Get Mystery Box with random crypto!

ኢኽቲላጥና አደጋዎቹ ≈ ኢብኑ-ል ቀይዪም፦ 'ሴቶችን ከወንዶች ጋር እንዲቀላቀሉ ማመቻቸት የ | 🌹የሱና እህቶች የለውጥ ሚና🌹

ኢኽቲላጥና አደጋዎቹ

ኢብኑ-ል ቀይዪም፦

"ሴቶችን ከወንዶች ጋር እንዲቀላቀሉ ማመቻቸት የሁሉም ፈሳድና አደጋ መሰረት ለመሆኑ ምንም ጥርጥር የለውም። ይህ ተግባር ጠቅላይና ሁሉን አካታች ለሆነ ቅጣት ዋናው ምክንያት ነው። የወንድና የሴት መቀላቀል ለብልግናና ለዝሙት መንሰራፋት ዋናው ሰበብ ነው። ለጅምላ ሞት መበራከትም የዝሙት መስፋፋት አብይ ምክንያት እንደሆነ ይታወቃል። ይህም ሴቶች ከወንዶች ጋር እንዲቀላቀሉ በማስመቸት፣ በወንዶች መሀል ተገላልጠውና ተጋጊጠው እንዲጓዙ በመፍቀድ የሚመጣ አደጋ ነው። ሙስሊም መሪዎች ከዲኑ በፊት የዱንያና የህዝቡ መበላሸት ዋናው ሰበብ ኢኽቲላጥ መሆኑን ቢገነዘቡ ኖሮ ነገሩን ጠንከር ባለ መልኩ በመከልከልና አዳራሽ መንገዶቹን በመዝጋት ላይ በትጋት ይበረቱና ይጠነክሩ ነበር።"

#الطرق_الحكمية" (صـ 237) .

https://t.me/abdurezaq27