Get Mystery Box with random crypto!

Zena Nebab ✅

የቴሌግራም ቻናል አርማ zena_nebab — Zena Nebab ✅ Z
የቴሌግራም ቻናል አርማ zena_nebab — Zena Nebab ✅
የሰርጥ አድራሻ: @zena_nebab
ምድቦች: ዜና
ቋንቋ: አማርኛ
ተመዝጋቢዎች: 2.67K
የሰርጥ መግለጫ

ትኩስ የሃገር ውስጥ እና የውጪ ዜናዎችን ከታማኝ ምንጭ የሚያገኙበት ቻናል
Keepup with the world, find information, get the headlines, be one step ahead, get the news in one place.
📩 @All_Input

Ratings & Reviews

2.67

3 reviews

Reviews can be left only by registered users. All reviews are moderated by admins.

5 stars

0

4 stars

1

3 stars

0

2 stars

2

1 stars

0


የቅርብ ጊዜ መልዕክቶች

2022-05-28 09:55:54 https://t.me/kingswoodethiopia
486 views06:55
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2021-08-24 19:01:45 የሰላም ሚኒስቴር ሚኒስትር ሙፈሪሃት ካሚል ከአውሮፓ ህብረት የአፍሪካ ቀንድ ልዩ ተወካይ አኔቴ ዌበር ጋር ተወያዩ።

በውይይቱ ሚኒስትሯ በሀገሪቱ ወቅታዊ ሁኔታና ቀጠናዊ ጉዳዮች ላይ ማብራሪያ ሰጥተዋል።

የአውሮፓ ህብረት ለሀገሪቱ ልማት በተለያዩ መስኮች እያደረገ ለሚገኘውን ድጋፍ ማመስገናቸውን ከሚኒስቴሩ ያገኘነው መረጃ አመላክቷል።

አኔቴ ዌበር በበኩላቸው የአውሮፓ ህብረት ከኢትዮጵያ መንግስት ጋር ለረጅም ዘመናት የቆየውን መልካም የዲፕሎማሲያዊና የልማት ትብብር ለመቀጠል ያለውን ጠንካራ ፍላጎት መግለፃቸውን ሚኒስቴር መስሪያቤቱ አስታውቋል።
2.8K views16:01
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2021-08-24 13:21:51 በኢትዮጲያ የኢንሹራንስ ማቋቋሚያ ካፒታል መጠን ሊጨምር ነው በሚል ስለወጣው መረጃ አላውቅም ሲል የኢትዮጲያ ብሄራዊ ባንክ ገለጸ፡፡

የኢትዮጵያ ብሄራዊ ባንክ ምክትል ገዢ አቶ ሰለሞን ደስታ የኢንሹራንስ ኢንዱስትሪ ማቋቋሚያ ካፒታል መጠን ሊጨምር ነው በሚል በአንድ መገናኛ ብዙሃን ላይ ስለወጣው ዘገባ ምንም አይነት መረጃ የለኝም ሲሉ ለአሃዱ ገልጸዋል፡፡

በባንኩ አሰራር መሰረት አዲስ ለሚመሰረቱ የኢንሹራንስ ኩባንያዎች የማቋቋሚያ ካፒታል አሁን በስራ ላይ ከሚገኘው የካፒታል መጠን ጭማሪ ቢደረግ እንኳን ከውሳኔ ሳይደረስ ጭማሪ ሊደረግ ነው ተብሎ ለህዝብ ይፋ አይደረግም ያሉት የባንኩ ምክትል ገዢ አቶ ሰለሞን አሁን ላይ ዝርዝር ሁኔታውን ለማስረዳት የሚያስችል መረጃ የለኝም ሲሉም ተናግረዋል፡፡

አሁን በስራ ላይ ባለው የኢትዮጲያ ብሄራዊ ባንክ መመሪያ መሰረት የኢንሹራንስ ኩባንያዎች ማቋቋሚያ ካፒታል 65 ሚሊየን ብር መሆኑ ይታወቃል፡፡

አሐዱ ራድዮ
2.1K viewsedited  10:21
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2021-08-24 13:20:22 የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ንግድ ቢሮ ፥ "የዳቦ ዋጋን ተመን ለማውጣት የሚፈቅድ አሰራር የለንም" አለ።

ቢሮ ይህን ያለው ለአሀዱ ኤፍ ኤም 94.3 ሬድዮ ጣቢያ ነው።

የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ንግድ ቢሮ የህዝብ ግንኙነት ሀላፊ አቶ ዳንኤል ሚኤሳ በሰጡት ቃል ፥ በመዲናዋ በርካታ ነዋሪዎች የዳቦ ዋጋ በእጅጉ መጨመሩን እንዲሁም የዳቦው መጠንና ዋጋው እንደማይመጣጠን ተደጋጋሚ ቅሬታ ያቀርባሉ ብለዋል።

በመዲናዋ ያሉ ከ 2 ሺህ በላይ ዳቦ ቤቶች ካለፈው 1 አመት ወዲህ ከንግድ ቢሮው ጋር የነበራቸውን ትስስር ያቋረጡ በመሆኑ አሁን ላይ ቢሮው የዋጋ ተመንን ለማውጣት የሚፈቅድ አሰራር እንደሌለው ተናግረዋል፡፡

መንግስት የስንዴ ድጎማውን ማቋረጡን ተከትሎም በመዲናዋ ያሉ ከ 2ሺ በላይ ዳቦ ቤቶች ትስስራቸውን ማቋረጣቸውንም አስረድተዋል፡፡

አቶ ዳንኤል ፥ "ምንም እንኳን በርካታ የመዲናዋ ነዋሪዎች ቅሬታ ቢያቀርቡም አሁን ባለው የቢሮው አሰራር ዳቦ ቤቶቹ ባስቀመጡት የዳቦ ግራም እና ዋጋ በትክክል እየሸጡ መሆን አለመሆኑን ቁጥጥር ይደረጋል እንጂ ዋጋ በመተመን በገበያው ጣልቃ መግባት አይቻልም" ሲሉ ተናግረዋል፡፡

አክለው በተያዘው አመት ባስቀመጡት የዳቦ ግራም መጠን ዋጋ ሲሸጡ ያልተገኙ ወደ 24 የሚጠጉ ዳቦ ቤቶች ላይ እርምጃ መወሰዱን ገልጸዋል፡፡
አሀዱ ኤፍ ሬድዮ
1.5K views10:20
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2021-08-24 13:18:58 የተባበሩት መንግስታት ድርጅት በሱዳን አብዬ ግዛት በሰላም ማስከበር ላይ የሚገኙ የኢትዮጵያ ወታደሮችን በሌላ ለመተካት መስማማቱን የአገሩ ሹማምንት መናገራቸውን ሱዳን ትሪቡን ዘግቧል፡፡

ከኢትዮጵያ ጋር በድንበር ፍጥጫ ውስጥ የምትገኘው ሱዳን በአወዛጋቢው የአብዬ ግዛት ውስጥ በሠላም አስከባሪነት የተሰማራው የኢትዮጵያ ሠራዊት በሌላ አገር ጦር እንዲተካ ከሦስት ወራት በፊት በውጭ ጉዳይ ሚኒስትሯ በኩል መጠየቋ መነገሩ ይታወሳል፡፡

እንደ ሱዳን ትሪቡን ዘገባ ከሆነ የአገሪቱ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር መርየም አል መሕዲ በተባበሩት መንግስታት ድርጅት የምሥራቅ አፍሪካ ልዩ መልእክተኛ ከሆኑት ፐርፋይት ኦናንጋ አንያንጋ እና ሌሎች የሰላም አስከባሪው ሹምምንት ጋር ካደረጉት የበይነ መረብ ውይይት በኋላ የመንግስታቱ ድርጅት የኢትዮጵያ ወታደሮች የአብዬ ግዛትን ለቀው እንዲወጡ ከስምምነት ተደርሷል፡፡

የአብዬ ግዛትን ይለቃሉ የተባሉት የኢትዮጵያ ወታደሮች፣ ከሥፍራው እንዲወጡ ከስምምነት የተደረሰው በቀጣይ ሦስት ወራት ጊዜ ውስጥ መሆኑም ተጠቅሷል፡፡

የተባበሩት መንግሥታት መረጃ እንደሚያመለክተው ከ3 ሺሕ 300 በላይ የኢትዮጵያ ሠራዊት አባላት በድርጅቱ ዕዝ ስር በአብዬ ግዛት ውስጥ ተሰማርተው የሠላም ማስከበር ተግባር እያከናወኑ ይገኛሉ።
1.2K views10:18
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2021-08-24 13:17:59 በቦሌ ክፍለ ከተማ በሚገኝ አንድ ፔንሲዮን የተደበቁ 20 ክላሽን-ኮቭ ጠመንጃዎች በቁጥጥር ስር መዋላቸውን የአዲስ አበባ ፖሊስ ገለፀ፡፡

በወንጀሉ የተጠረጠሩ ሁለት ግለሰቦች ተይዘው ምርመራ እየተጣራባቸው እንደሚገኝም ፖሊስ አስታውቋል፡፡

ትናንት ምሽት በቦሌ ክፍለ ከተማ ወረዳ አራት ልዩ ቦታው ውሃ ልማት ተብሎ በሚጠራው አካባቢ በሚገኘው አምባሳደር ፔንሲዮን ውስጥ የመኝታ አገልግሎት ፈልገው አልጋ ለመከራየት የገቡ ሁለት ግለሰቦች በማዳበሪያ የተጠቀለለ ለጊዜው ምንነቱ ያልታወቀ ነገር ይዘው ስለመግባታቸው በክትትል ተደርሶባቸዋል፡፡

የብሄራዊ መረጃና ደህንነት አገልግሎት ጥብቅ ጥናትና ክትትል ሲያደርግ ከቆየ በኋላ ከአዲስ አበባ ፖሊስ ጋር በመቀናጀትና አስፈላጊውን ህጋዊ ሂደት በመከተል በፔንሲዮኑ ውስጥ ባደረገው ብርበራ በጨርቅ እና በማዳበሪያ የተጠቀለሉ አስር ባለሰደፍ እና አስር ታጣፊ ክላሽን-ኮቭ ጠብመንጃዎችን እንዲሁም 17 የክላሽንኮቭ ጥይት ካርታዎችን በመኝታ ክፍል ውስጥ ተደብቀው መገኘታቸውንና በቁጥጥር ስር ማዋሉን ፖሊስ ገልጿል፡፡

ከውስጥ እና ከውጪ ፀረ- ሰላም ሃይሎች ጋር ተጣምረው ሃገራችንን ለማፍረስ እየሰሩ የሚገኙት የሽብር ቡድኖች ተልዕኳቸውን ለማሳካት የተለያዩ መንገዶችን ሊጠቀሙ እንደሚችሉ ተጠቅሷል፡፡

በተጨማሪም አስፈላጊውን ቅድመ ጥንቃቄ ለማድረግ አልጋ የሚያከራዩ ሆቴሎች፣ ፔንሲዮኖች እና መሰል አገልግሎት የሚሰጡ የንግድ ተቋማት እንዲሁም የመኖሪያ ቤት የሚያከራዩ ግለሰቦች የተከራዮችን ማንነት በደንብ ማረጋገጥ እና አጠራጣሪ ነገሮች ሲያጋጥሙ ለፀጥታ አካላት ጥቆማ በመስጠት እንዲተባበር የአዲስ አበባ ፖሊስ አሳስቧል፡፡
1.1K views10:17
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2021-08-24 13:17:23 በትግራይ ክልል ጊዜያዊ አስተዳደር ሰራተኞ የታዘዙ ቼኮች እንዳይመነዘሩ የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ለቅርጫፎቹ በደብዳቤ ማሳወቁን ዋዜማ ራዲዮ ከደብዳቤው ቅጂ ተረድቻለሁ ብሎ ዘግቧል፡፡

ንግድ ባንክ ትእዛዙን ያስተላለፈው የፌዴራል መንግስት በተናጠል አውጄዋለሁ ያለውን የተኩስ አቁም ተከትሎ መቀመጫውን አዲስ አበባ ካደረገው የትግራይ ክልል ጊዜያዊ አስተዳደር ደረሰኝ ባለው ደብዳቤ ላይ ተመስርቶ እንደሆነ ገልጿል።

በህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት በ‹‹ሽብርተኛ›› ድርጅትነት የተፈረጀው ሕወሓት ከፌዴራል መንግስት ጋር የገጠመውን ጦርነት ተከትሎ በትግራይ ክልል ያሉ የባንክ ሂሳቦች እንደታገዱ ደብዳቤው አስታውሷል።

የፌዴራል መንግስት ጦር መቀሌን ጨምሮ መላው የትግራይ ክልል ለወራት ከተቆጣጠረ በኋላ ክልሉን ለቆ ሲወጣ ክልሉን ሲያስተዳድሩ የቆዩት የጊዜያዊ አስተዳደሩ አባላት ወደ አዲሰ አበባ እንደተሰደዱ ይታወሳል።

በትግራይ ያሉ የባንክ ሂሳቦች የታገዱ ቢሆንም በጊዜያዊ አስተዳደሩ ከክልሉ የተለያዩ የባንክ ሂሳቦች (ሙያተኞቹ B እና Z አካውንቶች ከሚሏቸው) ወጭ እንዲሆን ያዘዙት ቼክ ስላለ ይሄንንም ቼክ በተለያዩ መንገዶች ለመመንዘር ጥረት ሊደረግ ስለሚችል ሁሉም የንግድ ባንክ ቅርንጫፎች ጥንቃቄን እንዲያደርጉና ቼኩን እንዳይመነዝሩ ከንግድ ባንኩ ፕሬዝዳንት ትእዛዝ እንደተላለፈላቸው ደብዳቤው ገልጿል።

የታዘዙ ቼኮችን ለመመንዘር የሚደረጉ ጥረቶች ካሉ የንግድ ባንኩ ሰራተኞች ለሚመለከተው አካል የሚያሳውቁባቸው ስልክ ቁጥሮችም በደብዳቤው ተዘርዝረዋል። ሆኖም እግዱ የተላለፈበት ትክክለኛ ምክንያት በደብዳቤው ላይ አልተገለጸም።

መንግስት ባለፉት ቀናት የሕወሓት የገንዘብ ምንጭ ይሆናሉ ብሎ ባሰባቸው የገንዘብ እንቅስቃሴዎች ላይ ተከታታይ እርምጃን መውሰዱ የሚታወቅ ነው። ንግድ ባንኮች በማስያዣ ብድር መስጠት እንዲያቆሙ፣ በህገወጥ ሀዋላ ላይ መወሰድ የጀመረው አሰሳ፣ እንዲሁም የንብረት በተለይ የቤት ሽያጭ ላይ የተላለፉት እገዳዎች የዚሁ አካል መሆናቸው ይታወቃል።
963 views10:17
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2021-08-24 13:16:20 ኤርትራ በጦር መሪዋ ላይ አሜሪካ የጣለችውን ማዕቀብ ውድቅ አደረገች


ኤርትራ ከትግራይ ጦርነት ጋር በተገናኘ በጦር መሪዋ ጄነራል ፊሊጶስ ወልደዮሐንስ ላይ በአሜሪካ የጣለችውን ማዕቀብ መሠረተ ቢስ ነው ብላዋለች፡፡

ኤርትራ መሠረተ ቢስ ያለችውን የአሜሪካን የማዕቀብ እርምጃ በተመለከተ በውጭ ጉዳይ ሚኒስቴሯ በኩል መግለጫ አውጥታለች።

የአሜሪካ አስተዳደር በጦር ኃይሎች ጠቅላይ ኤታማዦር ሹም ጄነራል ፊሊጶስ ወልደዮሐንስ ላይ ተቀባይነት የሌላቸውን ክሶች ሰንዝሯል ያለው መግለጫው፣ የኤርትራ መንግስት የተቃጣበትን መሠረተ ቢስ ውንጀላ እና ክስ በደብዳቤም ሆነ በመንፈስ እንደማይቀበል አስታውቋል።

የአሜሪካ አስተዳደር እንዲህ ዐይነት መሠረተ ቢስ የውንጀላ ዘመቻዎችን በኤርትራ ላይ ሲያደርግ የመጀመሪያው እንዳልሆነም ለአገሪቱ የውጭ ጉዳይ መስሪያ ቤት ኃላፊ አንቶንዮ ብሊንክን የተሰጠውን መልስ አስታውሷል፡፡

ኤርትራ ምክንያታዊ ያልሆኑ ያለቻቸው ተደጋጋሚ ክሶችን በዝምታ ልታልፍ እንደማትችልም መግለጫው ይጠቁማል።

ሐሰተኛ ያለው ውንጀላ ሊጣራ የሚችል ነገር ካለው በገለልተኛ አካል እንዲጣራም ለአሜሪካ አስተዳደር ጥሪ አቅርቧል።

የተባበሩት መንግስታት ድርጅት የጸጥታው ምክር ቤት ተደጋጋሚ የዓለም አቀፍ ህግጋትና የሃገራትን የሉዓላዊነት ጥሰቶች በመግታት እና መፈትሔ በመፈለግ ረገድ ኃላፊነቱን እንዲወጣም አሳስቧል።

በትግራይ ጦርነት የሚመሩት ጦር የተለያዩ ሰብዓዊ ጥሰቶችንና ግድያዎችን ፈጽሟል ያለው የአሜሪካ ፌዴራል ግምጃ ቤት፣ ጄነራል ፊሊጶስ በአሜሪካ አላቸው ያለውን ሐብት እንዳያንቀሳቅሱ ማገዱን ማስታወቁ የሚታወስ ነው።
854 views10:16
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2021-08-24 13:15:13 ኢትዮጵያ በቀጣዩ ዓመት ለሶስት ጎረቤት አገራት 1 ነጥብ 6 ቢሊዮን ኪሎ ዋት ኤሌክትሪክ እንደምትሸጥ አስታወቀች።
የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ሀይል በድረገጹ ባወጣው መግለጫ ተቋሙ በሚቀጥለው ዓመት ከኃይል ኤክስፖርት ከ138 ሚሊዮን ዶላር በላይ ገቢ ለማግኘት አቅዷል።
በተቋሙ የማርኬቲንግና ቢዝነሰ ደቨሎፕመንት መምሪያ ሥራ አስኪያጅ አቶ ሚኒሊክ ጌታሁን እንዳሉት በተያዘው የበጀት ዓመት ለሱዳን፣ ለጅቡቲ እና ኬንያ ከ1 ነጥብ 63 ቢሊዮን ኪሎ ዋት ሠዓት በላይ የኤሌክትሪክ ኃይል በማቅረብ 138 ነጥብ 25 ሚሊዮን የአሜሪካን ዶላር ገቢ ለማግኘት ታቅዷል፡፡
ገቢውን ለመሰብሰብ ለሱዳን 1 ነጥብ 1 ቢሊዮን ኪሎ ዋት ሠዓት ኤሌክትሪክ በማቅረብ 55 ነጥብ 48 ሚሊዮን ዶላር እንዲሁም ለጅቡቲ 527 ነጥብ 4 ሚሊዮን ኪሎ ዋት ሠዓት ኤሌክትሪክ በማቅረብ 34 ነጥብ 1 ሚሊዮን ዶላር ለማግኘት መታሰቡንም ሥራ አስኪያጁ ተናግረዋል፡፡
እስካሁን የኢነርጂ ኤክስፖርት ወዳልተጀመረበት ኬኒያ ወደ 695 ኪሎ ዋት ሰዓት የኤሌክትሪክ ኃይል ለማቅረብና 48 ነጥብ 65 ሚሊዮን ዶላር ለማግኘት ዕቅድ መያዙንም ስራ አስኪያጁ ገልጸዋል፡፡
በኢትዮጵያ በኩል የኢትዮ- ኬንያ ከፍተኛ የኤሌክትሪክ ኃይል ማስተላለፊያ መስመር በመጠናቀቁና የኬንያም ተጠናቆ አገልግሎት መስጠት እንደሚጀምር ታሳቢ ተደርጎ ከጥር 2014 ዓ.ም ጀምሮ ለመጀመሪያ ጊዜ ወደ ኬንያ የኤሌክትሪክ ኃይል ኤክስፖርት ለማድረግ እቅድ ተይዟል ተብሏል፡፡
በተጠናቀቀው በጀት ዓመት ለኬንያ 695 ሚሊዮን ኪሎ ዋት ሰዓት የኤሌክትሪክ ኃይል በማቅረብ 48 ነጥብ 6 ሚሊዮን ዶላር ገቢ ለመሰብሰብ ታቅዶ የነበረ ቢሆንም በኬንያ በኩል እየተገነባ ያለው የኢትዮ- ኬንያ የማስተላለፊያ መስመር ፕሮጀክት ግንባታ ባለመጠናቀቁ ለኬንያ የኤሌክትሪክ ኃይል ማቅረብ እንዳልተቻለ መዘገባችን ይታወሳል፡፡
ኢትዮጵያ ከሦስቱ ሀገራት በተጨማሪ በቀጣይ ከሶማሌ ላንድ፣ ከታንዛኒያ እና ደቡብ ሱዳን እና ከሌሎች የአፍሪካ ሀገራት ጋር የኤሌክትሪክ ኃይል ትስስር ለመፍጠር የሁለትዮሽ ግንኙነት በማድረግ ላይ ትገኛለች፡፡
ኢትዮጵያ በቀጣዮቹ 10 ዓመታት 71 የኤሌክትሪክ ሀይል ማመንጫ ጣቢያዎችን ለመገንባት ማቀዷን መግለጿ የሚታወስ ነው።
777 views10:15
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2021-08-24 13:14:06 ምርጫ ባልተካሄደባቸው ምርጫ ክልሎች የፊታችን መስከረም 20 ድምፅ ይሰጣል ተባለ

ሰኔ 14 ምርጫ ባልተካሄደባቸው ምርጫ ክልሎች የፊታችን መስከረም 20 ድምፅ እንዲሰጥ መወሰኑን የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ አስታወቀ።
ቦርዱ ምርጫ ባልተደረገባቸው ምርጫ ክልሎች ከሚወዳደሩ ፖለቲካ ፓርቲዎች ጋር ውይይት በማድረግ ድምፅ መስጫ ቀኑ መወሰኑን አስታውቋል።
ሁሉም የቦርዱ አመራሮች በተገኙበት የምክክር መድረክ በቦርዱ ዋና ሰብሳቢ ብርቱካን ሚደቅሳ አማካኝነት ቦርዱ ሲሰራቸው የቆያቸው ስራዎች የተመለከተ ሪፓርት ለፓርቲዎች የቀረበ ሲሆን ቀጣዩን የምርጫ ሂደት ከአካባቢዎቹ አጠቃላይ ሰላምና ተጨባጭ ሁኔታ ጋር በማገናዘብ ዝርዝር መረጃ ተሰጥቶ ውይይት ተደርጓል።
በዚህም ምርጫው በመጪው መስከረም 20ቀን 2014 ዓ/ም እንዲካሄድ ስምምነት ላይ ተደርሷል።
ድምፅ አሰጣጡ በሶማሌ፣ በሐረሪ ክልል እና በደቡብ ብሔር ብሔረሰቦች እና ህዝቦች ክልል የሚከናወን ሲሆን የደቡብ ምእራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ህዝበ ውሳኔም በተመሳሳይ ቀን መስከረም 20 ቀን 2014 ዓ.ም እንደሚከናወን ቦርዱ አስታውቋል።

አል ዐይን
716 views10:14
ክፈት / አስተያየት ይስጡ