Get Mystery Box with random crypto!

🌹የሱና እህቶች የለውጥ ሚና🌹

የቴሌግራም ቻናል አርማ yeswnaehitochmena — 🌹የሱና እህቶች የለውጥ ሚና🌹 የ
የቴሌግራም ቻናል አርማ yeswnaehitochmena — 🌹የሱና እህቶች የለውጥ ሚና🌹
የሰርጥ አድራሻ: @yeswnaehitochmena
ምድቦች: ያልተመደበ
ቋንቋ: አማርኛ
ተመዝጋቢዎች: 2.34K
የሰርጥ መግለጫ

♡..አንቺ ሙስሊም እህቴ ሆይ! ከመገላለጥ ተጠንቀቂ {{በአላህ ፍቃድ}} ከፈተናዎች ጠባቂሽ የሆነውን ሂጃብሽን አጥብቀሽ ያዢ!❥...
🍃═══ ¤❁✿❁¤ ═══🍃

Ratings & Reviews

3.00

3 reviews

Reviews can be left only by registered users. All reviews are moderated by admins.

5 stars

0

4 stars

1

3 stars

1

2 stars

1

1 stars

0


የቅርብ ጊዜ መልዕክቶች

2022-07-20 04:56:05 አስገራሚ መልስ!

አንድ ሴኩላሪስት የሆነ ግለሰብ እንዲህ አለ "ሴት ልጅ ውበቷን ለመጠበቅ ስትል ልጅ መውለድ አልፈልግም ማለት መብቷ ነው።"

ይህን ንግግር እየሰሙ ካሉ ሰዎች መካከል አንደኛው እንዲህ አለው "ምነው እናትህ ውበቷን ለመጠበቅ ስትል ባልወለደችህ ኖሮ!"

https://t.me/abdurezaq27
759 views01:56
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-05-15 08:07:24 ☞ለአስተዋዮች ብቻ!
―――――――――――
⇨አንዲት እጅግ በጣም ቆንጆ ሴት ሐጅና ዑምራ ለማረግ ወደ መካ አቀናች። ጀምረተ'ል ዐቀባ አካባቢ ሆና ጠጠሮችን ስትወረውር ገጣሚው ዑመር ኢብን አቢ ረቢዐ ተመለከታት። ይህ ሰው ፍቅር አዘል በሆኑ ግጥሞቹ ሴቶችን የሚያስቸግርና የሚያባብል በሴት ፍቅር የተለከፈ ዋልጌ ነበረ። ጠጋ ብሎ አናገራት መልስ አልሰጠችውም። በሁለተኛው ቀንም አናገራት። እሷም "ዞር በልልኝ! የተከበረው የአላህ ቤት ውስጥ እንዲሁም በተከበረ ቀን ውስጥ ነው ያለሁት! " ብላ ኮስተር አለችበት። ችክ ብሎ ይለማመጣትና ይገጣጥምላት ጀመረ። እሷም የጉዳዩን ሁኔታ መጋለጥ ሰግታ መወርወሯን ትታ ወደ ድንኳኗ ተመለሰች። በሶስተኛው ለሊት ወንድሟን "አብረን እንሂድና የሐጅ መናሲኮችን አሳየኝ" አለችው። ያ ገጣሚና ሴቶችን ለካፊ የሆነው ሰው ወንድሟን አብሯት ያየ ግዜ ከቦታው ሳይንቀሳቀስ እዛው ባለበት ተቀመጠ። ወደሷም አልተጠጋም። ይህን ስትመለከት ፈገግ ብላ ይህን ታዋቂ ግጥም ገጠመች።

*تعدو الكلاب على من لا أسود له*
*وتتقي صولة المستأسد الضاري*

☞የግጥሙ ግርድፍ ትርጉም

አንበሳ በሌለው ውሾች ይዘላሉ
ተናካሽ አንበሳን ጉዳት ግን ይሰጋሉ

☞ይህን ንግግሯን አቡ ጀዕፈር አል መንሱር የሰማ ግዜ "የቁርይሽ ወጣት ሴቶች ሁሉ ይህን ክስተት ሳይሰሙ እንዳይቀሩ ብዬ ወደድኩ" አለ።

☞በሆነ ከተማ ላይ አስተዋይና ሷሊሕ የሆነች እናት ነበረች። ሴት ልጇ ከቤት ስትወጣ ለወንድሟ "ተከተላት! ከእህትህ ጋር ሂድ። ሴት ልጅ መንገድ የሚያሰፋላትና የሚጠብቃት ወንድ ልጅ ከሌለ ልክ በተኩላዎች መሀል እንዳለች በግ ነች። ደካማው ተኩላም ይዳፈራታል!" ትለዋለች።

☞ገጣሚውም ይህን አለ!

قال الشاعر:
*إنّ الرجال الناظرين إلى النساء*
*مثلُ الكلاب تطوفُ باللحمانِ*
*إن لم تصن تلك اللحوم أسودُها*
*أُكِلت بلا عِوضٍ ولا أثمانِ*

≈≈የግጥሙ ግርድፍ ትርጉም⇓

ሴቶች ላይ አፍጣጭ ወንዶች
ምሳሌያቸው በክትን ዟሪ ውሾች
ስጋዋን አንበሳዋ ካልጠበቀች
ያለ ልዋጭና ክፍያ ተበላች!

[ዑዩኑል አኽባር ሊብን ቁተይባህ 4/107)]

☞እኔም ይህን አልኩኝ⇩

በተከበረው ቤት- ካልጠፋ ለካፊ
በየመንደሩማـ ሞልቷል አነፍናፊ
ኒቃብ ተሰናብቶ ـ ተነስንሰው ሽቶ
ቀሚስ አጭር ሆኖـ ጅልባቡ ተረስቶ
ከቤትህ ሲወጡـ ሸይጣን አጅቦልህ
ቅናት ሳይሰማህ ـካየህ ዝም ብለህ
የሰው ውሻ ሲሆንـ የሴትህ አጃቢ
መሞት ይሻልሀልـ አፈር ተቀላቢ


https://t.me/abdurezaq27
1.5K views05:07
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-04-17 17:07:08 بسم الله الرحمن الرحيم

አሰላሙአለይኩም ወራህመቱላሂ ወበረካቱ ውድ አህቶች ላለፉት ጊዜያቶቾ ሲሰጡ የነበሩት(የሴቶች ብቻ) የኡሰታዝ ጣሀ አህመድ(ሐፊዘሁሏህ) ደርሦች ከዙም ወደ የኡስታዝ የቴሌግራም ቻናል መዘዋወራቸውን እየገለፅን ለዛሬ የሚኖረን፥

የረመዳን ሙሐደራ በቀጥታ

ለሴቶች ብቻ

ዛሬ እሑድ 17 April 2022

ሰዓት 2:30PM UK Time
4:30 Saudi
10:30 Ethio Time

በኡስታዝ ጣሀ አህመድ (ሐፊዘሁሏህ)

https://t.me/tahaahmed9


‎
1.5K views14:07
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-04-03 06:17:07 የፆም አላማ ረሃብና ጥማትን እንዲሁም ጭንቅና መከራን መቋቋም መቻልን አካልን ማለማመድ አይደለም። ነገር ግን ለነፍሳችን ተወዳጅ የሆኑ ነገሮችን ይበልጥ ተወዳጅ ለሆነው ውዴታ ስንል መተውን ነፍሳችንን ማለማመድ ነው። የምንተዋቸው ተወዳጅ ነገሮች ምግብ፣ መጠጥና ወሲብ ሲሆኑ እነዚህን በመተው የሚፈለገው ውዴታ ደግሞ ልዕልናው ከፍ ያለው የአምላካችን አሏህ ውዴታ ነው።


(48سؤالا في الصيام ص10) ‎#ابن_عثيمين
‎#رمضان

https://t.me/abdurezaq27
1.4K views03:17
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-04-02 19:30:45 ከፆመኞች ሁሉ በላጩ ማን ነው?

ኢብኑ-ል ቀይዪም ይህን ይላሉ ፦

"ከዒባዳ ባልተቤቶች ሁሉ የተሻለ የሚባለው በዒዳው ውስጥ እጅግ አላህን ማውሳትን (ዚክርን) የሚያባዛ የሆነ ሰው ነው። ልክ እንደዚሁ ከፆመኞች ሁሉ በላጭ የሚባለው ግለሰብ በፆሙ ውስጥ አላህን ማውሳትን (ዚክርን) በማብዛት የተሻለ የሆነው ሰው ነው።"

الوابل الصيب 152
https://t.me/abdurezaq27
1.3K views16:30
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-03-15 18:05:39 እናቴን ወይስ ሚስቴን?

☞ጥያቄ ፡ እናቴ ብቻዋን በጭርታ ውስጥ ነው የምትኖረው። በጣም እሰጋላታለሁ። ዘወትር አብራኝ ለመኖር፣ ጭርታዋን ለማስወገድና እንድንከባከባት አምርራ ትጠይቀኛለች። ሚስቴ ደግሞ ከእናቴ ጋር አብሮ መኖርን በፍፁም አትፈልግም። ይህን የእናቴን ሀሳብ በፅኑ ትቃወማለች። ሚስቴን ልታዘዝ ወይስ እናቴን?

☞መልስ ከሸይኽ ፈውዛን ፦ "ይህቺ ሚስትህ ከእናትህ ጋር የማትስማማ ከሆነ ለብቻዋ አኑራት። አንተ ከእናትህ ጋር ኑር። አልያም እናትህን እንድትንከባከብ የምትረዳህን ሌላ ሚስት ፈልግ። አለበለዚያ ሚስትህን ታዘህ እናትህን ችላ የምትልና ብቻዋን የምትተዋት ከሆነ ይህ ተግባር ወላጅን ከመበደል ውስጥ የሚመደብ ታላቅ ወንጀል ነው።"

المصدر / مجموعة رسائل دعوية ومنهجية ٢ / محاضرة الربا .ط. الامام احمد .ص١٨٩.ج
https://t.me/abdurezaq27
1.5K views15:05
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-03-14 15:06:37 ታዋቂ ሳይሆን አዋቂ ሁን!

☞ሸሪዓዊ ርዕሶችን የሚመለከቱ ጭብጦች፣ ምልከታዎችና ትንታኔዎችን በብዕራችን ከመክተባችን፣ በአንደበታችን ከመናገራችንና በአእምሮኣችን ከማሰባችን በፊት በዚህ ርዕስ ላይ በቂ የሆነ የእውቀት ክምችት፣ ያልተዛባ የማስተላለፍ ብቃት እንዲሁም ሰናይ የሚባል እቅድ እንዳለን እናረጋግጥ። የኢስላም ሊቃውንቶች የተለያዩ ሸሪዓን የተመለከቱ ብይኖችንና ምልከታዎች ከመተንተናቸው በፊት አይኖቻቸው በሺዎች የሚገመቱ አያሌ ድርሳናትን ተመልክተው፣ መዳፎቻቸው ከአስር ሺዎች የሚልቁ ገፆችን አገላብጠውና ለዚህም መሰረታዊ ስንቅ የሚሆናቸውን ስር የሰደደ የፈጣሪ ፍራቻን አላብሰውት ነበር። በሸሪዓ ሚዛን ታዋቂነት በራሱ ተፈልጎ የሚለፋለት መሰረታዊ ግብ አይደለም። እንደውም በቀደምት አበዎች ዘንድ ታዋቂነትን መሻት ከመናፍቃን ተርታ የሚያስመድብ ሀጢያት ተደርጎ ተቆጥሯል።

አምሎኮኣዊ ድንበር የተበጀላቸው ነገሮች በአጠቃላይ ኢኽላስ የሚባል እጅግ ከባድ ድልድይ ተዘርግቶላቸዋል። ይህን ድልድይ ማለፍ የቻለ ብቻ ትክክለኛውን መቅሰድ ያሳካል። ይህን የተቀደሰ አላማ ባፈገፈገ መልኩ ዝናን መሻት የተቀላቀለበት ፅሁፍም ሆነ ድምፅ ብኩን መሆኑ እርግጥ ነው። የእውቀት ሽታን በወጉ ያላሸተቱ እጆችና ከእውቀት ነፃ አጃቢ የበዛላቸው ስብዕናዎች ይህን ትልቅ መርሆ በመሸሻቸው ሰበብ አስገራሚ ግትርነትና ማንነት ላይ ብቅ ይላሉ። ለጥቂት ግዜያት እጆች አፎች ላይ ተደራርበውና አይኖች ፈጠውላቸው የተደነቁ ፅሁፎች እንዲሁም ጆሮዎች የሚናፍቋቸው ድምፆች በእውነትም የአላህ ፊት ካልተፈለገባቸው ትቢያ ሆነው በአጭር ግዜያት ይበናሉ። በተቃራኒው እይታን የተነፈጉ የታፈኑ ፅሁፎችና ከማዳመጫ ታንቡር የሸሹ ድምፆች ሐቅ ተላብሰው የአላህ ፊት ከተሻባቸው በግዜ ሂደት ይጎመራሉ። በእውነትም ያብባሉ። ይህ ሁሉ በግዜ ሂደት የሚፈታ እንቆቅልሽ እንደሆነ እሙን ይሁንልኝ።

ለአላህ ተብለው የተሰሩ ተግባሮች ስራቸው ወደ ምድር እየሰደደ ፍሬያቸው እያበበ ሰዎችም ፈለጎቻቸውን እየቀጠፉና መአዛውን እየታወዱ ይዘወትራሉ። እውቀት ላይ ትእግስት የሌላቸው አካሎች በፍፁም መልካም ፍሬን ሊያፈሩ፣ ስብእናን ሊያንፁና የተንሻፈፈን ሊያቀኑ አይችሉም። ፅናትም አይኖራቸው። ተራ ዝና መሻት ይሰለቻል። ያደክማል። ከዝና ስር ተሰግስገው የተደበቁ እውነተኛ ማንነቶች ከእውቅና ማግስት ይፋ ሲሆኑ ግራ የሚያጋቡ አስገራሚ ስብዕናዎች ሆነው ብቅ ይላሉ።

እውቀት ከማንም በላይ ባለቤቱን ከቃላት ግድፈትና ከእሳቤ ብክነት እርምትን ይሰጣል። እውቀትና ኢኽላስ ያልጎተተው ዝና መኣዛው የጠነዛ፣ ቅምሻው የጎመዛና መጨረሻው መሳለቂያ ነው። ይህን ስል ሀቅ ተናጋሪ አፎችን ለመለጎምና ሀቅ ፀሀፊ እጆችን ለመጠምዘዝ አይደለም። በእውቀት ላይ ተቀምጠናል ብለው ለሚመፃደቁ ዝንጉዎች በፍፁም ብርታት አይሰጥም። ነገር ግን ሁሉም በልኩ እንዲራመድና ከደረጃው በላይ እንዳይንጠራራ ይሁን።

ዐብዱረዛቅ አል-ሐበሺይ

https://t.me/abdurezaq27
1.2K views12:06
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-03-13 17:01:49 ¨አግብታ የፈታች አልያም ባል የሞተባት ሴት ክብር!
—————————————————
አንዲት በሰሓቦች ዘመን የነበረች ሴት ባሏ የሞተ አልያም የፈታት ግዜ ሰሓቦች እሷን ለመንከባከብና ለመደገፍ ክብር በተላበሰ መልኩ ይቻኮሉ ነበር። የሰሓቦችን ታሪክ ብናገላብጥ አንዲት ሰሓቢይ ሴት አራት ሰሓቦችን በተለያየ ግዜ እንዳገባች እንረዳለን። አንዱ ሲሞት ሌላውን እያገባች ተከብራ ኖራለች። እሷን የመሰሉ ሴቶችን በንቀትና በጉድለት በፍፁም አይመለከቷቸውም ነበር።

ዐቲካ የምትባልን ሴት ተመልከት!። የታላቁ ሰሀቢይ አቡ በክር ልጅ አገባት። በጣም ታፈቅረው ነበር እሱም በቃላት ሊገለፅሉት በማይችል መልኩ ይንሰፈሰፍላታል። ከግዜያት ቡኃላ ሸሂድ ሆኖ ሞተ። ከዛም ታላቁ ሰሓቢይ ዑመር አል-ፋሩቅ አገባትና እሱም ሸሂድ ሆኖ ሞተ። ከዛም እሷን ለማግባትና ለማክበር የመልእክተኛው ሓዋሪይ የሚባለው ታላቁ ሰሓባ ዙበይር ኢብኑ-ል ዓዋም ተቻኮለ። አገባትም። ከጥቂት ግዜ ቡኃላም ሸሂድ ሆኖ ሞተ። እነዚህ ሁሉ ታላላቅ ሰዎች ሲሞቱ "በባሎቿ ላይ ሙሲባ የምታመጣ! "አልተባለችም። እንደውም "ሸሂድ መሆን የፈለገ ዐቲካን ያግባ!" ተብሏል።

የአስማዕ ቢንት ዑመይስን ታሪክ እናገላብጥ። የመጨረሻ ባሏ ታላቁ ሰሓቢይ ዐሊይ ኢብን አቢጧሊብ ነበር። ከሌሎች ባሎቿ የወለደቻቸውን ልጆች ያጫውታል። የሷን ጣፋጭ ንግግርና የልጆቿን ጨዋታ በመስማት በደስታ ፈገግም ይል ነበር። በቀደሙ ባሎቿ ላይ በፍፁም ቅናት አይሰማውም። "በቀደሙ ባሎችሽ ላይ ስሞቷ ብታሰሚ እቆጣሻለው! እነሱን በፍፁም በመጥፎ ስታነሺያቸው እንዳልሰማ። እነሱ ወዳጆቼ ናቸው።" ይላት ነበር። ሁሉንም አላህ ስራቸውን ይውደድ። የትኛዋም ሰሓቢያ ሌላ ባል ስታገባ የመጀመሪያ ባሏን እያወሳች በክህደት አልተጠረጠረችም።

የአላህ መልእክተኛም ከእናታችን ዐይሻ በስተቀር ድንግል ሴት አላገቡም። መጀመሪያ ትዳርን የመሰረቱትም ከሳቸው በፊት ትዳርን ከምታውቀው ከእናታችን ኸዲጃ ቢንት ኹወይሊድ ጋር ነበር። የተፈታችን አልያም ባል የሞተባትን ሴት ማግባት እንዲሁም ከአንድ በላይ ማግባት ስነ ምግባርን የሚጥስ፣ ክብርን የሚነካና የሚጠየፉት የወረደ ተግባር ቢሆን ቀድሞውንም ኢስላም ይከለክለዋል። ስነ ምግባርን፣ ልቅናንና እውነተኛ ሰብኣዊነትን ያስተማረን ኢስላም ነውና።

የተፈታች ሴት በፍፁም የውድቀት ምልክት አይደለችም። አላህን ከፈራች ከፍቺውም ቡኃላ አላህ ከችሮታው ያብቃቃታል። የተሻለ የህይወት መስመር ያበጅላታል። ከመጀመሪያ ባሏ የተሻለ መልካም የትዳር አጋር አላህ ሊሰጣት ይከጀላል። መጪው ቀናት በአላህ ፈቃድ መልካም ብስራትና ተስፋ ይዞ ብቅ ይላል። ስለዚህ አንገትሽን አትድፊ!

በሚያሳዝን ሁኔታ በአሁን ወቅት አግብታ የፈታችን ሴት ለማግባት የሚያስብ የሷን መብት ልክ እንደ አሮጌና ያገለገለ መኪና አስመስሎ ፕሮፖዛል የሚያቀርብ አለ። ይህ በሴቶች መብት ላይ ግፍና በደል ነው። ባል የሞተባት አልያም የፈታች እህትና ልጅ ቢኖረህ ለሷ የምትመኘውን ለሌችም እንስቶች መመኘት አለብህ። ይልቁንም የደረሰባቸውን ሀዘን ለመጠገን መሯሯጥ ይገባናል። በብዛት የሚያጋጥማቸውን ሞራላዊና ማህበረሰባዊ ተፅእኖ በመልካም ለመግፈፍ መታተር ይጠበቅብናል። በክፉ ከሚመለከቷቸው የሰው አውሬዎች ልንከላከላቸውና በደካማ ጎናቸው ለማጥቃት ካሰፈሰፉ ዋልጌዎች ልንጠብቃቸው የበኩላችንን ጥረት ማድረግ አለብን።

ስሜት ካወረው ፅልመት ተላቀን ሰብኣዊነት የተሞላ ኢስላሚዊ መንፈስ ይኑረን። ቁምነገሩ የኛ መልካም ስብዕና እንጂ የሷ የቀደመ ትዳር ተፅእኖ አይኖረውም። በብልሀትና በስነምግባር የተሞላ መልካም የትዳር አጋር ካገኘች በአላህ ፈቃድና ችሮታ ያለፈ ህይወቷን አስረስቶ ስኬታማ ትዳርን በሀሴት ይለግሳታል። ኋላ ቀር የሆኑ አባባሎች ጠፍረው አይከርችሙን። መመሪያችን ኢስላም ብቻ ይሁን።

በሙስሊም እህቶቻችን ላይ አላህን እንፍራ!https://t.me/abdurezaq27
1.0K views14:01
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-03-10 09:17:38 እህቶቻችን ወደ ዲን ሲቀርቡ፣ ኒቃብ ሲለብሱ፣ ቁርኣት ላይ ሲያተኩሩ አቅማቸውን የሚፈታተኑ ብዙ ፈተናዎችን ያስተናግዳሉ። ይበልጥ የሚያመው ደግሞ ከውጪው በበለጠ በቅርብ ሰው የሚመጣው ፈተና ነው። ከዚህም ይበልጥ የሚያመው ወደ ዲን ከቀረበው፣ ሰበብ ይሆናል ተብሎ ተስፋ ከሚጣልበት ወንድም የሚታየው ነገር ይበልጥ ሞራልን የሚያቀዘቅዝ፣ ስሜትን የሚጎዳ መሆኑ ነው። ቀጥሎ የማሰፍረው ከአንዲት እህት የደረሰኝ መልእክት ነው። መቼም የሁላችንም ልብ አንድ አይደለም። ምናልባት ቆም ብለን እናስብ ዘንድ በአላህ ፈቃድ የሆነ ያክል እገዛ ይኖረው ይሆናል።
اَلسَلامُ عَلَيْكُم وَرَحْمَةُ اَللهِ وَبَرَكاتُهُ‎
አንዳንዴ ነገሩ ይከብዳል...
ብዙ እህቶች የሚወድቁበት የሆነ ብዙ ከባድ ፈተና አለ። በጣም ጠንካራ የሆኑት እንጂ የጠይቋቋሙት። ደግሞ ሴቶች ደካማ እንደሆኑ ታውቃለህ። የታላቁ ጌታ በፍፁም ከኔ ራህመት ተስፋ አትቁረጡ የሚል የተስፋ ቃል ባልነበረ ብዙ እህቶች ተስፋ በቆረጡ ነበር....

አሏህ ካዘነላቸው የሱና ወንድሞች ዉጪ ነገሩ እንዲህ ሆኗል ከዲን ይልቅ መልክ እድሜ ላይ በርትተዋል። መስፈርቶቹ ከአንድ ሰው ነው የሚላኩት ተብሎ እስኪጠረጠር ድረስ እንድ አይነት በመልክ ወላ በእድሜ ቀይ ቆንጆ እድሜዋ ከዚህ በታች ብዙ ኪታብ የቀራች የተማረች...ብዙ ብዙ ደግሞ እሱ ጋር ኖሮ ቢሆን እሺ።

ሁሉም ሴቶች ቀይ ናቸውን??
እሺ አንድ ሴት ቢያንስ መልኩንና ቂርዓቱን ብታሟላ እንዴት የተማረችና እድሜዋ ከዚህ በታች እንዴት ሊሆን ይችላል??
Maybe ሊኖር ይችላል ግን እጅግ ጥቂት ነው።

የምር እስኪ አንድ ወንድ ሱኒይ ሲሆን ወደ ሱና ሲጠጋ ፂሙን ይለቃል ልብሱን ከፍ ያደርጋል እና ሌሎችንም ነገሮች ይፈፅማል። የታዘዘውን ይሄን በማድረጉ ወሀቢይ ሊባል ይችላል እና ሌላም ፈተና ሊደርስበት ይችላል። ግን ሀቂቃ እንደ ሴቷ አይፈተንም። ሴቷ ኒቃብ ስትለብስ ሙተበሪጅ ሆና ዝም ያሏት ቤተሰቦቿ ሙተሀጂብ የሆነች ቀን ከገዛ ቤተሰቦቿ ፊትናው ይጀምራል። ከዛን ስራዋን ታጣለች። ሌላ ስራ ለማግኝትም ትቸገራለች። እቤት በገባች በወጣች ቁጥር አዛ ትደረጋለች። "እኔ ያስተማርኩሽ ለዚ አይደለም፣ እንደሷ አመድ አፋሽ ሆነሽ እንዳትቀሪ" እየተባለ ምሳሌ ይሰጥባታል። ሀታ በገዛ ቤቷ ባዳ የሆነች ያክል እስኪሰማት ድረስ። ታውቀዋለህ ግን ይሄ ስሜት ምን ያክል እንደሚያም?!! እኔ ግን በጭራሽ አመድ አፋሽ አልሆንኩም። እንዲያውም የጌታዬን እዝነትና ዉዴታን ነው ያፈስኩት። ከዚያም ደርስ ትከለከላለች። ግን የሚገርመው ደርስ ልትሄድ ልትቀራ "የትራንስፖርት አልሰጥም" ያለ ቤተሰብ ለዱንያዊ ትምህርት በሺዎች አውጥቶ ያስተምራል!!

ትራንስፖርት አጥታ በእግርም ቢሆን እየሄድኩ ቂርዓቴን እቀራለሁ ብላ በህመም ምክንያት ያቆመች እህት እንዳለችስ...??

ከዚህ ሁሉ መውጫ ዲኗንም ለመማር ያላት አማራጭ ኒካህ ማሰር እንደሆነ ታስባለች። በቤተሰቦቿ ቤት እንዳትቀራ ተከልክላለችና። ግን ለኒካህ የሚመጡ ወደ ሱና ተጠግተዋል የሚባሉ ወንዶች ይሄ ነው መስፈርታቸው አላህ ካዘነለት ውጪ። ቢያንስ ዲንን አስቀድመው ቢሆን፣ ዲን የላትም ብሎ ቢሆን የሚተዋት በጣም ደስ ይል ነበር።
እስኪ እናንተ የሱና ወንድሞች ካላዘናችሁልን ማን ያዝንልናል? ኢኽዋኑ!? አህባሹ!? በጭራሽ እነሱማ ሂጃባችንንም አቂዳችንንም ሊያጠፉ ነው ሚፈልጉት።

አልገጠመህምን አልሰማህምን ሱኒይ ሆና ኢኽዋኒ አገባች ሲባል?! አንድ የሱና እህት ከዚህ ሁሉ በቃ አስተካክለዋለሁ ብላ ኢኽዋን አግብታ በዛው የቀረች የተገለበጠች። ግን አንዳንዷ ደግሞ የሱና ጀግና እንጂ አይሆንም ብላ ትንሽ እድሜዋ ከፍ ካለ......የሱና ወንድ የሚባሉት ደግም የሚፈልጉት በእድሜ ትንሿን ነው። ሁሉንም እየወቀስኩ አይደለም። ደግሞ የፈለጉትን መሰፈርት ማውጣት መብታቸው ነው።
ማንም የፈለገውን መስፈርት ማድረግ መብቱ ነው ግን...???

አላህ ለነሱ ያለውን ሪዝቅ ማንም አይወስደውም ሶብር ማድረግ ነው አላህ የተሻለውን ምርጡን ያመጣል ግን ያው ሴቶች ደካማ አይደለን
አንዳንዴ ያቅታል። ህመማችን እንዲገባችሁ ነው ይህን የምለው።

ምን እንደምፈራ ግን ታውቃለህ? በፊት ኒቃብ ስለብስ ኡሚ አሪፍ ስራ ነው ያለሽ (የመንግስት ስራ ነበር የምሰራው) "ይሄን ስራ አትተይው። ሌላው ቢቀር ቢያንስ ኒካህ እስከምታስሪ ቆይ። እንዲህ ኒቃብ ከለበሽ ባል አታገኚም። ማን ያይሻል?" ብላኝ ነበር። እኔ ግን ለነፍሴ: "በጭራሽ አላህን በመታዘዝሽ ሪዝቅሽ ቢሰፋ እንጂ አይጠብም። እንዲያውም አላህን መታዘዝ ሪዝቅ ለመምጣት ሰበብ ነው" እያልኩ አበረታት ነበር የመንግስቱን ስራም ተውኩት፣ በኒቃብ መስራት አይቻልምና።
አሁን ግን ድሮም ነግሬሽ ነበር
እኔ ያልኩሽን ብትሰሚ ኖሮ ... መባሉ ያስፈራኛል።
እሷን ደስ ይበላት ብዬ የምወደውን ቂርዓት ትቼ እሷ ደስ የሚያሰኛትን ነገር እየሰራሁ ነው አላህ ነገሮቼን እስከሚያስተካክልልኝ ድረስ።

ኒቃብ ስለለበስኩ ኡሚ ለወራቶች ነው ያኮረፈችኝ። አብረን አንድ ቤት ውስጥ ሆነን ትናፍቀኝ ነበር። ሀቂቃ በጣም የሚያሳምም ነው ስሜቱ። ግን መፀናኛዬ ጌታዬ ነበር። እሱ ቅርብ የሆነ ሁሉን ነገር እያየልኝ እየሰማ ስለሆነ ደስ ይለኝ ነበር። ወሏሂ በጣም የሚያስከፋ ነገር ገጥሞኝ እኔ ግን ጌታዬን እያሰብኩ እስቅ ነበር። ሶብር በማድረጌ ከእሱ የማገኝውን አጅር እያሰብኩ እፅናና ነበር። አልሀምዱሊላህ በፊትም አሁንም በቃላትም በንግግርም ልገልፀው የማልችለው ሰላምና መረጋጋት ደስታ በውስጤ አለ።

ሌሎችም ኒቃባቸውን ቤተሰብ የሚያቃጥልባቸው በጣም ከባድ ፊትና የሚገጥማቸው ብዙ እህቶች አሉ። ከኔም የባሰ ብዙ አለና አብዝቼ ጌታዬን አመሰግነዋል ሁሌም። ኒቃቤ ለኔ ክብሬ ውበቴ ነው ከአጉል እይታ የሚከላከለኝ በጌታዬ ፍቃድ መጠበቂያዬም ጭምር። አላህ ከፊትና ይጠብቀንና የሞትኩ ቀን ቢሆን እንጂ አይወልቅም ኢንሻ አላህ። ዱንያ ላይ ያለውን ነገር ሁሉ እንስጥሽ ቢሉኝ እንኳን ወላሂ ሱመ ወላሂ እኔ በኒቃቤ አልደራደርም። ከፍ ያለው አላህ ለሁላችንም እስቲቃማውን ይስጠን።
1.1K views06:17
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-03-10 09:17:16 ኢኽቲላጥና አደጋዎቹ
≈
ኢብኑ-ል ቀይዪም፦

"ሴቶችን ከወንዶች ጋር እንዲቀላቀሉ ማመቻቸት የሁሉም ፈሳድና አደጋ መሰረት ለመሆኑ ምንም ጥርጥር የለውም። ይህ ተግባር ጠቅላይና ሁሉን አካታች ለሆነ ቅጣት ዋናው ምክንያት ነው። የወንድና የሴት መቀላቀል ለብልግናና ለዝሙት መንሰራፋት ዋናው ሰበብ ነው። ለጅምላ ሞት መበራከትም የዝሙት መስፋፋት አብይ ምክንያት እንደሆነ ይታወቃል። ይህም ሴቶች ከወንዶች ጋር እንዲቀላቀሉ በማስመቸት፣ በወንዶች መሀል ተገላልጠውና ተጋጊጠው እንዲጓዙ በመፍቀድ የሚመጣ አደጋ ነው። ሙስሊም መሪዎች ከዲኑ በፊት የዱንያና የህዝቡ መበላሸት ዋናው ሰበብ ኢኽቲላጥ መሆኑን ቢገነዘቡ ኖሮ ነገሩን ጠንከር ባለ መልኩ በመከልከልና አዳራሽ መንገዶቹን በመዝጋት ላይ በትጋት ይበረቱና ይጠነክሩ ነበር።"

#الطرق_الحكمية" (صـ 237) .

https://t.me/abdurezaq27
850 views06:17
ክፈት / አስተያየት ይስጡ