Get Mystery Box with random crypto!

#ኸሚስ_አመሻሹ_ላይ ! ጉዴን እማዋዬው አለኝታዬ ነቢ! ነቢ ከጌትዬው መግባቢያ ቋንቋዬ፣ አስታራቂዬ | ሁስነል ኹሉቅ

#ኸሚስ_አመሻሹ_ላይ !
ጉዴን እማዋዬው አለኝታዬ ነቢ!
ነቢ ከጌትዬው መግባቢያ ቋንቋዬ፣ አስታራቂዬ፣ ወደ እልፍኝ
አዳራሹ እጄን ይዘው የሚያስገቡኝ አሳላፊዬ፣ ወደምፈልገው
መዳረሻዬ መንገዴ መንሃጄ ቂብላዬ ፊርቃዬ ጀምዓዬ ሶላቴ
የሁለት ዓለም ጀነቴ!
ለነቢ ያለኝ ፍቅር ሸርጡን ባይሞላም አውቀዋለሁ መዳኛዬ
ነው። ስማቸውን የማነሳበት ሶለዋትም ጭንቁን ሁሉ
ማለፊያዬ ነው። እማዋይሁ ነቢ ባዋዬንሁ ሁሉ አጚሱና
ያረሱለሏህ! አዛኙ ነቢ፣ ጋሻዬ ነብይ፣ ሁሌም ክፍት የሆነ
የምህረት በር፣ ሺሊላ ብሎ የሚመጣን ሲጠባበቅ ውሎ
የሚያድር ጠጀሳር ያወደው የሙሐባ ቀዬ፣ ከዓለም በሰፋው
መንደር በነቢ ጊቢ ተገኘን ሁሉ ይከወንልን ብለን፣ ፋይል
ከፍተን ወደ መሃል ዳኛው አሳልፉን አስወስኑልን አገር ይሻር
ብለን!
አዛ እንዲረግፍ ሽተናልና እንደዛ የዓረብ ገጠሬ
የማረፊያቸውን መዝጊያ ይዘን የሙጥኝ እንላለን። እንዲህ
ሆኖ ነበር… ጭንቅ ቢለው፣ ቢጨልምበት ከመዳኛው ጋር
ወንጀሉ ያራራቀው ቢመስለው ነቢ ያረፉበት መቃብር መጣና
"ያረሱለላህ በጣም ከባድ ወንጀል ፈፅሚያለሁ። ነገር ግን
አላህ
ﻭﻟﻮ ﺃﻧﻬﻢ ﺇﺫ ﻇﻠﻤﻮﺍ ﺃﻧﻔﺴﻬﻢ ﺟﺎﺀﻭﻙ ﻓﺎﺳﺘﻐﻔﺮﻭﺍ ﺍﻟﻠﻪ ﻭﺍﺳﺘﻐﻔﺮ
ﻟﻬﻢ ﺍﻟﺮﺳﻮﻝ ﻟﻮﺟﺪﻭﺍ ﺍﻟﻠﻪ ﺗﻮﺍﺑﺎ ﺭﺣﻴﻤﺎ
"እነሱም ነፍሶቻቸውን በበደሉ ግዜ ወደ አንተ ቢመጡና
አላህን ምህረት በለመኑ መልዕክተኛውም ለነርሱ ምሕረትን
በለመነላቸው ኖሮ አላህን ጸጸትን ተቀባይ አዛኝ ሆኖ ባገኙት
ነበር።" ማለቱን ሰምቻለሁና አሁን የተገኘሁት ምህረት
እንዲጠይቁልኝ ለመንገር ነው።" አለና እያለቀሰ አንዲትን
ግጥም አነብንቦ በእምባ ወደመጣበት ተመለሰ።
ይሄንን ክስተት አል-ኡትቢ እዬተመለከቱ ነበር። እንግዳው
ሰውዬ ከሄደ በኋላ ጥልቅ እንቅልፍ ወሰዳቸው።
በህልማቸውም ረሱሉላህን ﷺ ተመለከቱ። እንዲህም
አሏቸው። "ይህንን ሰው አግኘውና አላህ እንደማረው
አበስረው!" አሏቸው።
ሃዬ ሃዬ ቢጃሂ ሰይዲል ሙርሰሊን ስማቸውን ጠርተን
ወንጀላችን ተሰርዞ፣ ሃጃችን ሞልቶ፣ ድልና ፈረጃ ለ‘ኛ ሁኖ፣
አይበጆ ተበጥሮ፣ ወገን አማን ሁኖ ይንጋ!
#ሶሉ_ዓለል_ሐቢብ
አሏሁመ ሶሊ ወሰሊም ወባሪክ ዓላ ሰይዱና ወመውላና
ሙሐመድ ወዓላ አሊሂ ወሶህቢሂ ወሰለም!


 


                             
                                
                                      
ﷺ ﷺ ﷺ ﷺ ﷺ ﷺ ﷺ   
      ﷺ ﷺ ﷺ ﷺ ﷺ ﷺ ﷺ              ﷺ ﷺ ﷺ ﷺ ﷺ ﷺ ﷺ




  
      
ተመሳሳይ ሃሳብ ያላቸው መልክቶች ቶሎ ቶሎ እንዲደርሳቹ ቻናላችንን
Join እንዲያደርጉ እንጠይቃለን፡፡ሼር በማድረግ ለሎሎች እንዲደርሱ
ያግዙን፡፡

እባክወ ለሚወዱት ሸር ያድርጉ
                  
                 
              
:¨·.·¨: ❀   ቻናላችንን ይ ላ ሉን!
·. Telegram Join ያድርጉ
@yeresulnfkrmeglecha

@yeresulnfkrmeglecha

┄┄┉┉✽̶»̶̥ ✿ »̶̥✽̶┉┉┄┄