Get Mystery Box with random crypto!

☞ለአስተዋዮች ብቻ! ――――――――――― ⇨አንዲት እጅግ በጣም ቆንጆ ሴት ሐጅና ዑምራ ለማረግ ወደ | 🌹የሱና እህቶች የለውጥ ሚና🌹

☞ለአስተዋዮች ብቻ!
―――――――――――
⇨አንዲት እጅግ በጣም ቆንጆ ሴት ሐጅና ዑምራ ለማረግ ወደ መካ አቀናች። ጀምረተ'ል ዐቀባ አካባቢ ሆና ጠጠሮችን ስትወረውር ገጣሚው ዑመር ኢብን አቢ ረቢዐ ተመለከታት። ይህ ሰው ፍቅር አዘል በሆኑ ግጥሞቹ ሴቶችን የሚያስቸግርና የሚያባብል በሴት ፍቅር የተለከፈ ዋልጌ ነበረ። ጠጋ ብሎ አናገራት መልስ አልሰጠችውም። በሁለተኛው ቀንም አናገራት። እሷም "ዞር በልልኝ! የተከበረው የአላህ ቤት ውስጥ እንዲሁም በተከበረ ቀን ውስጥ ነው ያለሁት! " ብላ ኮስተር አለችበት። ችክ ብሎ ይለማመጣትና ይገጣጥምላት ጀመረ። እሷም የጉዳዩን ሁኔታ መጋለጥ ሰግታ መወርወሯን ትታ ወደ ድንኳኗ ተመለሰች። በሶስተኛው ለሊት ወንድሟን "አብረን እንሂድና የሐጅ መናሲኮችን አሳየኝ" አለችው። ያ ገጣሚና ሴቶችን ለካፊ የሆነው ሰው ወንድሟን አብሯት ያየ ግዜ ከቦታው ሳይንቀሳቀስ እዛው ባለበት ተቀመጠ። ወደሷም አልተጠጋም። ይህን ስትመለከት ፈገግ ብላ ይህን ታዋቂ ግጥም ገጠመች።

*تعدو الكلاب على من لا أسود له*
*وتتقي صولة المستأسد الضاري*

☞የግጥሙ ግርድፍ ትርጉም

አንበሳ በሌለው ውሾች ይዘላሉ
ተናካሽ አንበሳን ጉዳት ግን ይሰጋሉ

☞ይህን ንግግሯን አቡ ጀዕፈር አል መንሱር የሰማ ግዜ "የቁርይሽ ወጣት ሴቶች ሁሉ ይህን ክስተት ሳይሰሙ እንዳይቀሩ ብዬ ወደድኩ" አለ።

☞በሆነ ከተማ ላይ አስተዋይና ሷሊሕ የሆነች እናት ነበረች። ሴት ልጇ ከቤት ስትወጣ ለወንድሟ "ተከተላት! ከእህትህ ጋር ሂድ። ሴት ልጅ መንገድ የሚያሰፋላትና የሚጠብቃት ወንድ ልጅ ከሌለ ልክ በተኩላዎች መሀል እንዳለች በግ ነች። ደካማው ተኩላም ይዳፈራታል!" ትለዋለች።

☞ገጣሚውም ይህን አለ!

قال الشاعر:
*إنّ الرجال الناظرين إلى النساء*
*مثلُ الكلاب تطوفُ باللحمانِ*
*إن لم تصن تلك اللحوم أسودُها*
*أُكِلت بلا عِوضٍ ولا أثمانِ*

≈≈የግጥሙ ግርድፍ ትርጉም⇓

ሴቶች ላይ አፍጣጭ ወንዶች
ምሳሌያቸው በክትን ዟሪ ውሾች
ስጋዋን አንበሳዋ ካልጠበቀች
ያለ ልዋጭና ክፍያ ተበላች!

[ዑዩኑል አኽባር ሊብን ቁተይባህ 4/107)]

☞እኔም ይህን አልኩኝ⇩

በተከበረው ቤት- ካልጠፋ ለካፊ
በየመንደሩማـ ሞልቷል አነፍናፊ
ኒቃብ ተሰናብቶ ـ ተነስንሰው ሽቶ
ቀሚስ አጭር ሆኖـ ጅልባቡ ተረስቶ
ከቤትህ ሲወጡـ ሸይጣን አጅቦልህ
ቅናት ሳይሰማህ ـካየህ ዝም ብለህ
የሰው ውሻ ሲሆንـ የሴትህ አጃቢ
መሞት ይሻልሀልـ አፈር ተቀላቢ


https://t.me/abdurezaq27