Get Mystery Box with random crypto!

Zena Nebab ✅

የቴሌግራም ቻናል አርማ zena_nebab — Zena Nebab ✅ Z
የቴሌግራም ቻናል አርማ zena_nebab — Zena Nebab ✅
የሰርጥ አድራሻ: @zena_nebab
ምድቦች: ዜና
ቋንቋ: አማርኛ
ተመዝጋቢዎች: 2.67K
የሰርጥ መግለጫ

ትኩስ የሃገር ውስጥ እና የውጪ ዜናዎችን ከታማኝ ምንጭ የሚያገኙበት ቻናል
Keepup with the world, find information, get the headlines, be one step ahead, get the news in one place.
📩 @All_Input

Ratings & Reviews

2.67

3 reviews

Reviews can be left only by registered users. All reviews are moderated by admins.

5 stars

0

4 stars

1

3 stars

0

2 stars

2

1 stars

0


የቅርብ ጊዜ መልዕክቶች 2

2021-08-24 13:13:00 በሱዳን ጎርፍ ባስከተለው አደጋ ከ50 በላይ ሰዎች ህይወት ማለፉን ተከትሎ ግብጽ ሃዘኗን ገልጻለች፡፡

በጎርፍ አደጋው እናትና ልጅን ጨምሮ የ52 ዜጎች ህይወት ማለፉን የሀገሪቱ የሲቪል መከላከያ ብሔራዊ ምክር ቤትቃል አቀባይ አብደል ጋሊል አብደል ራሂም መናገራቸውን ኢጂብት ቱዴይ ዘግቧል።

ሱዳን አና ግብጽ ከኢትዮጵያ ታላቁ ህዳሴ ግድብ ግንባታ ጋር ተያይዞ የውሃ እጥረት ያጋጥማል በማለት ተደጋጋሚ ቅሬታ እንደሚያቀርቡ ይታወቃል፡፡

በአንጻሩ በቀጠናው በቂ የውሃ አቅርቦት መኖሩን ተከትሎ ሱዳን በተደጋጋሚ ለጎርፍ አደጋ እየተጋለጠች መሆኑን መረጃዎች ያመላክታሉ፡፡
671 views10:13
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2021-08-24 13:11:18 በአሜሪካ የሚገኙ ሕፃናት በዴልታ ኮቪድ 19 ቫይረስ እየተጠቁ መሆኑ ተጠቆመ፡፡የአሜሪካ ፔዲያትሪክስ አካዳሚ እና የሕፃናት ሆስፒታል ማሕበር ባወጡት ሪፖርት÷ ባሳለፍነው ሳምንት ብቻ በሀገሪቱ ወደ 94 ሺህ የሚጠጉ ሕፃናት በቫይረሱ ተጠቅተዋል ፡፡

ሉዚያና እና ፍሎሪዳ በርካታ በኮቪድ 19 ቫይረስ የተጠቁ ሕፃናት ሪፖርት የተደረገባቸው አካባቢዎች እንደሆኑም ተመላክቷል፡፡

በኒው ኦርሊያንስ የሕፃናት ሆስፒታል ውስጥ የሚሰራ ዶክተር ማርክ ክላይን ÷ በሆስፒታላቸው ውስጥ በኮሮና ቫይረስ ተጠቅተው ሊታከሙ ከሚሄዱ ሕፃናት ግማሽ ያህሉ እድሜያቸው ከ 2 ዓመት በታች ነው ብሏል፡፡

የተቀሩት በቫይረሱ የተጠቁና በሆስፒታሉ ለሕክምና የተገኙ ሕፃናት ደግሞ እድሜያቸው ከ 5 እስከ 10 ባለው ክልል ውስጥ የሚገኙ መሆናቸውን ጠቁመው፥ በጣም ሕፃናት በመሆናቸው ክትባት ለመስጠት አስቸጋሪ እንዳደረገው ዶክተሩ ገልፀዋል፡፡

ወረርሽኙ ከተከሰተ ወዲህ እስካሁን ወደ 4 ነጥብ 3 ሚሊየን የሚሆኑ ሕፃናት ቫይረሱ እንደተገኘባቸውና ቁጥሩም ከጊዜ ወደ ጊዜ እያሻቀበ መሆኑን ነው ከሲጂቲ ኤን ያገኘነው መረጃ የሚያመላክተው፡፡
649 views10:11
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2021-08-24 13:10:39 በኢትዮጵያ 3ኛው የኮቪድ 19 ወረርሽኝ መከሰቱን የሚያሳዩ ምልክቶች መታየታቸው ተገለጸ

On Aug 24, 2021  227

አዲስ አበባ፣ ነሐሴ 18፣ 2013 (ኤፍ ቢ ሲ) ሶስተኛው የኮቪድ 19 ወረርሽኝ በኢትዮጵያ መከሰቱን የሚያሳይ ምልክት መታየቱን የጤና ሚኒስትር ዶክተር ሊያ ታደሰ ገለጹ።

 

ዶክተር ሊያ ጉዳዩን አስመልክተው ዛሬ በሰጡት መግለጫ ÷ በኢትዮጵያ ባሳለፍነው ሳምንት ብቻ 5 ሺህ 547 ሰዎች በኮሮና ቫይረስ መያዛቸውን ተናግረዋል፡፡

 

በአንድ ቀን ውስጥ ከ1 ሺህ በላይ ሰዎች መያዛቸውን የገለጹት ሚኒስትሯ÷ የወረርሽኙ መጠን ከዚህ በፊት ካለው በእጅጉ መጨመሩን ተናግረዋል።

 

የኮቪድ 19 ወረርሽኝ በአሁኑ ሰዓት ቫይረሱ የሚገኝበት ሰው ቁጥር ምጣኔ በእጅጉ መጨመርም ሶስተኛው የኮቪድ 19 ወረርሽኝ በኢትዮጵያ መከሰቱን የሚያመላክት መሆኑን ጠቁመዋል፡፡

 

ማህበረሰቡም ከዚህ በፊት የሚያደርገውን ጥንቃቄ አጠናክሮ መቀጠል እንዳለበት ሚኒስትሯ አሳስበዋል፡፡

 

በቅድስት ተስፋዬ
629 viewsedited  10:10
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2021-08-24 13:08:29 ዕድሜያቸው ከ35 በላይ ለሆኑ የህብረተሰብ ክፍሎች የኮቪድ 19 ክትባት በመንግስት ጤና ጣቢያዎች ሊሰጥ መሆኑን የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ጤና ቢሮ አስታወቀ፡፡

የጤና ቢሮው ኃላፊ ዶክተር ዮሐንስ ጫላ የኮሮና ቫይረስ ወረርሽኝ ካለፉት 4 ሳምንት ጀምሮ በአዲስ አበባ በኮቪድ 19 የመያዝ መጠን ፤ በጽኑ የሚታመሙ ሰዎች ፤ እንዲሁም በበሽታዉ ምክኒያት ህይወታቸዉን ያጡ ሰዎች ቁጥር ከፍተኛ ጭማሪ አሳይቷል : :

ይህም በበርካታ የአፍሪካ ሀገራት የታየውን የወረርሽኙ 3ኛዉ ማአበል በከተማችን የመታይት አዝማሚያ ያሳያል ብለዋል : :

የኮቪድ 19 ክትባትን መስጠት ወረርሽኙን ለመከላከል ትልቅ አስተዋጽኦ የሚያደርግ ሲሆን÷ በኮቫክስ ፋሲሊቲ አማካይነት ወደ ሀገራችን የሚገቡትን ክትባቶች በየደረጃዉ ላሉ በስራ ባህሪያቸዉ ለቫይረሱ ይበልጥ ተጋለጭ ለሆኑ የጤና ባለሙያወች ፤ እድሜቸዉ ከ65 አመት በላይ ለሆኑ እና እድሜቸዉ ከ 55 – 64 የሆኑና ተጓዳኝ የጤና ችግር ላለባቸዉ ብቻ ቅድሚያ እንዲያገኙ ሲደረግ መቆቱን ጠቅሰዋል፡፡

በአሁኑ ወቅትም በለጋሽ ሀገራት እገዛ የተለያዩ ክትባቶች ወደ ሀገራችን እየገቡ እንደሚገኙና እስካሁንም አስትራዜኒካ ፤ ሲኖፋርምና ጆንሰን ጆንሰን የሚባሉ ክትባቶች አገልግሎት ላይ እየዋሉ ይገኛሉ ብለዋል : :

የክትባቶቹ መጠሪያ የተለያየ ቢሆንም በደህንነታቸዉና ፍቱንነታቸዉ፣ የወረርሽኙን ስርጭት ከመቆጣጠርና በወረርሽኙ ሊደርስ የሚችለዉን የከፋ ህመምና ሞት ከመከላከል አንጻር ሁሉም ክትባቶች ተመሳሳይ ዉጤት ያላቸዉ መሆኑን አንስተዋል፡፡

በዚህም ማህበረሰቡ ያለምንም ስጋት ወደ መንግስት ጤና ጣቢያዎች በመሄድ ክትባቱን በነፃ ያለምንም ክፍያ በመዉሰድ ራሱንና ቤተሰቡን ከአስከፊ ወረርሽኝ እንዲጠብቅም ዶክተር ዮሐንስ ማሳሰባቸውን ከቢሮው ያገኘነው መረጃ ያመለክታል: :

በዚህ ዙር የሚሰጠው ክትባት ከዚህ በፊት ክትባቱን ያልወሰዱ ከ1ሚሊየን በላይ የህብረተሰብ ክፍሎች እንደሆኑ ገልፀው÷ እድሜቸዉ 35 ዓመት የሆኑ: እድሜቸዉ ከ 18 አመት በላይ የሆኑና ተጓዳኝ በሽታ ላለባቸዉ ሰዎች ክትባቱን ለመስጠት ታስቧል፡፡

በተጨማሪም በስራ ባህሪያቸዉ ተጋላጭ ናቸዉ ተብለዉ የተለዩ ከ105 በላይ ለሚሆኑ የመንግስትና የግል ተቋማት ክትባቱን ለመስጠት መታቀዱንም ገልጸዋል : :

በተጨማሪም ኃላፊው ክትባቱን መዉሰድ ወረርሽኙን ለመከላከል አንዱ ዘዴ ቢሆንም የኮቪድ 19 ወረርሽኝ መከላከያ ዘዴዎችን መተግበር አስፈላጊ መሆኑንም ገልጸዋል : :

ህብረተሰቡ ክትባቱ የሚሰጠዉ በነፃ መሆኑን አዉቆ ምንም አይነት ክፍያ የሚጠይቅ አካል ካለ ለጤና ተቛሙ ሀላፊዎች ወይም በአቅራቢያዉ ለሚገኝ የህግ አካላት ጥቆማ እንዲሰጡ አሳስበው ቢሮው ጉዳዩን ተከታትሎ እርምጃ የሚወስድ መሆኑን ተናግረዋል : :
612 views10:08
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2021-08-24 13:07:07 የጸጥታ ጥበቃው ምክር ቤት በመጪው ሐሙስ በትግራይ ጉዳይ እንደሚመክር ተሰማ !


የተባበሩት መንግስታት ድርጅት የጸጥታ ጥበቃው ምክር ቤት፤ በኢትዮጵያ በትግራይ ክልል ባለው ነባራዊ ሁኔታ ላይ በመጪው ሐሙስ በዝግ ሊመክር መሆኑ ተሰምቷል፡፡ ምክር ቤቱ በትግራይ ክልል ውጊያ ከተቀሰቀሰ ወዲህ በጉዳዩ ላይ ሲወያይ የሐሙሱ ለስምንተኛ ጊዜ ነው።


የትግራይ ሁኔታን በተመለከተ የጸጥታው ምክር ቤት ስብሰባ እንዲያደርግ የጠየቁት ስድስት ሀገራት መሆናቸው የተነገረው ሲሆን፣ እነዚህ አገራት አየርላንድ፣ ኢስቶኒያ፣ ፈረንሳይ፣ ኖርዌይ፣ ብሪታኒያ እና አሜሪካ ናቸው፡፡


ስድስቱ ሀገራት ስብሰባው እንዲካሄድ የጠየቁት፤ የተባበሩት መንግስታት ድርጅት ዋና ጸሐፊ አንቶኒዮ ጉተሬዝ በኢትዮጵያ የተኩስ አቁም እንዲደረግ ጥሪ ማቅረባቸውን ተከትሎ ስለመሆኑም ተዘግቧል፡፡


ጉተሬዝ በሐሙሱ ስብሰባ ላይ ተገኝተው በጉዳዩ ላይ ማብራሪያ ይሰጣሉ ተብሎ እንደሚጠበቅ ጉዳዩን በቅርብ የሚያውቁ የዲፕሎማቲክ ምንጮች ነግረውኛል ብሎ ኢትዮጵያ ኢንሳይደር ድረ ገጽ ጽፏል፡፡


ከተመድ ዋና ጸሐፊ በተጨማሪ በቅርቡ ወደ ኢትዮጵያ በተጓዙበት ወቅት ትግራይን ጎብኝተው የተመለሱት የድርጅቱ የሰብዓዊ እና የአስቸኳይ እርዳታ አስተባባሪ ማርቲን ግሪፊትዝም በስብሰባው ላይ እንደሚሳተፉ ነው የተነገረው፡፡
571 views10:07
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2021-08-24 12:59:15 የሽብር ቡድኖቹን እንቅስቃሴ ለመግታት ዝግጅት ማድረጉን የኦሮሞ ብሄረሰብ ልዩ ዞን አስታወቀ
************************

የህወሓትና ሸኔ የሽብር ቡድኖችን እንቅስቃሴ ለመግታት በቂ ዝግጅት ማድረጉን በአማራ ክልል የኦሮሞ ብሔረሰብ አስተዳደር ልዩ ዞን አስታወቀ፡፡

የፌደራል፣ የክልልና የኦሮሞ ብሔረሰብ አስተዳደር ልዩ ዞን የመንግስት የስራ ሃላፊዎች በባቲ ግንባር የተሰማራውን ሚሊሻ የስራ እንቅስቃሴ ጎብኝተዋል፡፡

የልዩ ዞኑ ወረዳዎች፣ ከደቡብ ወሎና የአፋር ክልል የሚዋሰኑባቸው ቦታዎች ላይ የተሰማራው ሚሊሻ የሽብር ቡድኖቹ ሰርገው መግባት የሚችሉበትን መንገድ ሙሉ ለሙሉ ዘግተናል ብሏል፡፡

የኢኖቬሽንና ቴክኖሎጂ ሚኒስትር ዴኤታ አህመዲን መሐመድ (ዶ/ር) የፖለቲካ አመራሩ፣ የሀገር ሽማግሌዎችና የፀጥታ ሃይሉ የሽብር ቡድኖቹን ለመመከት ያደረጉትን ዝግጅት አድንቀዋል፡፡

መተባበር ከቻልን አንዳች ሃይል አይደፍረንም ያሉት ሚኒስትር ዴኤታው የስጋት ቦታዎችን ሁሉ በመድፈን ህዝባችንን ከስጋት ነፃ ማድረግ አለብን ብለዋል፡፡

በአማራ ክልል የኦሮሞ ብሔረሰብ አስተዳደር ልዩ ዞን ዋና አስተዳዳሪ አቶ አህመድ ሐሰን የህዝባችን ጠላት የሆኑትን የህወሓትና የሸኔ ቡድኖችን የሰርጎ ገብ እንቅስቃሴ ለመግታት ሚሊሻው በአስተማማኝ ቁመና ላይ መሆኑን ተናግረዋል።

የአማራ ክልል ገቢዎች ቢሮ ምክትል ኃላፊ ፍቅረማርያም ደጀኔ የኢትዮጵያውያን ሁሉ ጠላት የሆኑትን ቡድኖች ለመመከት ትብብር ወሳኝ መሆኑን አንስተዋል፡፡
594 views09:59
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2021-08-24 12:58:09 የተሻሻለው የታሪፍ ደንብ የጦር መሣሪያዎችን በነጻ ማስገባት የሚፈቅድ መሆኑ ተገለጸ

አዲስ የተሻሻለው የታሪፍ ደንብ የወታደራዊ (ሚሊተሪ) ከባድ የጦር መሣሪያዎችን ማለትም እንደ ጠመንጃ፣ ሮኬት፣ ላውንቸር እና እሳት የሚተፉ መሣሪያዎችን ከቀረጥ ነጻ እንዲገቡ የሚፈቅድ መሆኑ ተገለጸ።
የአገር መከላከያ ሚኒስቴር፣ የፌዴራል እና የክልል ፖሊስ ተቋሞች፣ የሕዝብ ደሕንነት ተቋሞች ወደ አገር የሚያስገቧቸዉ የመከላከያና የሕዝብ ደህንነት መሣሪያዎች፣ ለነዚሁ አገልግሎት የሚዉሉ ክፍሎችና እና ቁሳቁሶች (አክሰሰሪዎች) በነጻ እንዲገቡ ማሻሻያው ይፈቅዳል።
581 views09:58
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2021-08-24 09:17:15 የኢትዮጵያ ጠቅላይ ዐቃቤ ሕግ ጌዲዮን ጢሞቴዎስ (ዶ/ር) ከቢቢሲ ሀርድቶክ ፕሮግራም ጋር ሰኞ ዕለት ቆይታ አድርገው በትግራይ ከተከሰተው ጦርነት ጋር በተያያዘ ለተነሱላቸው ጥያቄዎች ምላሽ ሰጥተዋል።

ትግራይ ውስጥ ተጀምሮ ሌሎች ክልሎች ስለተስፋፋው ጦርነት ፣ በትግራይ ስለተቋረጡት መሰረታዊ አገልግሎቶች፣ ሰለሰብአዊ መብት ጥሰቶች፣ ስለእርዳታ አቅርቦት እና ተያያዥ ጉዳዮች ጠቅላይ ዐቃቤ ሕጉ ከስቴፈን ሳከር ተወያይተዋል።

ዶ/ር ጌዲዮን በምን ጉዳዮች ላይ ምላሽ ሰጡ ?
- የሰብዓዊ እርዳታ ጉዳይ
- ሰላማዊ መፍትሔ
- የትግራይ ተወላጆች እስር
- የሰብዓዊ መብት ጥሰት ክሶች
- ስለመሠረታዊ አገልግሎቶች ... ሌሎችም።

ያንብቡ : telegra.ph/BBC-HardTalk-08-24 / ጥሩ የሆነ የኢንተርኔት ግንኙነት ማግኘት ከቻላችሁም ከላይ የተያያዘውን የድምፅ ፋይል ያዳምጡ።

Credit : BBC Amharic Service

tikvahethiopia
615 views06:17
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2021-08-24 09:13:36 ቦርዱ የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ሕዝበ ውሳኔ መስከረም 20 እንዲካሄድ ወሰነ


የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ጳጉሜ 1፣ 2013 ይካሄዳል ተብሎ ቀጠሮ የያዘለትን የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ሕዝበ ውሳኔ በአዲስ ዓመት መስከረም 20 እንዲካሄድ ውሳኔ አሳልፏል፡፡


ምርጫ ቦርድ ለሁለት ጊዜያት ያራዘመው ሕዝበ ውሳኔ፣ በከፋ፣ በዳውሮ፣ ቤንች ሸኮ፣ ምዕራብ ኦሞና የሸካ ዞኖች እንዲሁም የኮንታ ልዩ ወረዳን የሚያሣትፍ ነው፡፡


በሌላ በኩል ሰኔ 14፣ 2013 ምርጫ ባልተካሄደባቸው ምርጫ ክልሎች የድምጽ መስጫ ቀን በተመሳሳይ መስከረም 20፣ 2014 እንዲሆን መወሰኑን ምርጫ ቦርድ አስታውቋል፡፡

በጉዳዩ ላይ ነሐሴ 13፣ 2013 ምርጫ ባልተደረገባቸው የምርጫ ክልሎች ከሚወዳደሩ ፖለቲካ ፓርቲዎች ጋር ውይይት ማድረጉን ያስታወቀው የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ፣ ከፓርቲ ተወካዮቹ ሀገሪቱ አሁን ካለችበት ሁኔታ አንጻር ምርጫ ማድረጉ ተገቢ አይደለም የሚል አስተያየት የሰጡ መኖራቸውን፣ በአንጻሩ ደግሞ ሰኔ 14፣ 2013 የተደረገውም ምርጫ የተደረገው በተመሳሳይ የፀጥታ ችግር በነበረበት ሁኔታ፤ አንጻራዊ ሰላም ያለባቸው አካባቢዎች ተለይተው እንደተካሄደ ጠቅሰው፤ አሁን የሚካሄደው ምርጫም እንደቀደመው ሁሉ የተሻለ ፀጥታ ያለባቸውን አካባቢዎች በመለየት ማካሄድ እንደሚቻል አስተያየት ተሰጥቷል መባሉንም ገልጧል፡፡

በመጨረሻም መስከረም 20 ድምፅ አሰጣጡ ይከናወን ያለው ቦርዱ፣ ምርጫው የሚከናወነው በሶማሌ፣ በሐረሪ እና በደቡብ ክልሎች መሆኑንም አስታውቋል፡፡
AmbaDigMedia
614 views06:13
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2021-08-24 09:12:08 የኢትዮጵያ የሀገር መከላከያ ሰራዊት በአማራ ክልል ደቡብ ጎንደር ዞን በህወሓት ተይዘው የነበሩ ቦታዎች ማስለቀቁን አስታወቀ።

#Ethiopia : መከላከያ ሰራዊት ከአማራ ልዩ ኃይል እና የአማራ ሚሊሻ ጋር በመሆን በወሰደው እርምጃ ፦ ጋሳይ፣ ክምር ድንጋይ፣ ጎብጎብ፣ ሳሊና ንፋስ መውጫ ነፃ ማውጣቱን ገልጿል።

የንፋስ መውጫ ከተማ ነዋሪዎች ህወሓት በንፋስ መውጫ ከተማ ንፁሃንን መግደሉንና በርካታ ውድመት ማድረሱን የተናገሩ ሲሆን ሀገር መከላከያ ሰራዊት ወደከተማቸው ሲገባ አቀባበል አድርገዋል።

በሀገር መከላከያ ሰራዊት የሰሜን ምዕራብ ዕዝ አንደኛ ኮር አዛዥ ብርጋዴር ጄነራል ብርሃኑ ጥላሁን ፤ ከሰሞኑን ህወሓት ህዝቡን በጣም እንደጎዳው ፤ የቀረ ነገር ሳይኖር ዘርፊያ እንደፈፀመ ገልፀው ፥ "ህዝባችን እንዲህ ያለ ወራዳ ተግባር ማየቱ የሚያሳዝን ነው፤ ነገር ግን አሁን ላይ ቡድኑ ዋጋውን እያገኘ ነው" ብለዋል።
ብርጋዴር ጄነራል ብርሃኑ ጥላሁን ፥ ህወሓት በወረራ የያዛቸውን ቦታዎች በሙሉ የማስለቀቅ እና የማፅዳት ስራ እየተሰራ ነው ያሉ ሲሆን አሁን ላይ ከመኪና ወርዶ እየተበታተነ ነው እሱን የመልቀም ስራ እየተሰራ ነው፤ የሚሸሽበትም መንገድ ተዘግቷል፤ ትግራይ ውስጥ ያየውን ጉድ እዚህም ያየዋል፤ እዚህ ገብቶ መውጣት የሚባል ነገር እንደሌለ ያየዋል" ብለዋል።
አዛዡ ፤ ህወሃት ስርዓት መቀየር ነው ፍላጎቴ ይላል እንጂ ተግባሩ ሀገር ማፍረስ እና ሀገር ማውደም ነው ፣ ኢትዮጵያን ማፍረስ ነው የማፍረስ ምልክቱም ህዝቡን ምን እያረገው እንዳለ ማየት በቂ ነው ፤ የከተማውን ህዝብ ጠይቁ ምን አድርጓቸው እንደሄደ ፤ እነሱ የስርዓት አራማጅ አይደሉም ፤ ድሆች ናቸው ፤ ከድሆቹ አፍ ነጥቆ ሽሮ ሳይቀር እየጫነ እየወሰደ ያለው" ሲሉ አስረድተዋል።

"በአጠቃላይ ቡድኑ ስርዓት መቀየር ብቻ ሳይሆን ሀገር ማጥፋት ስለሆነ በዚህ ሀገር አጥፊ ኃይል ላይ ማንም ትዕግስት ሊኖረው አይገባም ኢትዮጵያን ወዳታለሁ የሚል ሁሉ መሰለፍ አለበት" ብለዋል። ይህ ደግሞ ለማንም ሳይሆን እራስን እና ሀገርን ለመከላከል እና ሀገርን ለማዳን ነው" ሲሉ ተናግረዋል።
Natnael Mekonen
634 views06:12
ክፈት / አስተያየት ይስጡ