የአዲስ አበባ ከተማ መምህራን ማህበር ፕሬዘዳንት አቶ ድንቃለም ቶሎሳ በበኩላቸው መምህራን በህብረት ስራ ማህበራት ተደራጅተው የቤት ባለቤት እንዲሆኑ የትምህርት ቢሮ ሀላፊ ዶ/ር ዘላለም ሙላቱ ላደረጉት አስተዋፅዎና የከተማ አስተዳደሩ ለመምህራን ቅድሚያ በመስጠቱ ምስጋና አቅርበው መምህራኖችም የቁጠባ ባህላቸውን በማሳደግ የቤት ባለቤት የሚያደርጋቸውን ዕድል በአግባቡ መጠቀም እንደሚገባቸው አስገንዝበዋል። በመርሀግብሩ የአዲስ አበባ ቤቶች ልማትና አስተዳደር ቢሮ እና ከህብረት ስራ ኮሚሽን መምህራኑ በህብረት ስራ ማህበራቱ ለመደራጀት መከተል ስለሚገባቸው ቅድመ ሁኔታዎችና እስካሁን የተከናወኑ የቅድመ ዝግጅት ተግባራትን በተመለከተ የመወያያ ሰነድ ቀርቦ በተሳታፊዎች የተለያዩ አስተያየቶች የተሰጡ ሲሆን ለተነሱ ጥያቆዎች የአዲስ አበባ ቤቶች ልማትና አስተዳደር ቢሮ ጽህፈት ቤት ኃላፊ አቶ አብዲሳ አራርሳ፣ የህብረት ስራ ኮሚሽን ኮሚሽነር ሉሊት ግደይ እንዲሁም በመምህራን ማህበር ፕሬዘዳንት ድንቃለም ቶሎሳ እና በዶክተር ዘላለም ሙላቱ ምላሽ ተሰቷል። መረጃዎችን በፍጥነት ለማግኘት ማሰፈንጠሪያዎቹን ይጫኑ! What Sapp: - https://whatsapp.com/channel/0029VaHFiBpA2pLF0lLslK2D You Tube: https://www.youtube.com/@addisababaeducationbureau9728 TikTok፡- tiktok.com/@aaeducationbureau Telegram ፡ https://t.me/wwwAddisAbabaeducationbureau Twitter ፡ https://twitter.com/aacaebc Face book: https://www.facebook.com/aacityeducationcommunication Blog: - http://www.aacaebc.wordpress.com/ Website: - aaceb.gov.et Email;- aacaebc@gmail.com Instagram: - https://www.instagram.com/aacaeb/ 14.7K viewsAbebe Chernet, 09:07