#ወግ_ብቻ #ናፍቆትህ ናፍቆኛል. . ትዝታዬ . " . . . ወሰን አልባው ፍቅርሽ ፣ ጠብቆኝ በስስት ፣ አድርጎኛልና መንገዴን እንዳልስት። ለአንኳኳለት ሁሉ ልቤ አይከፈትም ፣ እንኳንስ አካሌ ሃሳቤ አይሸፍትም።. . . .. . . . " ይኼን ሙዚቃ እንደ ዛሬ ብቻዬን ሳልቆዝምበት በፊት………ጮክ ብለን ዘፍነነዋል . . . ተለጣጥፈን አዳምጠነዋል. . . ተገባብዘነዋል. . . ትዝታ ፅፈንበታል. . . . . ያኔ …… ጥር ከመግባቱ በፊት ሳውቀው. . . "ምወደው ጫካ አለ" አለኝ የመጀመርያ የአብሮነት ምሳችንን እየበላን ነበር. . . "ትወስደኛለህ " "ከፈለግሽ ደስ ይለኛል " ካለንበት ዕሮብ ለቀጣዩ ዕሮብ አቀድን. . . ፍቅሩን አንዴ ነው የጠጣሁት ለዚህም ነው አሁንም እንደ አማልክት ምኖረው. . . የዓለምን ምስጢር የገለጠልኝ እውነት ነበር. . . ሚሆነውም እሱ ነው. . አስፈሪው ጫካውን ሲያሳየኝ አልፈራውም ፣ አልደነገጥኩም. . . . አልተጨነኩም. . . . ነፍሴ ስትዘል . . . ስታመሰግን አየዋት . . . ያኔ ነው ያፈቀረችው መሰለኝ . . አክብራው ስታጎነብስ አይቻታለው. . . ነፃነቷን ሰቷት ነበር እና. . . . ከዛ ቀን በኃላ ከንፈናል . . . ያለሱ ሚታየኝ ውበት፣ የሚጣፍጠኝ ስም አጣው. . . በረርኩ . . ልቡ ውስጥ ፣ ነፍሱ ውስጥ ፣ አዕምሮው ውስጥ . . በፍቅር ፈቀደልኝ. . . ለኔ ደክሞት ፣ሰንፎ አያውቅም. . . ያፈቅረኛል!! ፍቅሩን መላው አካላቱ ይናገራሉ. . . ሊመሽ ሲል ከመለያየታችን በፊት መንገድ ዳር ሻይ እንጠጣለን. . . እኔ ችፕስ ወዳለው . . . እሱ ጨጓራውን ያመዋል . . . ቢሆንም ይበላልኛል. . .ቦታውን ወዶት እኮ አደለም ሚቀመጥልኝ እኔ ስላልኩት ነው. . . . ማይወደውን ፣ ማይፈልገውን ሁሉ ለኔ ፣ ለፍቅራችን ሲል ፈልጎት ነበር . . * * * ዛሬ………… ደክሞት ፣ ደክሞኝ ጠፍተናል. . . የዘረጋነውን እውነት በመቆሳሰል ደብቀነዋል. . . ያቀፈኝ ክንዱ ተሰብስቦዋል ፣ ጥጉ ፣ ጥጌ ላይ ነኝ. . . ህልሞቻችን ከቀኖቻችን ጋር ተኳርፈዋል . . . የራሱ ልብ ውስጥ ፣ የራሴ ነፍስ ውስጥ ተወታትፈናል. . . . ደምኖብናል . . . እራሴን ጠይቃለው " ፍቅራችን እውነት አበቃ ?" ይቆጨኛል. . . ሚቆጨኝ ስለሌለ ሳይሆን ያልነገርኩት ስላለ ነው. . . "ያልኖርኩልክ የቀረኝ ሂወት አለኝ. . . ያላሳየሁክ ያልሆንኩልክ እውነት አለኝ ፣ ውሃን ልወልድልህ ፈልጋለው ፣ እስከ እድሜዬ አመሻሽ አንተን ነው ምፈልገው ፣ እንደ ደነስናቸው ዳንሶች ፣ እንደነበሩን ፀሃይና ጨረቃ ፣እደተሳሙት ከንፈሮቻችን ፣ እደተራመድንባቸው ጓዳናዎች ፣ እዳለቀስንበት ምሽት ፣በጅብ እንደፈራንበት ቀን ፣ እንደ ደበደበን ዝናብ ፣ እዳቃጠለን ሀሩር ፣ እንደ ጉርሻችን ፣ እንደ ሰጠከኝ አበቦች . . ተው ትዝታ አንሁን . . " ልለው ፈልጋለው! "ከአንተ ጋር የአንዲት ሰዓት ሐሴት ዘላለማዊ ውድ ቅርፅ ነው።. . . ፍቅራችን ከዘመናት በፊት የጠፋውን ማሙዝ እንዲሆን አልፈልግም. . . የሳትነውን መንገድ እንመለስበት፣ ኑርልኝ፣ ልኑርልህ ፣ ና ፣ ልምጣ " ልለው እፈልጋለው . . . . ግን አልለውም አንዳንድ እውነቶች መነገር አይፈልጉም ፣ ቁጭትን እየወለዱ ቢሆን እንኳን በመደበቅ ይፀናሉ. . . ቢሆንም ናፍቆትህ ዝም ብሎ ይናፍቀኛል ፣ ናፍቆ ያሰኘኛል. . . እንዳልመጣም ፣ እንድመጣም ይመክረኛል!! /ትዝታ / |❀:✧๑♡๑✧❀| @wegoch @wegoch @wegoch 7.7K viewsC-ራክ, edited 10:49