Get Mystery Box with random crypto!

#ሰይጣን_የማይችላቸው_8ቱ_ትምህርቶች #አንድ- ደጋግማችሁ  የምታስቧቸው ሀሳቦች አካላዊ ተጓዳ | የፍቅር ጎጆ

#ሰይጣን_የማይችላቸው_8ቱ_ትምህርቶች



#አንድ- ደጋግማችሁ  የምታስቧቸው ሀሳቦች አካላዊ ተጓዳኞቻቸውን/አቻዎቻቸውን እንደሚስቡ አስታውሱ። ስለዚህ ስለምታስቡት ሃሳብ ተጠንቀቁ።

#ሁለት- ሁለት አካላት ሰውነታችንን እንደሚቆጣጠሩት ማወቅ አለብን።  ከእነዚህ አካላት አንዱ ለፍርሃት የሚነሳሳና ምላሽ የሚሰጥ ሲሆን፣ ሌላው ለእምነት የሚነሳሳና ምላሽ የሚሰጥ ነው። 

በእምነት ትመራለህ ወይንስ ፍርሃት እንዲቆጣጠርህ ትፈቅዳለህ?

#ሶስት- ተስፋ ሳይቆርጡ ውድቀትን አልፎ የመሄድ አቅም በየትኛውም የህይወት ጥሪ ውስጥ የላቀ ስኬት ላስመዘገበ ሰው ሁሉ ዋና ሀብት ነው።

#አራት- ውድቀት ሰው ሰራሽ ነው።  ሰው እንደ ቋሚነት እስካልተቀበለው ድረስ ፈጽሞ እውን አይሆንም።

#አምስት- የአንተ ብቸኛ ገደብ በራስህ አእምሮ ውስጥ የፈጠርከው ነው።

#ስድስት- ተፈጥሮ ስራ ፈትነትን ወይም ባዶነትን አይታገስም።  ሁሉም ቦታ በአንድ ነገር የተሞላ መሆን አለበት።  ግለሰቡ አእምሮውን  ለአዎንታዊ እና ለፈጠራ ሀሳቦች መገለጫነት ካልተጠቀመበት ተፈጥሮ አእምሮን በአሉታዊ ሐሳቦች ላይ እንዲሠራ በማስገደድ ክፍተቱን ይሞላል።

#ሰባት- አንድ ሰው እውቀትን እንዲጨምር ወይም ዋናውን የህይወት አላማውን ለማሳካት የሚያስችሉ ልማዶችን እንዲያዳብር ሲያስገድድ ውድቀት ሁሌም በረከት ነው።

#ስምንት እርግጠኛ በሆነ የህይወት አላማ የሚንቀሳቀስ ሰው በጊዜያዊ ሽንፈት እና ውድቀት መካከል ያለውን ልዩነት ይገነዘባል። ዕቅዶቹ ሲከሽፉ ሌሎችን እቅዶች ይተካል እንጂ ዓላማውን አይለውጥም። በፅናት ይቀጥላል!

#የስኬት_ፍልስፍና መጽሐፍ

የናፖሊዮን ሂል መጽሐፍ

የስኬት_ፍልስፍና 10ኛ ዕትም

teklu ጥላሁን