Get Mystery Box with random crypto!

እህቶቻችን ወደ ዲን ሲቀርቡ፣ ኒቃብ ሲለብሱ፣ ቁርኣት ላይ ሲያተኩሩ አቅማቸውን የሚፈታተኑ ብዙ ፈተ | 🌹የሱና እህቶች የለውጥ ሚና🌹

እህቶቻችን ወደ ዲን ሲቀርቡ፣ ኒቃብ ሲለብሱ፣ ቁርኣት ላይ ሲያተኩሩ አቅማቸውን የሚፈታተኑ ብዙ ፈተናዎችን ያስተናግዳሉ። ይበልጥ የሚያመው ደግሞ ከውጪው በበለጠ በቅርብ ሰው የሚመጣው ፈተና ነው። ከዚህም ይበልጥ የሚያመው ወደ ዲን ከቀረበው፣ ሰበብ ይሆናል ተብሎ ተስፋ ከሚጣልበት ወንድም የሚታየው ነገር ይበልጥ ሞራልን የሚያቀዘቅዝ፣ ስሜትን የሚጎዳ መሆኑ ነው። ቀጥሎ የማሰፍረው ከአንዲት እህት የደረሰኝ መልእክት ነው። መቼም የሁላችንም ልብ አንድ አይደለም። ምናልባት ቆም ብለን እናስብ ዘንድ በአላህ ፈቃድ የሆነ ያክል እገዛ ይኖረው ይሆናል።
اَلسَلامُ عَلَيْكُم وَرَحْمَةُ اَللهِ وَبَرَكاتُهُ‎
አንዳንዴ ነገሩ ይከብዳል...
ብዙ እህቶች የሚወድቁበት የሆነ ብዙ ከባድ ፈተና አለ። በጣም ጠንካራ የሆኑት እንጂ የጠይቋቋሙት። ደግሞ ሴቶች ደካማ እንደሆኑ ታውቃለህ። የታላቁ ጌታ በፍፁም ከኔ ራህመት ተስፋ አትቁረጡ የሚል የተስፋ ቃል ባልነበረ ብዙ እህቶች ተስፋ በቆረጡ ነበር....

አሏህ ካዘነላቸው የሱና ወንድሞች ዉጪ ነገሩ እንዲህ ሆኗል ከዲን ይልቅ መልክ እድሜ ላይ በርትተዋል። መስፈርቶቹ ከአንድ ሰው ነው የሚላኩት ተብሎ እስኪጠረጠር ድረስ እንድ አይነት በመልክ ወላ በእድሜ ቀይ ቆንጆ እድሜዋ ከዚህ በታች ብዙ ኪታብ የቀራች የተማረች...ብዙ ብዙ ደግሞ እሱ ጋር ኖሮ ቢሆን እሺ።

ሁሉም ሴቶች ቀይ ናቸውን??
እሺ አንድ ሴት ቢያንስ መልኩንና ቂርዓቱን ብታሟላ እንዴት የተማረችና እድሜዋ ከዚህ በታች እንዴት ሊሆን ይችላል??
Maybe ሊኖር ይችላል ግን እጅግ ጥቂት ነው።

የምር እስኪ አንድ ወንድ ሱኒይ ሲሆን ወደ ሱና ሲጠጋ ፂሙን ይለቃል ልብሱን ከፍ ያደርጋል እና ሌሎችንም ነገሮች ይፈፅማል። የታዘዘውን ይሄን በማድረጉ ወሀቢይ ሊባል ይችላል እና ሌላም ፈተና ሊደርስበት ይችላል። ግን ሀቂቃ እንደ ሴቷ አይፈተንም። ሴቷ ኒቃብ ስትለብስ ሙተበሪጅ ሆና ዝም ያሏት ቤተሰቦቿ ሙተሀጂብ የሆነች ቀን ከገዛ ቤተሰቦቿ ፊትናው ይጀምራል። ከዛን ስራዋን ታጣለች። ሌላ ስራ ለማግኝትም ትቸገራለች። እቤት በገባች በወጣች ቁጥር አዛ ትደረጋለች። "እኔ ያስተማርኩሽ ለዚ አይደለም፣ እንደሷ አመድ አፋሽ ሆነሽ እንዳትቀሪ" እየተባለ ምሳሌ ይሰጥባታል። ሀታ በገዛ ቤቷ ባዳ የሆነች ያክል እስኪሰማት ድረስ። ታውቀዋለህ ግን ይሄ ስሜት ምን ያክል እንደሚያም?!! እኔ ግን በጭራሽ አመድ አፋሽ አልሆንኩም። እንዲያውም የጌታዬን እዝነትና ዉዴታን ነው ያፈስኩት። ከዚያም ደርስ ትከለከላለች። ግን የሚገርመው ደርስ ልትሄድ ልትቀራ "የትራንስፖርት አልሰጥም" ያለ ቤተሰብ ለዱንያዊ ትምህርት በሺዎች አውጥቶ ያስተምራል!!

ትራንስፖርት አጥታ በእግርም ቢሆን እየሄድኩ ቂርዓቴን እቀራለሁ ብላ በህመም ምክንያት ያቆመች እህት እንዳለችስ...??

ከዚህ ሁሉ መውጫ ዲኗንም ለመማር ያላት አማራጭ ኒካህ ማሰር እንደሆነ ታስባለች። በቤተሰቦቿ ቤት እንዳትቀራ ተከልክላለችና። ግን ለኒካህ የሚመጡ ወደ ሱና ተጠግተዋል የሚባሉ ወንዶች ይሄ ነው መስፈርታቸው አላህ ካዘነለት ውጪ። ቢያንስ ዲንን አስቀድመው ቢሆን፣ ዲን የላትም ብሎ ቢሆን የሚተዋት በጣም ደስ ይል ነበር።
እስኪ እናንተ የሱና ወንድሞች ካላዘናችሁልን ማን ያዝንልናል? ኢኽዋኑ!? አህባሹ!? በጭራሽ እነሱማ ሂጃባችንንም አቂዳችንንም ሊያጠፉ ነው ሚፈልጉት።

አልገጠመህምን አልሰማህምን ሱኒይ ሆና ኢኽዋኒ አገባች ሲባል?! አንድ የሱና እህት ከዚህ ሁሉ በቃ አስተካክለዋለሁ ብላ ኢኽዋን አግብታ በዛው የቀረች የተገለበጠች። ግን አንዳንዷ ደግሞ የሱና ጀግና እንጂ አይሆንም ብላ ትንሽ እድሜዋ ከፍ ካለ......የሱና ወንድ የሚባሉት ደግም የሚፈልጉት በእድሜ ትንሿን ነው። ሁሉንም እየወቀስኩ አይደለም። ደግሞ የፈለጉትን መሰፈርት ማውጣት መብታቸው ነው።
ማንም የፈለገውን መስፈርት ማድረግ መብቱ ነው ግን...???

አላህ ለነሱ ያለውን ሪዝቅ ማንም አይወስደውም ሶብር ማድረግ ነው አላህ የተሻለውን ምርጡን ያመጣል ግን ያው ሴቶች ደካማ አይደለን
አንዳንዴ ያቅታል። ህመማችን እንዲገባችሁ ነው ይህን የምለው።

ምን እንደምፈራ ግን ታውቃለህ? በፊት ኒቃብ ስለብስ ኡሚ አሪፍ ስራ ነው ያለሽ (የመንግስት ስራ ነበር የምሰራው) "ይሄን ስራ አትተይው። ሌላው ቢቀር ቢያንስ ኒካህ እስከምታስሪ ቆይ። እንዲህ ኒቃብ ከለበሽ ባል አታገኚም። ማን ያይሻል?" ብላኝ ነበር። እኔ ግን ለነፍሴ: "በጭራሽ አላህን በመታዘዝሽ ሪዝቅሽ ቢሰፋ እንጂ አይጠብም። እንዲያውም አላህን መታዘዝ ሪዝቅ ለመምጣት ሰበብ ነው" እያልኩ አበረታት ነበር የመንግስቱን ስራም ተውኩት፣ በኒቃብ መስራት አይቻልምና።
አሁን ግን ድሮም ነግሬሽ ነበር
እኔ ያልኩሽን ብትሰሚ ኖሮ ... መባሉ ያስፈራኛል።
እሷን ደስ ይበላት ብዬ የምወደውን ቂርዓት ትቼ እሷ ደስ የሚያሰኛትን ነገር እየሰራሁ ነው አላህ ነገሮቼን እስከሚያስተካክልልኝ ድረስ።

ኒቃብ ስለለበስኩ ኡሚ ለወራቶች ነው ያኮረፈችኝ። አብረን አንድ ቤት ውስጥ ሆነን ትናፍቀኝ ነበር። ሀቂቃ በጣም የሚያሳምም ነው ስሜቱ። ግን መፀናኛዬ ጌታዬ ነበር። እሱ ቅርብ የሆነ ሁሉን ነገር እያየልኝ እየሰማ ስለሆነ ደስ ይለኝ ነበር። ወሏሂ በጣም የሚያስከፋ ነገር ገጥሞኝ እኔ ግን ጌታዬን እያሰብኩ እስቅ ነበር። ሶብር በማድረጌ ከእሱ የማገኝውን አጅር እያሰብኩ እፅናና ነበር። አልሀምዱሊላህ በፊትም አሁንም በቃላትም በንግግርም ልገልፀው የማልችለው ሰላምና መረጋጋት ደስታ በውስጤ አለ።

ሌሎችም ኒቃባቸውን ቤተሰብ የሚያቃጥልባቸው በጣም ከባድ ፊትና የሚገጥማቸው ብዙ እህቶች አሉ። ከኔም የባሰ ብዙ አለና አብዝቼ ጌታዬን አመሰግነዋል ሁሌም። ኒቃቤ ለኔ ክብሬ ውበቴ ነው ከአጉል እይታ የሚከላከለኝ በጌታዬ ፍቃድ መጠበቂያዬም ጭምር። አላህ ከፊትና ይጠብቀንና የሞትኩ ቀን ቢሆን እንጂ አይወልቅም ኢንሻ አላህ። ዱንያ ላይ ያለውን ነገር ሁሉ እንስጥሽ ቢሉኝ እንኳን ወላሂ ሱመ ወላሂ እኔ በኒቃቤ አልደራደርም። ከፍ ያለው አላህ ለሁላችንም እስቲቃማውን ይስጠን።