋዮች ያድርገን



@zilivingword


@astemiren

@christology_GC
526 viewsBINU, 13:49
ክፈት / አስተያየት ይስጡ