Get Mystery Box with random crypto!

ቱንቢ ላቭ ሚዲያ 💟

የቴሌግራም ቻናል አርማ tunbi_love_media — ቱንቢ ላቭ ሚዲያ 💟
የቴሌግራም ቻናል አርማ tunbi_love_media — ቱንቢ ላቭ ሚዲያ 💟
የሰርጥ አድራሻ: @tunbi_love_media
ምድቦች: ሃይማኖት
ቋንቋ: አማርኛ
ተመዝጋቢዎች: 2.69K
የሰርጥ መግለጫ

"፤ እግዚአብሔርም፦ አሞጽ ሆይ፥ የምታየው ምንድር ነው? አለኝ። እኔም፦ ቱንቢ ነው አልሁ። ጌታም፦ እነሆ፥ በሕዝቤ በእስራኤል መካከል ቱንቢ አደርጋለሁ፤ ከእንግዲህም ወዲህ ደግሞ አላልፋቸውም፤" (ትንቢተ አሞጽ 7: 8)
______________
ለማንኛውም ሀሳብና አስተያነት ✍️
📞 251 932000657 ወይም
በቴሌግራም @byitref ያገኙናል::

Ratings & Reviews

3.67

3 reviews

Reviews can be left only by registered users. All reviews are moderated by admins.

5 stars

0

4 stars

2

3 stars

1

2 stars

0

1 stars

0


የቅርብ ጊዜ መልዕክቶች 2

2022-07-09 20:35:35
1.1K viewsBiniyam, 17:35
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-07-09 20:35:35
950 viewsBiniyam, 17:35
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-07-09 20:35:34 ሰላም ለእናንተ ይሁን...ዛሬ የኢድ አል አድሀ በዓል የሚከበርበት ቀን ነው...በዚህም ምክንያት ለሙስሊም ወንድሞቻችን የሚሆንና የወንጌል መልዕክትን የያዘ የእንኳን አደረሳችሁ መልዕክት እንልካለን።በምንጠቀመው social media በሙሉ ተጠቅመን በመላክ ለብዙዎች ወንጌልን የመስማትና የመዳን ምክንያት እንሆናለን...ጌታም የሚድኑትን ሰዎች ቁጥር ይጨምራል።
“እግዚአብሔርንም እያመሰገኑ በሕዝብ ሁሉ ፊት ሞገስ ነበራቸው። ጌታም የሚድኑትን ዕለት ዕለት በእነርሱ ላይ ይጨምር ነበር።”
— ሐዋርያት 2፥47
855 viewsBiniyam, 17:35
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-07-04 07:07:41
የማለዳ መና ቀን 27-10-2014E.C
ሐዋርያት 3
¯¯¯¯¯¯¯¯¯¯
¹¹ እርሱም ጴጥሮስንና ዮሐንስን ይዞ ሳለ፥ ሕዝቡ ሁሉ እየተደነቁ የሰሎሞን ደጅ መመላለሻ በሚባለው አብረው ወደ እነርሱ ሮጡ።
¹² ጴጥሮስም አይቶ ለሕዝቡ እንዲህ ሲል መለሰ፦ የእስራኤል ሰዎች ሆይ፥ በዚህ ስለ ምን ትደነቃላችሁ? ወይስ በገዛ ኃይላችን ወይስ እግዚአብሔርን በመፍራታችን ይህ ይመላለስ ዘንድ እንዳደረግነው ስለ ምን ትኵር ብላችሁ ታዩናላችሁ?
¹³ የአብርሃምና የይስሐቅ የያዕቆብም አምላክ፥ የአባቶቻችን አምላክ፥ እናንተ አሳልፋችሁ የሰጣችሁትንና ሊፈታው ቈርጦ ሳለ በጲላጦስ ፊት የካዳችሁትን ብላቴናውን ኢየሱስን አከበረው።
¹⁴ እናንተ ግን ቅዱሱን ጻድቁንም ክዳችሁ ነፍሰ ገዳዩን ሰው ይሰጣችሁ ዘንድ ለመናችሁ፥
¹⁵ የሕይወትንም ራስ ገደላችሁት፤ እርሱን ግን እግዚአብሔር ከሙታን አስነሣው፥ ለዚህም ነገር እኛ ምስክሮች ነን።
¹⁶ በስሙም በማመን ይህን የምታዩትንና የምታውቁትን የእርሱ ስም አጸናው፥ በእርሱም በኩል የሆነው እምነት በሁላችሁ ፊት ይህን ፍጹም ጤና ሰጠው።
¹⁷ አሁንም፥ ወንድሞቼ ሆይ፥ እናንተ እንደ አለቆቻችሁ ደግሞ ባለማወቅ እንዳደረጋችሁት አውቄአለሁ፤
¹⁸ እግዚአብሔር ግን ክርስቶስ መከራ እንዲቀበል አስቀድሞ በነቢያት ሁሉ አፍ የተናገረውን እንዲሁ ፈጸመው።
¹⁹-²⁰ እንግዲህ ከጌታ ፊት የመጽናናት ዘመን እንድትመጣላችሁ አስቀድሞም ለእናንተ የመረጠውን ኢየሱስ ክርስቶስን እንዲልክላችሁ፥ ኃጢአታችሁ ይደመሰስ ዘንድ ንስሐ ግቡ ተመለሱም።

---------------------
@TUNBI_LOVE_MEDIA
@TUNBI_LOVE_MEDIA
------------------------
269 viewsMeti Mulugeta, 04:07
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-07-03 21:07:15
#ከሀምሌ 2 እስከ ነሀሴ 28 የሚቆይ የአዳጊ ወጣቶች የክረምት ኘሮግራም።
__________
#በእነዚህ_ወቅቶች
የፀሎት ፤
የአምልኮ፤
የትምርህት እና
የጨዋታ ጊዜ ይኖረናል። የፀሎት ፤
ፕሮግራሞች የሚኖሩበት ቀናቶች
ሀሙስ ፣ አርብ እና ቅዳሜ ከ 9:00 እስከ 11:00 ይሆናል::
#አድራሻ - ደቡብ አዲስ አበባ መሰረተ ክርስቶስ ቤተክርስቲያን
263 viewsBêrêkêt YZ, edited  18:07
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-07-03 07:28:19
የማለዳ መና ቀን26-10-2014E.C
ዕንባቆም 3
¯¯¯¯¯¯¯¯¯¯
¹⁶ እኔ ሰምቻለሁ፥ ልቤም ደነገጠብኝ፤ ከድምፁ የተነሣ ከንፈሮቼ ተንቀጠቀጡ፤ መንቀጥቀጥ ወደ አጥንቶቼ ውስጥ ገባ፤ በስፍራዬ ሆኜ ተናወጥሁ፤ በሚያስጨንቁን ሕዝብ ላይ እስኪመጣ ድረስ የመከራን ቀን ዝም ብዬ እጠብቃለሁ።
¹⁷ ምንም እንኳ በለስም ባታፈራ፥ በወይንም ሐረግ ፍሬ ባይገኝ፥ የወይራ ሥራ ቢጐድል፥ እርሾችም መብልን ባይሰጡ፥ በጎች ከበረቱ ቢጠፉ፥ ላሞችም በጋጡ ውስጥ ባይገኙ፥
¹⁸ እኔ ግን በእግዚአብሔር ደስ ይለኛል፤ በመድኃኒቴ አምላክ ሐሤት አደርጋለሁ።
¹⁹ ጌታ እግዚአብሔር ኃይሌ ነው፤ እግሮቼን እንደ ዋላ እግሮች ያደርጋል፤ በከፍታዎችም ላይ ያስሄደኛል።
Hab 3 (NIV)
¯¯¯¯¯¯¯¯¯¯
¹⁷ Though the fig tree does not bud and there are no grapes on the vines, though the olive crop fails and the fields produce no food, though there are no sheep in the pen and no cattle in the stalls,
¹⁸ yet I will rejoice in the Lord, I will be joyful in God my Savior.
¹⁹ The Sovereign Lord is my strength; he makes my feet like the feet of a deer, he enables me to go on the heights. For the director of music. On my stringed instruments.
---------------
@TUNBI_LOVE_MEDIA
@TUNBI_LOVE_MEDIA
------------------
291 viewsMeti Mulugeta, 04:28
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-07-01 22:09:29
ቅዱሳን በ Lord Good fellowship የተማሪዎች ህብረት የተዘጋጀ ድንቅ የትምህርት እና የፀሎት ፕሮግራም ተዘጋጅቷል የምትችሉ ሁሉ እንድትገኙ በጌታ ፍቅር ጋብዘናል::
____
ማክሰኞ
ሰኔ 28
ከ9:3
0 ጀም
#አድራሻ :- በሰሚት ሙሉ
ወንጌል ቤተ ክርስቲያን

@TUNBI_LOVE_MEDIA
@TUNBI_LOVE_MEDIA
318 viewsBêrêkêt YZ, edited  19:09
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-06-30 07:28:17
የማለዳ መና ቀን23-10-2014E.C
መዝሙር 63
¯¯¯¯¯¯¯¯¯¯
¹ አምላኬ፥ አምላኬ፥ ወደ አንተ እገሠግሣለሁ፤ ነፍሴ አንተን ተጠማች፥ ሥጋዬ አንተን እንዴት ናፈቀች እንጨትና ውኃ በሌለበት በምድረ በዳ።
² ኃይልህንና ክብርህን አይ ዘንድ እንዲሁ በመቅደስ ውስጥ ተመለከትሁህ።
³ ምሕረትህ ከሕይወት ይሻላልና ከንፈሮቼ ያመሰግኑሃል።
⁴ እንዲህ በሕይወቴ ዘመን አመሰግንሃለሁ፥ በአንተም ስም እጆቼን አነሣለሁ።
⁵ ነፍሴ በቅቤና በስብ እንደሚጠግቡ ትጠግባለች፥ ከንፈሮቼም ስምህን በደስታ ያመሰግናሉ።
⁶ በመኝታዬም አስብሃለሁ፥ በማለዳም እናገርልሃለሁ፤
⁷ ረዳቴ ሆነኸኛልና፥ በክንፎችህም ጥላ ደስ ይለኛልና።
⁸ ነፍሴ በኋላህ ተከታተለች፥ እኔንም ቀኝህ ተቀበለችኝ።
⁹ እነርሱ ግን ነፍሴን ለከንቱ ፈለጓት፤ ወደ ምድር ጥልቅ ይገባሉ።
¹⁰ ለሰይፍ እጅ አልፈው ይሰጣሉ፥ የቀበሮም እድል ፈንታ ይሆናሉ።
¹¹ ንጉሥ ግን በእግዚአብሔር ደስ ይለዋል፤ በእርሱ የሚምል ሁሉ ይከብራል፥ ሐሰትን የሚናገር አፍ ይዘጋልና።
---------------
@TUNBI_LOVE_MEDIA
@TUNBI_LOVE_MEDIA
------------------
378 viewsMeti Mulugeta, 04:28
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-06-29 08:53:46
የማለዳ መና ቀን 22-10-2014E.C
ኢሳይያስ 1
------
⁹ የሠራዊት ጌታ እግዚአብሔር ዘርን ባያስቀርልን ኖሮ፥ እንደ ሰዶም በሆንነ እንደ ገሞራም በመሰልነ ነበር።
¹⁰ እናንተ የሰዶም አለቆች ሆይ፥ የእግዚአብሔርን ቃል ስሙ፤ እናንተ የገሞራ ሕዝብ ሆይ፥ የአምላካችንን ሕግ አድምጡ።
¹¹ የመሥዋዕታችሁ ብዛት ለእኔ ምን ይጠቅመኛል? ይላል እግዚአብሔር፤ የሚቃጠለውን የአውራ በግ መሥዋዕትንና የፍሪዳን ስብ ጠግቤያለሁ፤ የበሬና የበግ ጠቦት የአውራ ፍየልም ደም ደስ አያሰኘኝም።
¹² በእኔ ፊት ልትታዩ ብትመጡ ይህን የመቅደሴን አደባባይ መርገጣችሁን ከእጃችሁ የሚሻ ማን ነው?
¹³ ምናምንቴውን ቍርባን ጨምራችሁ አታምጡ፤ ዕጣን በእኔ ዘንድ አጸያፊ ነው፤ መባቻችሁንና ሰንበታችሁን በጉባኤ መሰብሰባችሁን አልወድድም፤ በደልንም የተቀደሰውንም ጉባኤ አልታገሥም።
¹⁴ መባቻችሁንና በዓላቶቻችሁን ነፍሴ ጠልታለች ሸክም ሆነውብኛል፥ ልታገሣቸውም ደክሜያለሁ።
¹⁵ እጃችሁንም ወደ እኔ ብትዘረጉ ዓይኔን ከእናንተ እሰውራለሁ፥ ልመናንም ብታበዙ አልሰማችሁም፤ እጆቻችሁ ደም ተሞልተዋል።
¹⁶ ታጠቡ ሰውነታችሁንም አንጹ፤ የሥራችሁን ክፋት ከዓይኔ ፊት አስወግዱ፤ ክፉ ማድረግን ተዉ፥
¹⁷ መልካም መሥራትን ተማሩ፥ ፍርድን ፈልጉ፥ የተገፋውን አድኑ፥ ለድሀ አደጉ ፍረዱለት ስለ መበለቲቱም ተምዋገቱ።
¹⁸ ኑና እንዋቀስ ይላል እግዚአብሔር፤ ኃጢአታችሁ እንደ አለላ ብትሆን እንደ አመዳይ ትነጻለች፤ እንደ ደምም ብትቀላ እንደ ባዘቶ ትጠራለች።
¹⁹ እሺ ብትሉ ለእኔም ብትታዘዙ፥ የምድርን በረከት ትበላላችሁ፤
²⁰ እንቢ ብትሉ ግን ብታምፁም፥ ሰይፍ ይበላችኋል፤ የእግዚአብሔር አፍ ይህን ተናግሮአልና።

---------------------
@TUNBI_LOVE_MEDIA
@TUNBI_LOVE_MEDIA
------------------------
354 viewsMeti Mulugeta, 05:53
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-06-28 08:41:25
የማለዳ መና ቀን 21-10-2014E.C
2 ዜና 7
¯¯¯¯¯¯¯¯¯¯
¹¹ ሰሎሞንም የእግዚአብሔርን ቤትና የንጉሡን ቤት ጨረሰ፤ በእግዚአብሔር ቤትና በራሱ ቤት ይሠራው ዘንድ በልቡ ያሰበውን ሁሉ አከናወነ።
¹² እግዚአብሔርም ለሰሎሞን በሌሊት ተገልጦ እንዲህ አለው፦ ጸሎትህን ሰምቻለሁ፥ ይህንም ስፍራ ለራሴ ለመሥዋዕት ቤት መርጫለሁ።
¹³ ዝናብ እንዳይወርድ ሰማያቱን ብዘጋ፥ ወይም ምድሪቱን ይበላ ዘንድ አንበጣን ባዝዘው፥ ወይም በሕዝብ ላይ ቸነፈር ብሰድድ፥
¹⁴ በስሜ የተጠሩት ሕዝቤ ሰውነታቸውን አዋርደው ቢጸልዩ፥ ፊቴንም ቢፈልጉ፥ ከክፉ መንገዳቸውም ቢመለሱ፥ በሰማይ ሆኜ እሰማለሁ፥ ኃጢአታቸውንም ይቅር እላለሁ፥ ምድራቸውንም እፈውሳለሁ።
¹⁵ አሁንም በዚህ ስፍራ ለሚጸለይ ጸሎት ዓይኖቼ ይገለጣሉ፥ ጆሮቼም ያደምጣሉ።
¹⁶ አሁንም ስሜ ለዘላለም በዚያ ይኖር ዘንድ ይህን ቤት መርጫለሁ ቀድሻለሁም፤ ዓይኖቼና ልቤም ዘወትር በዚያ ይሆናሉ።
¹⁷ አንተም ደግሞ አባትህ ዳዊት እንደ ሄደ በፊቴ ብትሄድ፥ እንዳዘዝሁህም ሁሉ ብታደርግ፥ ሥርዓቴንና ፍርዴንም ብትጠብቅ፥
¹⁸ ከአባትህ ከዳዊት ጋር፦ በእስራኤል ላይ አለቃ፥ የሚሆን ከዘርህ አይታጣም ብዬ ቃል ኪዳን እንዳደረግሁ የመንግሥትህን ዙፋን አጸናለሁ።
-----------------------
@TUNBI_LOVE_MEDIA
@TUNBI_LOVE_MEDIA
-----------------------
328 viewsMeti Mulugeta, 05:41
ክፈት / አስተያየት ይስጡ