2022-08-23 00:04:18
“የዘንድሮው ሀገር አቀፍ የ12ኛ ክፍል ፈተና ተሰርቆ ወጥቷል” ከሚል ፅሁፍ ጋር በስፋት የተጋራው ምስል በቅንብር የቀረበ ነው።
የትምህርት ምዘናና ፈተናዎች አገልግሎት ዋና ዳይሬክተር እሸቱ ከበደ (ዶ/ር)
“የዘንድሮው ሀገር አቀፍ የ12ኛ ክፍል ፈተና ተሰርቆ ወጥቷል” የሚል መረጃ በማህበራዊ ትስስር ገፆች መሰራጨቱ ብዥታን ፈጥሯል።
ጉዳዩን በተመለከተ አስተያየታቸውን የሰጡት የትምህርት ምዘናና ፈተናዎች አገልግሎት ዋና ዳይሬክተር እሸቱ ከበደ (ዶ/ር) የተሰራጨው መረጃ ሀሠተኛ መሆኑን ገልጸዋል።
“የዘንድሮ” ነው ተብሎ የተጋራው የፈተና ቡክሌት በ2013/14 (2021) ዓ.ም የተሰጠ እንደሆነ ለኢትዮጵያ ቼክ አረጋግጠዋል።
በ2013/14 (2021) ዓ.ም የተሰጠ የኬሚስትሪ ፈተናም በተመሳሳይ ሁኔታ ዓመቱ ኤዲት ተደርጎ ሲሰራጭ መመልከታቸውን ዋና ዳይሬክተሩ ተናግረዋል።
"ተፈታኝ ተማሪዎች በማህበራዊ ሚዲያ የሚሰራጩ መሰል መረጃዎችን ከማመናቸው በፊት የአሰራጩን ታማኝነት እንዲያጣሩና ትክክለኛነቱን እንዲመረምሩ"
ዋና ዳይሬክተሩ መክረዋል።
የአገር አቀፍ ፈተናን የተመለከቱ ሀሠተኛ መረጃ የሚያሰራጩ አካላት “ፖለቲካን ከታዳጊዎች ህይዎት ቢለዩ መልካም ነው” ሲሉ ኃላፊው አሳስበዋል።
@wellaptop
3.7K views𝐖𝐞𝐥𝐥 𝐨𝐰𝐧𝐞𝐫 G, 21:04