Get Mystery Box with random crypto!

ቱንቢ ላቭ ሚዲያ 💟

የቴሌግራም ቻናል አርማ tunbi_love_media — ቱንቢ ላቭ ሚዲያ 💟
የቴሌግራም ቻናል አርማ tunbi_love_media — ቱንቢ ላቭ ሚዲያ 💟
የሰርጥ አድራሻ: @tunbi_love_media
ምድቦች: ሃይማኖት
ቋንቋ: አማርኛ
ተመዝጋቢዎች: 2.69K
የሰርጥ መግለጫ

"፤ እግዚአብሔርም፦ አሞጽ ሆይ፥ የምታየው ምንድር ነው? አለኝ። እኔም፦ ቱንቢ ነው አልሁ። ጌታም፦ እነሆ፥ በሕዝቤ በእስራኤል መካከል ቱንቢ አደርጋለሁ፤ ከእንግዲህም ወዲህ ደግሞ አላልፋቸውም፤" (ትንቢተ አሞጽ 7: 8)
______________
ለማንኛውም ሀሳብና አስተያነት ✍️
📞 251 932000657 ወይም
በቴሌግራም @byitref ያገኙናል::

Ratings & Reviews

3.67

3 reviews

Reviews can be left only by registered users. All reviews are moderated by admins.

5 stars

0

4 stars

2

3 stars

1

2 stars

0

1 stars

0


የቅርብ ጊዜ መልዕክቶች 3

2022-06-27 19:08:17 #ሚስዮናዊነት


ደህንነትን በእርግጥ አግኝተናል ወይስ ደህንነት የሚመስለውን ቅብ ነው ያገኘነው??? ዛሬ ቱንቢያችንን በደህንነታችን ላይ ጥለን እንለካለን
ከመንፈስ ቅዱስ ጋርም ትክክለኛውን ቤት እንሰራለን

በፍጥረት መጀመሪያ ላይ ሰውን ሲፈጥር የነበረውን መልክ በኃጢአት ምክንያት ጠፋ፤ ያንን መልክ ለመመለስ ለተመረጠው ህዝብ ሕግ ተሰጠ። ሕግን በራስ አቅምና ችሎታ ለመፈፀም ግን በጣም ከባድ ሆነ ሕጉ ወደ እግዚአብሔር ከማስጠጋት ይልቅ ኃጢአትን በደንብ እንዲያውቁ አደረገ። ከዚያም መሲሁን ክርስቶስን ወደ ምድር ሰው ሆኖ በመገለጥ ሕግን ሁሉ በመፈፀም ኃጢአትን አሸነፈ። እዚህ ጋር ነው እንግዲህ ማስተዋል ያለብን; ኢየሱስ ክርስቶስ ሕግን ሁሉ ፈፀመ ስንል ሻረልን (ከሕግ በላይ) ሆንን ህግን መጠበቅ አይጠበቅብንም ማለት አይደለም። ይልቁንስ ሊያጠፋን የሚችለውን ኃጢአትን ማሸነፍ የምችልበትን ሕግን ሁሉ መፈፀም የሚያስችለውን #ፀጋ በመንፈሱ አማካኝነት አለበሰን ሕጉንም አጠበቀው። እንኳን ህግን ሻረ ልንል ይልቁንም አጠበቀው ምክንያቱ ደግሞ በፊት አታመንዝር ያለው አሁን ግን ያየ የተመኘ ኃጢአተኛ ነው አለ: ባልንጀራችሁን ውደዱ ያለው የሚጠሉአችሁን ውደዱ አለ፤ ግን ህጉን ብቻ ሰቶን ራሳችሁ ተወጡት አላለንም ማድረግም የምንችልበትንም #ፀጋ ሰጠን።

እግዚአብሔር ኃጢአትን ይጠላል፤ ይቀጣልም። አንዴ አምኜ ድኛለው ስለዚህ ኃጢአትን ብሰራ እንኳን (Continuously) የደህንነት አክሊሌን አላጣም" በሚል እምነት ዋናቸውን ይነጥቃቸዋል። ይሄንንም እውነት እንዲመስል የወልድን ስራ በጣም አልቆና አጉልቶ ያሳዩናል፤ እኔ አሁን ለደህንነቴ የምሰራው ስራ አይኖርም ኢየሱስ ሰርቶ ጨርሶልኛል ይላሉ ልክ ናቸው እኛ ለመዳን ማመን ብቻ ነው የሚጠበቅብን ከዳንን በኃላ ግን እንድንቀደስና እንደሚገባ እንድንኖር መንፈስ ቅዱስን ሰጥቶናል። መንፈስ ቅዱስ እኛን ገና ሰርቶን አልጨረሰንም ደህንነታችን አላለቀም። (ኤፌ 2፥21-22)

#የክርስቶስ_ፀጋ ሕግን መፈፀም እንድንችል ይረዳናል።ፀጋው በክርስቶስ አምነን፣ ኃጢአትን ክደን ፣ ተቀድሰን ወደ እግዚአብሔር እንድንቀርብ ያደርገናል።
ቲቶ 2
¯¯¯¯¯¯¯¯¯¯
¹¹ ሰዎችን ሁሉ የሚያድን የእግዚአብሔር ጸጋ ተገልጦአልና፤
¹²-¹³ ይህም ጸጋ፥ ኃጢአተኝነትንና ዓለማዊን ምኞት ክደን፥ የተባረከውን ተስፋችንን እርሱም የታላቁን የአምላካችንንና የመድኃኒታችንን የኢየሱስ ክርስቶስን ክብር መገለጥ እየጠበቅን፥ ራሳችንን በመግዛትና በጽድቅ እግዚአብሔርንም በመምሰል በአሁኑ ዘመን እንድንኖር ያስተምረናል፤

#ፀጋው ኃጢአትን እንዳናደርግ ብቻም ሳይሆን መልካም ነገርን እንድናደርግ ያግዘናል። “እንግዲህ በጎ ለማድረግ አውቆ ለማይሠራው ኃጢአት ነው።”
— ያዕቆብ 4፥17
ይህ ፀጋ እምነታችንን በስራ እንድንተገብር ያደርጋል።እምነትና ስራ ተነጥለው የሚታዩ አይደሉም።
ያዕቆብ 2
¯¯¯¯¯¯¯¯¯¯
¹⁷ እንደዚሁም ሥራ የሌለው እምነት ቢኖር በራሱ የሞተ ነው።
¹⁸ ነገር ግን አንድ ሰው፦ አንተ እምነት አለህ እኔም ሥራ አለኝ፤ እምነትህን ከሥራህ ለይተህ አሳየኝ፥ እኔም እምነቴን በሥራዬ አሳይሃለሁ ይላል።
ስለዚህ ሊገባን የሚገባው ነገር እምነታችን ስራም አለው፤ ኃጢአትን ክደን ኃጢአተኛ ሆኖ መቀጠል አያድንም። እግዚአብሔር በምንም ሁኔታ ለኃጢአት ስፍራ ኖሮት አያውቅም የለውምም። ነፍሴና መንፈሴ ድነዋል በስጋዬ ኃጢአት ብሰራ Nothing አይባልም በውስጣችን ያለው መንፈስ ቅዱስ አንዱን ከአንዱ ነጥሎ አይቀድስም!“የሰላምም አምላክ ራሱ ሁለንተናችሁን ይቀድስ፤ መንፈሳችሁም ነፍሳችሁም ሥጋችሁም ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ በመጣ ጊዜ ያለ ነቀፋ ፈጽመው ይጠበቁ።” — 1ኛ ተሰሎንቄ 5፥23

#ሁለት_ነገሮችን_እናስተውል!!
፩. ኢየሱስ ሕግን ፈፅሞልናል ኃጢአት ብንሰራም አንዴ አምነናልና ደህንነታችን አይጠፋም ማለት እምነትን ከስራ ለይተን ለማሳየት መሞከርና የፀጋውን ባለጠግነት ማሳነስ ነው።
ማቴዎስ 7
¯¯¯¯¯¯¯¯¯¯
²¹ በሰማያት ያለውን የአባቴን ፈቃድ የሚያደርግ እንጂ፥ ጌታ ሆይ፥ ጌታ ሆይ፥ የሚለኝ ሁሉ መንግሥተ ሰማያት የሚገባ አይደለም።
²² በዚያ ቀን ብዙዎች፦ ጌታ ሆይ፥ ጌታ ሆይ፥ በስምህ ትንቢት አልተናገርንምን፥ በስምህስ አጋንንትን አላወጣንምን፥ በስምህስ ብዙ ተአምራትን አላደረግንምን? ይሉኛል።
²³ የዚያን ጊዜም፦ ከቶ አላወቅኋችሁም፤ እናንተ ዓመፀኞች፥ ከእኔ ራቁ ብዬ እመሰክርባቸዋለሁ።
፪. የፀጋውን ጉልበት ተረድተን ግን ደግሞ ስፍራ ያልሰጠን ደግሞ በተሰጠን ፀጋ መልካም ነገሮችን ለማድረግ መጣጣር እንጀምር። ፀጋው አድኖናል ደግሞም ያድነናል።

JOIN JOIN JOIN
------------------------------------
@TUNBI_LOVE_MEDIA
@TUNBI_LOVE_MEDIA
------------------------------------
306 viewsMeti Mulugeta, 16:08
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-06-27 07:11:24
የማለዳ መና ቀን 20-10-2014E.C
ማቴዎስ 6
¯¯¯¯¯¯¯¯¯¯
¹⁴ ለሰዎች ኃጢአታቸውን ይቅር ብትሉ፥ የሰማዩ አባታችሁ እናንተን ደግሞ ይቅር ይላችኋልና፤
¹⁵ ለሰዎች ግን ኃጢአታቸውን ይቅር ባትሉ፥ አባታችሁም ኃጢአታችሁን ይቅር አይላችሁም።
¹⁶ ስትጦሙም፥ እንደ ግብዞች አትጠውልጉ፤ ለሰዎች እንደ ጦመኛ ሊታዩ ፊታቸውን ያጠፋሉና፤ እውነት እላችኋለሁ፥ ዋጋቸውን ተቀብለዋል።
¹⁷-¹⁸ አንተ ግን ስትጦም፥ በስውር ላለው አባትህ እንጂ እንደ ጦመኛ ለሰዎች እንዳትታይ ራስህን ተቀባ ፊትህንም ታጠብ፤ በስውር የሚያይ አባትህም በግልጥ ይከፍልሃል።
¹⁹ ብልና ዝገት በሚያጠፉት ሌቦችም ቆፍረው በሚሠርቁት ዘንድ ለእናንተ በምድር ላይ መዝገብ አትሰብስቡ፤
²⁰ ነገር ግን ብልም ዝገትም በማያጠፉት ሌቦችም ቆፍረው በማይሠርቁት ዘንድ ለእናንተ በሰማይ መዝገብ ሰብስቡ፤
²¹ መዝገብህ ባለበት ልብህ ደግሞ በዚያ ይሆናልና።
²² የሰውነት መብራት ዓይን ናት። ዓይንህ እንግዲህ ጤናማ ብትሆን፥ ሰውነትህ ሁሉ ብሩህ ይሆናል፤
²³ ዓይንህ ግን ታማሚ ብትሆን፥ ሰውነትህ ሁሉ የጨለመ ይሆናል። እንግዲህ በአንተ ያለው ብርሃን ጨለማ ከሆነ፥ ጨለማውስ እንዴት ይበረታ!
²⁴ ለሁለት ጌቶች መገዛት የሚቻለው ማንም የለም፤ ወይም አንዱን ይጠላል ሁለተኛውንም ይወዳል፤ ወይም ወደ አንዱ ይጠጋል ሁለተኛውንም ይንቃል፤ ለእግዚአብሔርና ለገንዘብ መገዛት አትችሉም።

---------------------
@TUNBI_LOVE_MEDIA
@TUNBI_LOVE_MEDIA
------------------------
353 viewsMeti Mulugeta, 04:11
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-06-25 07:15:15
የማለዳ መና ቀን 18-10-2014E.C
መክብብ 11
¯¯¯¯¯¯¯¯¯¯
¹ እንጀራህን በውኃ ፊት ላይ ጣለው፥ ከብዙ ቀን በኋላ ታገኛዋለህና።
² ለሰባት ደግሞም ለስምንት እድል ፈንታን ክፈል፥ በምድር ላይ የሚሆነውን ክፉ ነገር ምን እንደሆነ አታውቅምና።
³ ደመናት ዝናብ በሞሉ ጊዜ በምድር ላይ ያፈስሱታል፤ ዛፍም ወደ ደቡብ ወይም ወደ ሰሜን ቢወድቅ፥ ዛፉ በወደቀበት ስፍራ በዚያ ይኖራል።
⁴ ነፋስን የሚጠባበቅ አይዘራም፥ ደመናንም የሚመለከት አያጭድም።
⁵ የነፋስ መንገድ እንዴት እንደ ሆነች አጥንትም በእርጉዝ ሆድ እንዴት እንድትዋደድ እንደማታውቅ፥ እንዲሁም ሁሉን የሚሠራውን የእግዚአብሔርን ሥራ አታውቅም።
⁶ ወይም ይህ ወይም ያ ማናቸው እንዲበቅል ወይም ሁለቱ መልካም እንዲሆኑ አታውቅምና በማለዳ ዘርህን ዝራ፥ በማታም እጅህን አትተው።
⁷ ብርሃን ጣፋጭ ነው ፀሐይንም ማየት ለዓይን መልካም ነው።
⁸ ሰው ብዙ ዘመን በሕይወት ቢኖር በሁሉም ደስ ይበለው፤ ሆኖም የጨለማውን ዘመን ያስብ፥ ብዙ ቀን ይሆናልና። የሚመጣው ነገር ሁሉ ከንቱ ነው።
⁹ አንተ ጐበዝ፥ በጕብዝናህ ደስ ይበልህ፥ በጕብዝናህም ወራት ልብህን ደስ ይበለው፥ በልብህም መንገድ ዓይኖችህም በሚያዩት ሂድ፤ ዳሩ ግን ስለዚህ ነገር ሁሉ እግዚአብሔር ወደ ፍርድ እንዲያመጣህ እወቅ።
¹⁰ ሕፃንነትና ጕብዝና ከንቱዎች ናቸውና ከልብህ ኀዘንን አርቅ፥ ከሰውነትህም ክፉን ነገር አስወግድ።
-----------------------
@TUNBI_LOVE_MEDIA
@TUNBI_LOVE_MEDIA
-----------------------
434 viewsMeti Mulugeta, 04:15
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-06-23 07:46:50
የማለዳ መና ቀን 16-10-2014
ናሆም 1
¯¯¯¯¯¯¯¯¯¯
² እግዚአብሔር ቀናተኛና ተበቃይ አምላክ ነው፤ እግዚአብሔር ተበቃይና መዓትን የተሞላ ነው፤ እግዚአብሔር ተቃዋሚዎቹን ይበቀላል፥ ለጠላቶቹም ቍጣውን ይጠብቃል።
³ እግዚአብሔር ትዕግሥተኛ፥ ኃይሉም ታላቅ ነው፥ በደለኛውንም፦ ንጹሕ ነህ አይልም፤ እግዚአብሔር በወጀብና በዐውሎ ነፋስ ውስጥ መንገድ አለው፥ ደመናም የእግሩ ትቢያ ነው።
⁴ ባሕሩንም ይገሥጻታል፥ ያደርቃትማል፥ ወንዞችንም ሁሉ ያደርቃል፤ ባሳንና ቀርሜሎስም ላልተዋል፥ የሊባኖስም አበባ ጠውልጎአል።
⁵ ተራሮችም ከእርሱ የተነሣ ታወኩ፥ ኮረብቶችም ቀለጡ፤ ምድርና ዓለም የሚኖሩበትም ሁሉ ከፊቱ ተናወጡ።
⁶ በቍጣው ፊት የሚቆም ማን ነው? የቍጣውንም ትኵሳት ማን ይታገሣል? መዓቱ እንደ እሳት ይፈስሳል፥ ከእርሱም የተነሣ ዓለቶች ተሰነጠቁ።
⁷ እግዚአብሔር መልካም ነው፥ በመከራ ቀንም መሸሸጊያ ነው፤ በእርሱ የሚታመኑትንም ያውቃል።

---------------------------
@TUNBI_LOVE_MEDIA
@TUNBI_LOVE_MEDIA
----------------------------
431 viewsMeti Mulugeta, 04:46
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-06-22 08:00:26
የማለዳ መና ቀን 15-10-2014E.C
ምሳሌ 4
¯¯¯¯¯¯¯¯¯¯
¹ እናንተ ልጆች፥ የአባትን ተግሣጽ ስሙ፥ ማስተዋልንም ታውቁ ዘንድ አድምጡ፤
² መልካም ትምህርትን እሰጣችኋለሁና፤ ሕጌን አትተዉ።
³ እኔም አባቴን የምሰማ ልጅ ነበርሁና፥ በእናቴም ዘንድ እወደድ ነበር።
⁴ ያስተምረኝም ነበር እንዲህም ይለኝ ነበር፦ ልብህ ቃሌን ይቀበል፤ ትእዛዜን ጠብቅ በሕይወትም ትኖራለህ።
⁵ ጥበብን አግኝ፤ ማስተዋልን አግኝ፤ አትርሳም፥ ከአፌም ቃል ፈቀቅ አትበል።
⁶ አትተዋት፥ ትደግፍህማለች፤ ውደዳት፥ ትጠብቅህማለች።
⁷ ጥበብ ዓይነተኛ ነገር ናትና ጥበብን አግኝ፤ ከሀብትህም ሁሉ ማስተዋልን አትርፍ።
⁸ ከፍ ከፍ አድርጋት፥ እርስዋም ከፍ ከፍ ታደርግሃለች፤ ብታቅፋትም ታከብርሃለች።
⁹ ለራስህ የሞገስ አክሊልን ትሰጥሃለች፥ የተዋበ ዘውድንም ታበረክትሃለች።
¹⁰ ልጄ ሆይ፥ ስማ፥ ንግግሬንም ተቀበል፤ የሕይወትህም ዘመን ትበዛልሃለች።
¹¹ የጥበብን መንገድ አስተማርሁህ፤ በቀናች ጎዳና መራሁህ።
¹² በሄድህ ጊዜ እርምጃህ አይጠብብም፤ በሮጥህም ጊዜ አትሰናከልም።
¹³ ተግሣጽን ያዝ፥ አትተውም፤ ጠብቀው፥ እርሱ ሕይወትህ ነውና።
¹⁴ በኃጥኣን መንገድ አትግባ፥ በክፉ ሰዎችም ጎዳና አትሂድ።
¹⁵ ከእርስዋ ራቅ፥ አትሂድባትም፤ ፈቀቅ በል ተዋትም።
¹⁶ ክፉ ካላደረጉ አይተኙምና፥ ካላሰናከሉም እንቅልፋቸው ይወገዳልና።
¹⁷ የኃጢአትን እንጀራ ይበላሉና፥ የግፍንም ወይን ጠጅ ይጠጣሉና።
¹⁸ የጻድቃን መንገድ ግን እንደ ንጋት ብርሃን ነው፥ ሙሉ ቀን እስኪሆንም ድረስ እየተጨመረ ይበራል።
-----------------------
@TUNBI_LOVE_MEDIA
@TUNBI_LOVE_MEDIA
-----------------------
401 viewsMeti Mulugeta, 05:00
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-06-20 19:13:04 #ሚስዮናዊነት

ወንጌል የገባውና ጌታን ተቀበለ የምንለው ሰው የህይወቱ ትኩረት ምንድነው?? እናም ወንጌል በህይወቱ ላይ ማምጣት የሚገባው የህይወት ለውጥ መርሆች እንዴት መሆን አለበት?
በመጀመሪያ ወንጌል የራሳችን ከመሆን አውጥቶ የጌታ ወደ መሆን፣ የራስን ፈቃድና ሀሳብ ከመፈፀም አውጥቶ ጌታዬ ብለን የተቀበልነውን አምላክ ፍቃድ ወደ መፈፀም መግባት ማለት ነው።
“ወይስ ሥጋችሁ ከእግዚአብሔር የተቀበላችሁት በእናንተ የሚኖረው የመንፈስ ቅዱስ ቤተ መቅደስ እንደ ሆነ አታውቁምን? በዋጋ ተገዝታችኋልና ለራሳችሁ አይደላችሁም፤ ስለዚህ በሥጋችሁ እግዚአብሔርን አክብሩ።”
— 1ኛ ቆሮንቶስ 6፥19-20
የበደለው ማንነቴን በክርስቶስ ደም ዋጋ ተከፍሎበት አሁን በክርስቶስ ፃድቅ ተብያለው። ፀድቀሀል ሲለኝ የሰራሁትን ኃጢአት በሙሉ እንዳልሰራክ ተደርጎ ተቆጥሮልሀል። ስለዚህ ዋጋ ከፍሎ ላፀደቀኝ ጌታ እገዛለታለው።
ለተገዛንለት ጌታ የምንኖረው ለእርሱ በመታዘዝ ነው። ለክርስቶስ በመታዘዝ ውስጥ እውነተኛ እምነትና ንሠሀ ልንገባ ይገባል። መንፈሳዊውም ሆነ ግብረገባዊ ኑሮዐችን ለጌታም ሆነ ለሰዎች በግልጥ መታየት አለበት። “በሰማያት ያለውን የአባቴን ፈቃድ የሚያደርግ እንጂ፥ ጌታ ሆይ፥ ጌታ ሆይ፥ የሚለኝ ሁሉ መንግሥተ ሰማያት የሚገባ አይደለም።”
— ማቴዎስ 7፥21
ክርስቶስን ከመቀበላችን በፊት የነበሩን ባህሪያቶቻችን በሙሉ በጌታ ፊት ተቀባይነት የሌለው ከሆነ መተውና በቃሉ ባህሪያችንን መቅረፅ አለብን። ለምሳሌ አንዳንድ ሰው እኔ ሰውን ይቅርታ መጠየቅ አልወድም ፣ቶሎ ቁጣ የሚቀናው ሰው....ብቻ ባህሪዬ ነው በሚል አጉል አባባል መጥፎ ባህርያቸውን እያባበሉ የሚኖሩ አሉ። ይሄ አይነት የወንጌል ተቃራኒ አመለካከቶችን ሁሉ በጌታ ፍቃድና ባህሪ መለወጥ አለባቸው። ባህሪዬ ነው ብዬ የተቀበልኩት መጥፎ አስተሳሰቤ ከተቀበልኩት ጌታ ጋር የሚጋጭ ከሆነ ሚዛኔ ልክ አይደለም ማለት ነው። ስለዚህ በንሰሀ በመመለስ ያልተገራውን ባህርይ በቃሉ መግራት ተገቢ ነው። መንፈሳዊነት በቤተክርስቲያን መሰብሰቢያ አዳራሽና በህብረት ውስጥ ብቻ ወይም የምናሳየው ተግባር ብቻ አይደለም። መንፈሳዊነት church መድረክ ላይ ብቻ የምንጨርሰው ነገር ሳይሆን ዕለት ዕለት የምንኖረው ሕይወት ነው። ወንጌል በሁሉ ነገራችን ላይ የጌታን ፍቃድ ብቻ እንድንኖር ያደርጋል። የሰጠንን ትዕዛዙን ስንጠብቅም እንደወደድነው በዚያ እናውቃለን። “መልካሙን ሥራችሁን አይተው በሰማያት ያለውን አባታችሁን እንዲያከብሩ ብርሃናችሁ እንዲሁ በሰው ፊት ይብራ።”— ማቴዎስ 5፥16
“ትእዛዜ በእርሱ ዘንድ ያለችው የሚጠብቃትም የሚወደኝ እርሱ ነው፤ የሚወደኝንም አባቴ ይወደዋል እኔም እወደዋለሁ ራሴንም እገልጥለታለሁ።”
— ዮሐንስ 14፥21
1ኛ ዮሐንስ 5
¯¯¯¯¯¯¯¯¯¯
² እግዚአብሔርን ስንወድ ትእዛዛቱንም ስናደርግ የእግዚአብሔርን ልጆች እንድንወድ በዚህ እናውቃለን።
³ ትእዛዛቱን ልንጠብቅ የእግዚአብሔር ፍቅር ይህ ነውና፤ ትእዛዛቱም ከባዶች አይደሉም።

**ወንጌል_ያሸንፋል
---------------------------------------
@TUNBI_LOVE_MEDIA
@TUNBI_LOVE_MEDIA
----------------------------------------
414 viewsMeti Mulugeta, 16:13
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-06-20 19:12:35
343 viewsMeti Mulugeta, 16:12
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-06-20 07:51:22
የማለዳ መና ቀን 13-10-2014E.C
ዘፍጥረት 32
¯¯¯¯¯¯¯¯¯¯
²² በዚያች ሌሊትም ተነሣ፥ ሁለቱን ሚስቶቹንና ሁለቱን ባሪያዎቹን አሥራ አንዱንም ልጆቹን ወስዶ የያቦቅን ወንዝ ተሻገረ።
²³ ወሰዳቸውም ወንዙንም አሻገራቸው፥ ከብቱንም ሁሉ አሻገረ።
²⁴ ያዕቆብ ግን ለብቻው ቀረ፤ አንድ ሰውም እስከ ንጋት ድረስ ይታገለው ነበር።
²⁵ እንዳላሸነፈውም ባየ ጊዜ የጭኑን ሹልዳ ነካው፤ ያዕቆብም የጭኑ ሹልዳ ሲታገለው ደነዘዘ።
²⁶ እንዲህም አለው፦ ሊነጋ አቀላልቶአልና ልቀቀኝ። እርሱም፦ ካልባረክኸኝ አልለቅቅህም አለው።
²⁷ እንዲህም አለው፦ ስምህ ማን ነው? እርሱም፦ ያዕቆብ ነኝ አለው።
²⁸ አለውም፦ ከእንግዲህ ወዲህ ስምህ እስራኤል ይባል እንጂ ያዕቆብ አይባል፤ ከእግዚአብሔር ከሰውም ጋር ታግለህ አሸንፈሃልና።
²⁹ ያዕቆብም፦ ስምህን ንገረኝ ብሎ ጠየቀው። እርሱም፦ ስሜን ለምን ትጠይቃለህ? አለው። በዚያም ስፍራ ባረከው።
³⁰ ያዕቆብም፦ እግዚአብሔርን ፊት ለፊት አየሁ፥ ሰውነቴም ድና ቀረች ሲል የዚያን ቦታ ስም ጵኒኤል ብሎ ጠራው።
³¹ ጵኒኤልንም ሲያልፍ ፀሐይ ወጣችበት፥ እርሱም በጭኑ ምክንያት ያነክስ ነበር።
³² ስለዚህም የእስራኤል ልጆች እስከ ዛሬ ድረስ የወርችን ሹልዳ አይበሉም፤ የያዕቆብን ጭን ይዞ የወርችን ሹልዳ አደንዝዞአልና።

---------------------
@TUNBI_LOVE_MEDIA
@TUNBI_LOVE_MEDIA
------------------------
392 viewsMeti Mulugeta, 04:51
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-06-19 07:13:06
የማለዳ መና ቀን 12-10-2014E.C
1ኛ ሳሙኤል 12
¯¯¯¯¯¯¯¯¯¯
¹⁹ ሕዝቡም ሁሉ ሳሙኤልን፦ ንጉሥ በመለመናችን በኃጢአታችን ሁሉ ላይ ይህን ክፋት ጨምረናልና እንዳንሞት ስለ ባሪያዎችህ ወደ አምላክህ ወደ እግዚአብሔር ጸልይ አሉት።
²⁰ ሳሙኤልም ሕዝቡን አለ፦ አትፍሩ በእውነት ይህን ክፋት ሁሉ አደረጋችሁ፤ ነገር ግን እግዚአብሔርን በፍጹም ልባችሁ አምልኩት እንጂ እግዚአብሔርን ከመከተል ፈቀቅ አትበሉ።
²¹ ምናምንቴ ነውና የማይረባንና የማያድን ከንቱን ነገር ለመከተል ፈቀቅ አትበሉ።
²² እግዚአብሔር ለእርሱ ሕዝብ ያደርጋችሁ ዘንድ ወድዶአልና እግዚአብሔር ስለ ታላቅ ስሙ ሕዝቡን አይተውም።
²³ ደግሞ መልካሙንና ቅኑን መንገድ አስተምራችኋለሁ እንጂ ስለ እናንተ መጸለይን በመተው እግዚአብሔርን እበድል ዘንድ ይህ ከእኔ ይራቅ።
²⁴ ብቻ እግዚአብሔርን ፍሩ፥ ያደረገላችሁንም ታላቅ ነገር አይታችኋልና በፍጹም ልባችሁ በእውነት አምልኩት።
²⁵ ነገር ግን ክፉ ብትሠሩ እናንተም ንጉሣችሁም ትጠፋላችሁ።
-----------------------
@TUNBI_LOVE_MEDIA
@TUNBI_LOVE_MEDIA
-----------------------
397 viewsMeti Mulugeta, 04:13
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-06-07 23:33:20 Track 9
____________
@TUMBI_LOVE_MEDIA
@TUMBI_LOVE_MEDIA
673 viewsBêrêkêt YZ, 20:33
ክፈት / አስተያየት ይስጡ