Get Mystery Box with random crypto!

የ እውቀት ማዕድ

የቴሌግራም ቻናል አርማ yewuketmaed — የ እውቀት ማዕድ
የቴሌግራም ቻናል አርማ yewuketmaed — የ እውቀት ማዕድ
የሰርጥ አድራሻ: @yewuketmaed
ምድቦች: ያልተመደበ
ቋንቋ: አማርኛ
ተመዝጋቢዎች: 2.20K
የሰርጥ መግለጫ

ቻነሉ የተለያዪ አዝናኝና አስተማሪ ፕሮግራሞችን እንዲሁም አዳዲስ መረጃወችን አለም አቀፍ ግኝቶችን በተለያዩ ዘርፍ እውቀት የምትቀስሙበትን አማራጭ ያቀርባል።
ማንኛውም አስተያየት እና ጥያቄ ካላችሁ @teppi10_Bot ላይ አስፍሩልኝ!
የመወያያ Group—https://t.me/yewuketmaed8

Ratings & Reviews

4.50

2 reviews

Reviews can be left only by registered users. All reviews are moderated by admins.

5 stars

1

4 stars

1

3 stars

0

2 stars

0

1 stars

0


የቅርብ ጊዜ መልዕክቶች 2

2022-03-22 22:02:10 በወጣትነት ሁሉም ነገር ትክክል ነው ከሚል መመሪያ
ውጣ ፤ ሁሉንም ካላየሁ አላምንም አትበል ። ሰምቶ ማመን ፣
ከተጎዱት መማር አስተዋይነት መሆኑን አትርሳ ። የሰማንያ
ዓመት ዕውቀትን ለመገብየት ግድ ሰማንያ ዓመት መኖር
የለብህም ። ሰማንያ ዓመት ከኖሩት በትሕትና መጠየቅ
ይገባሃል ።
:
ምክርን ብትሰማ በነጻ ትማራለህ ። ምክርን አልሰማ
ብትል ግን በዋጋ እንደምትማር እወቀው ። በዋጋ መማር ግን
አድካሚ ደግሞም የሚያስመርር ነው ። ብልህ ከሆንህ በሰው
ከደረሰው ትማራለህ ፣ ሞኝ ከሆንህ ግን በራስህ ሲደርስ
ትማራለህ ።
:
የታየህን አሳይ ፣ ያልታየህን አጥራው ። በደንብ
ያልተረዳኸውን አታስተምረው። ያልቀመስከውን ለሰው
አትጋብዝ ። የሰማኸውን ሁሉ አትመን ። ያየኸውን ሁሉ ስጡኝ
፣ የተናገርከውን ሁሉ ፈፅሙ አትበል ። የሰጠኽውን እርሳ
እንጂ አታውራ። ፍፃሜውን ሳታይ ምስጋና አታብዛ ። ቀኑ
ሳይመሽ ቀኑ ጥሩ ነው አትበል ።
:
ዓይንህ የፊቱን ቢያይ ልብህ የኋላውን ያስብ ። ነገ ላይ
እንድትደርስ የትናንቱን አትርሳ ። የምትሄድበት እናዳይጠፋህ
የመጣህበትን አትዘንጋ ።
:
የአባቶችህን መልካም ሥራ አብነት አድርግ ። ካሳለፉት
ሕይወት ተማር እንጂ አወዳሽና ወቃሽ አትሁን ። ሌሎች
መሆን ያለባቸውን ስታውቅ አንተ መሆን ያለብህ
እንዳይጠፋህ ተጠንቀቅ ። ደግሞም አንተም በታሪክ ፊት
መሆንህን እወቀው ።
:
ክፋት አይሙቅህ ፣ መልካም ነገርም ብርድ ብርድ
አይበልህ ። ለክፋት አቅም ካለህ ለበጎ ነገርም አቅም አለህና
ተግባርህ የምርጫ ውጤት ነውና አስብበት ።
:
ገንዘብ የሚመልሰው የገንዘብን ጥያቄ ብቻ ነውና ሁሉንም
ነገር ገንዘብ ያስገኝልኛል ብለህ አታስብ ። ላለው አትሩጥ ፣
ምጽዋትህና ተግባርህ በአቅምህ መጠን ይሁን እንጂ
ከአቅምህ አትነስ ። ድሃም ሆነህ ተበድረህ ስጦታ አትስጥ ።
በጣም ካልቸገረህ ለቅንጦት አትበደር ። ያንተን ድርሻ
ከጨረስህ ያልተጨረሰ የሌሎችን ድርሻ ፈፅምላቸው ።
:
ለሀብታም አትሳቅ ፣ የደሀ ጉልበት አይለፍብህ ፣ ያለ ሰው
ሰው አልሆንክምና ሰው አትጥላ ፣ የወጣህበትን መሰላል
አትገፍትር ፣ ለመውረድም ያስፈልግሃልና ፣ ያየኽውን ሴት
ሁሉ የመውደድ ጠባይህ ካለቀቀህ ትዳር አትያዝ ፣
ካልጋበዙህ በቀር አማካሪ አትሁን ፣ ባልጠሩህ ሥፍራ አቤት
አትበል ፣ ካልሾሙህ መሪ አትሁን ፣ ጉድለት በሌለበት ቦታ
ጊዜህን አታባክን ፣ የሰው ፊት ጥገኛ ሁነህ ሲስቁልህ
የምትስቅ ሲቆጡህ የምታለቅስ አትሁን ፣ ነገርህን በልክ ፣
ቃልህን በጣዕም ፣ ድምፅህን በዝግታ ፈፅመው ።
:
እውር እንዳይሉህ ያልታየኽን አያለሁ አትበል ። ጨካኝ
እንዳይሉህ ያልተሰማህን ጩኸት እሰማለሁ አትበል ። ንፉግ
እንዳይሉህ ያለ አቅምህ እረዳለሁ አትበል ። ነገር
አይገባውም እንዳይሉህ ያልገባህን እንደገባህ አድርገህ
አትለፍ ። አንድ በጎ ዕውቀት ሳትጨብጥ የዋልክበትን ቀን
እንደ ኖርክበት አትቁጠረው ፣ ስለዚህ መፅሐፍትን አንብብ ፣
አዋቂዎችን ጠይቅ ፣ ሁሉን ሳትንቅ ስማ ።
:
ሥልጣን ሲሰጥህ መሪ እንጂ አለቃ አትሁን ፤ ከፊት
እየቀደምህ አስከትል እንጂ ከኋላ ሆነህ አትቅደም ።
:
በዓላማ ኑር ፤ እንቅፋቶች የሚያጸኑህ እንጂ ተግባርህን
የሚያስተውህ አይሁኑ ። ሕይወት ትምህርት ቤት መሆኑና
ባለማወቅ ብዙ ትህምርቶች እንዳያመልጡህ ተጠንቀቅ ።
:
የመከራ ቀን ወዳጆችህን አትርሳ ፤ የዛሬ ሰው ብቻ አትሁን
፤ የትላንቱንም አስብ ፤ አንገት የተፈጠረው ዞሮ ለማየት ነውና

:
ዓለም ዋዣቂ ናት ። ከፍና ዝቅ ስትል አትደናገጥ ፤ ፀሐይ
ዝናብን ተከትላ ትፈነጥቃለች ። ከመከፋትም በኋላ ትልቅ
መፅናናት ይሆናል ። ከሌሊት በኋላም ሌሊት አይመጣም ።
ከሀዘን በኋላ ደስታ ይሆናልና በርታ!
:
መነቀፍን አትፍራ ፤ ነቀፋህን ግን አጥራው ፤ ስለ ሀሰት
ሳይሆን ስለ እውነት ተገፋ ፤ ሌሎችን ውደድ ፍቅር ስጦታ
እንጂ ብድር አይደለምና አልወደዱኝም ብለህ በአበዳሪዎች
አንቀጽ አትካሰስ ፤ የገባህን አድርግ የዚህ ዓለም ሰው
ሲወድህም ሲጠላህም ባለማወቅ ነው ። ብዙዎች
ስለወደዱህ ይወድሃል ፤ ብዙዎች ስለጠሉህ ይጠላሃል ።
:
ሁልጊዜ የበላዮችህን አትመልከት ፤ የበታቾችህንም
ተመልከት ። ለድምፅ አልባዎች ጩህላቸው ፣ ለተጠቁት
ተሟገትላቸው ። እውነት እውነት በማለትህ የምታጣው
ሀሰተኛ ወዳጅህን ብቻ ነው ። እውነት እውነት በማለትህ
የምታተርፈው ግን እውነተኛ ወዳጅን ነው ።
:
ደጋፊዎች ተከታዮች አይደሉም ። ሰዎች ስለደገፉህም
የያዝኩት እውነት ነው ብለህ መንቻካ አትሁን ፤ ምናልባት ዛሬ
የሚጮሁልህ ዛሬን ሊረሱብህ ሊሆን ይችላልና ።
ሲያለቅሱልህም ቃልህ ማርኳቸው ሳይሆን የሞተ ዘመዳቸው
ትዝ ብሏቸው ሊሆን ይችላልና አለቀሱ ብለህ ንግግርህን
ድንበር አታሳጣው ። እውነትንም በደጋፊ ብዛት እንዳትመዝናት
ተጠንቀቅ ።
:
ለእውነታ እንጂ ለይሉኝታ አትኑር ፤ ያን ስልህ የምትኖርበት
ሕዝብና ባሕል ከእውነት ጋር እስካልተጋጨ መጋፋት
የለብህም። ሠዎች የሚቀበሉህ ባሕላቸውን ስታውቅና
ስታከብርላቸው ነው ።
:
ልጅነት የለሰለሰ መሬት ፣ ወጣትነት የአዝመራ ዘመን ፣
ሽምግልና ደግሞ የአጨዳ ዘመን መሆኑን አስተውል ።
በሽምግልናህ የምታጭደው የወጣትነትህን አዝመራ ነውና
ዛሬ ለምትዘራው ተጠንቀቅ ።
:
የሰዎችን ያለማወቅ አግዝ ፤ ዕውቀትህ ባላወቁት ላይ
እንድትኮራና እንድትፈርድ አያድርግህ የአዋቂ ኩሩ ቁጥሩ
ካላዋቂዎች ነውና ማወቅ ባለዕዳነት እንዳይሆን አላዋቂዎችን
እርዳቸው !!

ሁሉን ወሬ ላውራ አትበል ፣ የደበቁህን ምስጢር
አታውጣጣ ፣ የሰማኽውን ወሬና የተገለጠልህን ምስጢር
ምን መፍትሔ ሰጠኸውና ? ያየህውን ሥራ ሁሉ እሰራለሁ
የሰማኸውን ትምህርት ሁሉ እማራለሁ አትበል ። ይህ
የተሰወረው የቅንዓት ጠባይ ነውና ሁሉን ልያዝ ማለትም ዝንጉ
አድረጎ እንዳያስቀርህ ሁሉም ውስጥ ልኑር አትበል ።

ቆንጆዎች ቁንጅናቸው ሁሉን የሚተካ እየመሰላቸው
ከዕውቀትና ከትሕትና ይርቃሉ ። ሁሉንም ሰው በመልካቸው
የሚማርኩት ስለሚመስላቸው ኩሩና ተንኮለኞች ይሆናሉ ።
አንተ ግን ቆንጆ ወዳጅን እንጂ ቆንጆ ቁመናን አትሻ ፤ ቆንጆ
ትዳርን እንጂ ቆንጆ ሴትን አትመኝ ፤ የላይ ነገር ከንቱና ኀላፊ
ነውና በሚፈርስ አካል ፣ ኑሮ በሚለውጠው መልክ አትደለል።

እወድሃለሁ ብለህ የምትናገረውን ቃል ውለታ አታድርገው
፣ መውደድህን የምትናገረው እንወድሃለን እንዲሉህ አይሁን ፣
ሠላም ያለው አፍቃሪ የራሱን ፍቅር ያለ ምክንያት መፈፀም
የሚችል ብቻ እንደሆነ እወቅ ። መወደድህን ለመስማት
አትጠብቅ ።

የሰዎችን ያለማወቅ አግዝ ፤ ዕውቀትህ ባላወቁት ላይ
እንድትኮራና እንድትፈርድ አያድርግህ የአዋቂ ኩሩ ቁጥሩ
ካላዋቂዎች ነውና ማወቅ ባለዕዳነት እንዳይሆን አላዋቂዎችን
እርዳቸው ።

ዛሬ የመዝራት ዘመንህ ነገ መከርህ ነውና በእምነት
እውነትን ዝራ ፤ በምታውቀው ቦታ ላይ አገልጋይ
በማታውቀው መልካም ተግባር ላይ ደጀን ሁን ፤ በቦታህ
መምህር ያለቦታህ ተማሪ ሁን ፤ ክብሩ እንዳይቀንስብህ ከዕቃ
ትምክህት ፣ ከዕውቀት ሙግት ራቅ ።

ይቀጥላል.....
1.3K viewsedited  19:02
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-03-22 18:17:56 ትዕግሥት የሌለው ሰው ለዓመታት የካበውን በአንዲት ደቂቃ ይንደዋል። ወዳጄ ጨለማ ላይ ስለተበሳጨህ አይነጋም ።የሚነጋው ሰዓቱን ጠብቆ ነው ። ደመናው ላይ ስለተበሳጨህም አይፈካም ፣ የሚፈካው በጊዜው ነው ። ቀዩ የትራፊክ መብራት አረንጓዴ የሚሆነው በተመደበለት ሰዓት እንጂ በአንተ ንዴት አይደለም።

ስለዚህ አንድ ነገር አስተውል ህይወት የሆነችውን ትሆናለች እንጂ አንተ የግድ ሁኚ ያልካትን አትሆንምና ትዕግሥትን ገንዘብህ አድርግ !

@yewuketmaed
1.2K views15:17
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-03-20 11:45:33 አንድ አይነ ስውር ሰውዬ አንድ ለየት ያለ ልምድ አለው፥ቀኑ ሲጨላልም ከቤት ይወጣና ወክ እያረገ ንፁ አየር ወስዶ ይመለሳል ታድያ ሁል ጊዜ ከእጁ ፍኖስ አይለየውም ነበረ በአንድ ምሽት ሶስት ወጣቶች ሲያልፉ አይነ ስውሩን ሰውዬ ከነፍኖሱ ያገኙታል ከዛም በማሾፍ እንዲህ አሉ "አንተ አይነስውር ሰው ነህ ልክ እንደሚያይ ሰው ፍኖስ ይዘህ መዞር በጣም ይገርማል" ብለው ተሳለቁበት ሰውዬውም በርጋት እንዲህ አላቸው"

ልክ ናችሁ እኔ አላይም ነገር ግን ፍኖሱ ይጠቅመኛል ምክኒያቱም ሰወች እኔን በጨለማ ውስጥ ሳያዩኝ ከገፈተሩኝ ቡሀላ ከምናደድባቸው ፍኖሱን ይዤ ባበራላቸው ለሁለታችንም ይጠቅማል"አለ ....
ወጣቶቹም በሰውዬው ቅን አስተሳሰብ ተደነቁ ሳያስተውሉ በመናገራቸው ግን በሀፍረት አንገታቸውን ደፉ!!።።

ሁል ጊዜም ፍርድ ከመስጠታችን በፊት ራሳችንን በሌላ ሰው ጫማ ውስጥ ከተንም ቢሆን ለማሰብ እንሞክር ክፉ ተናግረን የሰውን ስሜት ከመጉዳታችን በፊት ጥቂት እናስብ ።

@yewuketmaed
1.4K viewsedited  08:45
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-03-13 23:58:30 አንድ አንዴ አጋጥመውህ ያውቃሉ?፣ የሆኑ ድንጋይ የሆኑ ሰዎች፣ ልክ እንደገደል ማሚቱ የእራሳቸውን ነገር ብቻ ማስተጋባት የሚፈልጉ የሆኑ?፣ ልክ እንደ ባዶ ቅል ዝም ብለው የሚጮኹ፣ ያልተባሉትን የሚሉ፣ በቀኝ ሲባሉ በግራ በግራ ሲባሉ በቀኝ የሚሉ፣ ወደ ታች ሲባሉ ወደ ላይ፣ ወደ ላይ ሲባሉ ወደ ታች የሚሄዱ፣ በስተሰሜን ሲባሉ በስተደቡብ የሚሉ ቀኝ ግራ፣ ግራ ቀኝ የገባቸው፤ ህይወትን አሳመርን እያሉ የሌላውንም የሚያጠለሹ፣ ነገሮችን አጠራን እያሉ የባሰ የሚያደፈርሱ፣ ሰዎችን ከአደጋ ጠበቅን ብለው የሚገድሉ፣ አስብኩልህ፣ አዘንኩልህ፣ ተጨነኩልህ ብለው ህይዎትህን ለማመሰቃቀል የሚጥሩ ነጭና ጥቁር መለየት ያቃታቸው፣ ጥሩውን ከመጥፎ ማወቅ የከበዳቸው፤ ልትረዳቸው ብትሞክርም ያን መርዛማ ማንነታቸውን በአንተ ላይ የሚተፉ መልካም መሳይ ክፉ ሰዎች፣ አሳቢ መሳይ አውደይዳይ፣ አዛኝ መሳይ መሰሪ፣ ወዳጅ መሳይ ጠላት፣ ጠቃሚ መሳይ ጎጂ፣ ህይወትን መረዳት ያቃታቸው፣ የፈጣሪን መኖር የዘነጉ፤ህይወት፣ ልቦና ተገለባባጭ መሆኑን የዘነጉ ሰዎች፣ በመልካምነትህ፣ በአዛኝነትህ፣ በአሳቢነትህ፣ በአፍቃሪነትህ የጎዱህ፣ ያስከፉህ፣ የተጫወቱብህ... እንደነዚህ አይነት ሰዎች ወደ ህይወትህ መጥተው ከነበር?... መሄድ ሲፈልጉ በእልልታ ሸኛቸው እና ተዋቸው ምንም አያረጉልህም፣ ከአንተም ላይ አንድም ነገር አያጎሉብህም። አንድ ነገር ልበልህ ሁሉን ተመልካች ጌታ ውሳኔውን ለእሱ ተወው ያኔ የልብህ ይሞላልሃል፤ እመነኝ ያኔ ማየት ምትፈልገውን ታየዋለህ።
:
@yewuketmaed
1.6K views20:58
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-03-09 20:21:46 2+2=3፣ 2+2=4 እና 2+2=5…6…


ይህ ስሌት ትክክለኛውን የሂሳብ ቀመር የተጻረረ መሆኑ እውን ነው፡፡ ነገር ግን ‘mathematics for accounting’ የተሰኘው የትምህርት ዘርፍ ይቀበለዋል፡፡ በዚህ ስሌትም አንድ ድርጅት አትርፏል ወይስ ከስሯል? የሚለውን ለማወቅ ይጠቀምበታል፡፡

ይህም ማለት፡-
አንድ ድርጅት ወጪና ገቢውን በሚያሰራበት ሰዓት 2+2=3 ካመጣ ስራ ላይ ካዋለው አንድ ብር በማጉደል እንደከሰረ ያመለክታል፡፡
ሁለተኛው 2+2=4 ከሆነ ትርፍም ሆነ ኪሳራ አላጋጠመውም፡፡ አራት ብር ስራ ላይ አዋለ በስተመጨረሻም አራት ብር አገኘ፡፡

የመጨረሻውና ሦስተኛው 2+2=5… ከሆነ ስራ ላይ ካዋለው ገንዘብ አንድ ብርና ከዚያ በላይ አትርፏል እንደ ማለት ነው፡፡
ይህንን ቀመር ወደ ህይወታችን መልሰን ነገሩን እናጢነው፡-


2+2=3

ምናልባት አንተ ይህንን የህይወት ዑደት አድርገህ ትጠቀመው ይሆናል፡፡ ስትፈጠር ትልቅ ነበርክ፣ በወንጀል ያልተጨማለክ፣ ከፍ ስትል ህልም ያለህ፣ ትልቅን ቦታ የተመኘህ… ከቆይታዎች በኋላ ግን ህልምህን የዘነጋህ፣ ከወንጀል ለመራቅ የማትጥር፣ ወደኋላ እየተጓዝክ መሆኑን የተረዳህ ልትሆን ትችላለህ፡፡

ያንተ ኪሳራ ወደ ኋላ መጓዝህን ማወቅህ አይደለም፡፡ እየተጓዝክ ያለህበት መስመር እንደማያዋጣ እያወክ በዛው ላይ መጽናትህ እንጂ፡፡ አንድ ድርጅት እየከሰረ መሆኑን የተረዳ ጊዜ እንዴት ብሎ ከኪሳራ መዳን እንዳለበት አቅጣጫን አስቅምጦ፣ አቅሙን አሟጦ እንደሚሰራ ልብ በል፡፡

አንተም ያለህበትን ቦታ እወቅ፣ የት መገኘት እንደነበረብህ አስተውል፡፡ ወደ ትክክለኛው መስመር እንዴት መምጣት እንዳለብህ አሰላስል፤ እውነተኛውን መንገድ ምረጥና ወደ እሱ ቅረብ፤ በሁለቱም አለም ትርፋማ ሁን፤ ከኪሳርም ዳን፡፡

2+2=4

የብዙዎቻችን ችግር ነው ማለት ይቻላል፡፡ መተኛት፣ መነሳት፣ መብላት፣ መጠጣት… ሁሌም ተመመሳይ ኑሮን መኖር፡፡ የተሻለን ነገር አለማሰብ፣ አዲስ ነገር ከመሞከር መራቅ፣ ያልለመድከውን ነገር አለመሞከር፣ ከመልካም ስራ መዘናጋት፡፡ ዛሬም ነገም ከነገ ወዲያም ምንም ለውጥ አለማሳየት፡፡ ኪሳራም ትርፍም አለማስመዝገብ ነው፡፡

አንድ ድርጅት ኪሳራም ሆነ ትርፍ ካልገጠመው አዲስ ሃሳብ በማምጣት አዲስ አሰራርን ይጀምራል፡፡ አሁንም እራስህን ልትፈትሽ ግድ ይላል፡፡ አንተ አቅሙ አለህና ከዛሬው የበለጠ ልታተርፍ ይገባል፡፡ አሁን ካለህበት የተሻልክ መሆን ትችላለህ፡፡ ተነስና ስንቅህን አዘጋጅተህ ጉዞህን ጀመር፡፡ ዛሬህ ከነገህ የተሸለ እንዲሆን ጣር፡፡

2+2=5…

ስታተርፍ ደስ ይልሃል፡፡ ከፈጣሪ ጋር ያለህንም ግንኙነት ስታጠብቅ ደስስስስስስስስ ትሰኛለህ፡፡ ህይወትህን በትርፋማ መንገድ ላይ የምትመራ ከሆነ ባለህበት ላይ ጽና፤ ትርፍ በትርፍ ለማድረግ ጣር፡፡

በስተመጨረሻም

ዛሬ ምን አተረፍኩ? ከሶስቱ የትኛውን ነው የምትከተል? ጊዜዬን ብዙ ነገሬን ሰውቼ ሳበቃ ወደ ኪሳራ ነው የማመራው ወይስ… ? እያልክ እራስህን በመጠየቅ ያለህበትን ደረጃ አጣራ፡፡
.
@yewuketmaed
1.7K views17:21
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-03-07 19:27:20 *
*
ፈንድሻ እንዴት ነጣች አማረች ቢሉ፤ እሳት የሚባል ፈተናን ተቋቁሟ ችላ ይላሉ!
#ወዳጄ ህይወት ከዚህ የተለየ ነገር የላትም፤ ጥሬ ከነበርክ ታበስልሃለች፣ በስለህ ከነበረም ትፈትንሃለች፤ ሁሉንም የህይወት መስክ ታስጎበኝሃለች፣ በፈተና እሳት ታቃጥልሃለች፣ በጨለማ ፍም ታንተከትክሃለች፣ ተስፋ በሚያስቆርጥ ቃንቄ ታግልሃለች... ይህን ሁሉ የምታልፈው ግን ዛሬን በመታገስ ነገር ተስፋ በማድረግ ነው። ሁለቱ ባንተ ህይወት ውስጥ ካሉ ሁሉን ታልፈዋለህ፤ የድል፣ የስኬት ማማ ላይ ትደርሳለህ።

@yewuketmaed
1.5K views16:27
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-03-07 12:17:07 በሩስያና በዩክሬን ጉዳይ አስመልክቶ ባልና ሚስት አልጋቸው ላይ ምን አወጉ? ጆን ጊያን የተባለ በፌስቡክ ይሄን ፅፏል;

ከመተኛቴ በፊት ባለቤቴ እንዲህ አለችኝ; "ይህች ሩሲያ በጣም መጥፎ አገር ናት።ዩክሬናውያን ኔቶን ለመቀላቀል ከፈለጉ መብታቸውና እና ነፃነታቸው ነው። ሩሲያ ጣልቃ የመግባት መብት የላትም.። ኔቶ ሩሲያ ዩክሬንን ለመውረር የተጠቀመችበት ሰበብ ነው። " አለችኝ

ለባለቤቴ መልስ አልመለስኩም ። ወደ ኩሽና ሄድኩና ቢላዋ ይዤ ወደ አልጋው አጠገብ ሄድኩ።ከዚያም "እንተኛ "አልኩኝ። ሚስቴ በከፊል በተሸፈኑ አይኖቿ ተመለከተችኝ ።
"ቢላ ይዘህ እንዴት ትተኛለህ ?" አለችኝ ። "አትጨነቂ።እንተኛ። ቢላ ይዞ መተኛት የኔ ጉዳይ ነው። መብቴም ነው ።ነፃነቴንም አትጋፈፊ " አልኳት ።
ሚስቴም " አንተ ቢላ ይዘህ ስትተኛ እንዴት ልተኛ እችላለሁ? በድንገት ብትቆርጠኝስ ወይስ ወግተህ ብትገለኝስ ? " አለችኝ።

" አየሽ አንቺ የራስሽን ባል እንኳን አታምኒውም። ሩሲያ ዩክሬንን እንድታምን እንዴት ትጠብቃያለሽ? " ዩክሬን ኔቶን አባል ሆና አሜሪካን ጨምሮ ሌላችም አባላት ከባድ መሳሪያ ወደ ዩክሬን ቢያስገቡ ሩስያ እንዴት በሰለም እንቅልፍ ትተኛለች? "አልኳት ።

@yewuketmaed
1.5K views09:17
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-02-25 10:18:32 አባት ወደ ቢሮው ሊሄድ ቦርሳውን እያዘገጃጀ እያለ ልጁ መጣና...
" አባየ መስሪያ ቤትህ ልትሄድ ነው ?"
"አዎ"
" አባየ ቢሮህ በሰዓት ስንት ነው የሚከፍልህ ?"
" ይህ የአንተ ጉዳይ አይደለም... አይመለከትህም" " አባየ ንገረኝ ፈልጌው ነው ? " አይን አይኑን እያየ
" ውይ ምን ያደርግልሃል ... እሺ 100 ብር ነው " ብሎት ሊሄድ ሲል
" አባየ 50 ብር አበድረኝ "
" አንተ ልጅ ላቤን ጠብ አድርጌ የማመጣው ላንተ ኮልኮሌ መግዣ መሰለህ ? ዞር በል ወደዛ አሁን ልሂድበት " ሲለው ልጁ እያለቀሰ ወደ መኝታ ቤቱ ገብቶ ጋደም አለ ፡፡ አባት የልጁ ማልቀስ ስላሳዘነው ወደ ልጁ መኝታ ክፍል ሄደ
" ልጀ ተኛህ እንዴ ? " " አልተኛሁም " አለው እምባውን ከአይኑ ላይ አየጠረገ "50 ብርህን እንካ " ልጁ እየሳቀ ተቀበለው
" ደስ አለህ አይደል ? ሰዓት ስለደረሰ ልሂድ "
" ቆይ አባየ እንዳትሄድ" ከአልጋው ስር የሰበሰበውን ሳንቲም እና ብሮች አወጣና ለአባቱ አሳየዉ
" አባየ ይኸ አጎቶቼ እኛ ቤት ሲመጡ የሚሰጡኝን የሰበሰብኩት ብር ነው አንተ ከሰጠኸኝ ብር ጋር ሲደመር መቶ ብር ይሆናል ይኸን ብር እንካ #ለአንድ_ሰዓት ከኔ ጋር አብረኸኝ እንድትሆን እፈልጋለሁ አለው አባቱም በጣም አዘነ ማልቀስም ጀመረ ልጆች የወላጅን ጊዜ ከምንም በላይ ይፈልጋሉ ከነሱ ጋር ማሳለፍ አለብን።

ለልጆቻችን #ብር ሳይሆን #ግዜ እንስጣቸው፡፡

@yewuketmaed
2.2K views07:18
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-02-24 15:30:01 የዩክሬኑ ፕሬዚዳንት ዘለንስኪ ከደቂቃዎች በፊት ዩክሬንን ለቀው አምልጠዋል።
1.5K views12:30
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-02-24 15:22:25
ፑቲን

እንግሊዝን በዘኝ አፉ አንድ ጊዜ የሚተፋት
የሩሲያ ኒኩሊየር ቦንቦ ኢላማ የሚሆኑ ቦታዎችን ለይቶ አፉን አዙሮ ቆሟል።

ሶቬት ቃል የሚለው የሩሲያ የሀየር ሀይል ኦፕሬሽን (አንድ) በሚል ዘመቻ
የዩክሬንን ዋና ከተማ ከረቭን ሙሉ በመሉ በጭስ አፍኖ በመሀል እሳት እያሳየ መቆጣጠር ጀምሯል።

ቤላሩስ ለይ የነበረው የሩሲያና የቤላሩስ ታንከኛ እሳት እየተፋ ወደ ዩክሬን መግባት ጀምሯል።

የዩክሬን ኢንተርናሽናል አውሮፕላን ማረፊያ ነዷል።

ከ50,000 በላይ ዩክሬናውያን እግራቸው ወደ መራቸው መሰደድ ጀምረዋል።

ወደ እንግሊዝ ዘጠኝ ዋና ዋና የጦር ማእከላት የተጠመዱ የሩሲያ የኒውክለር ቦምብ ማስወንጨፊያዎች ተዘጋጅተው በተጠንቀቅ ቆመዋል። በነገራችን ከምዕራባውያን አገሮች፣ ትል

በጣም የሚገርመው ግን አሜሪካ አለኝ ብላ የምትኮራበት ራዳር ፑቲን በአንድ ደቂቃ ከጥቅም ውጭ አድርጎ የዩክሬንን ዋና ከተማ ባዶ እጇን ማስቀረቱ ነው። ይሄም ብቻ አይደለም ዩክሬንን ከምዕራባውያን የመጣላት መሳሪያ ሁሉ በ22 ደቂቃ ኦፕሬሽን ወደ አመድነት መቀየሩ ነው።

ሱሌማን አብደላ

@yewuketmaed
1.5K viewsedited  12:22
ክፈት / አስተያየት ይስጡ