የአዲስ አበባ ከተማ ወጣቶችና ስፖርት ቢሮ ኃላፊ አቶ በላይ ደጀን በበኩላቸው ትምህርት ቤቶች የነገ የሀገር ተረካቢ ዜጎችም ሆኑ ተተኪ ስፖርተኞች የሚፈሩባቸው ተቋማት እንደመሆናቸው ቢሮው ከአዲስ አበባ ትምህርት ቢሮ ጋር በጋራ በመሆን በትምህርት ቤቶች የሚገኙ የማዘውተሪያ ስፍራዎችን በማስፋፋትም ሆነ በተማሪዎችና መምህራን መካከል ስፖርታዊ ውድድሮችን በማካሄድ ላይ እንደሚገኝ ገልጸው በቀጣይ በሁሉም ትምህርት ቤቶች የሚካሄደው የማለዳ ስፖርታዊ እንቅስቃሴ ተጠናክሮ እንዲቀጥልና የስፖርት ሳይንስ መምህራን ሙያዊ ክህሎታቸውን የሚያሳድጉበት ስልጠና እንዲያገኙ በትኩረት የሚሰራ መሆኑን አስታውቀዋል፡፡ በመርሀ ግብሩ የአዲስ አበባ ከተማ ወጣቶችና ስፖርት ቢሮ ምክትል ቢሮ ኃላፊ አቶ ዳዊት ትርፉ ባለፉት ሁለት አመታት ሁለቱ ቢሮዎች በጋራ ያከናወኑዋቸው እና በቀጣይ ትኩረት የሚደረግባቸውን ተግባራት አቅርበዋል፡፡ መረጃዎችን በፍጥነት ለማግኘት ማሰፈንጠሪያዎቹን ይጫኑ! What Sapp: - https://whatsapp.com/channel/0029VaHFiBpA2pLF0lLslK2D You Tube: https://www.youtube.com/@addisababaeducationbureau9728 TikTok፡- tiktok.com/@aaeducationbureau Telegram ፡ https://t.me/wwwAddisAbabaeducationbureau Twitter ፡ https://twitter.com/aacaebc Face book: https://www.facebook.com/aacityeducationcommunication Blog: - http://www.aacaebc.wordpress.com/ Website: - aaceb.gov.et Email;- aacaebc@gmail.com Instagram: - https://www.instagram.com/aacaeb/ 14.5K viewsAbebe Chernet, 13:52