Get Mystery Box with random crypto!

--- ሽማግሌው ---- ግሩም ተበጀ ገና በጠዋቱ --- 2 : 30 ላይ . . . ክሊኒካችን | የተፃፉ ሃሳቦች•°•°•°•

--- ሽማግሌው

---- ግሩም ተበጀ

ገና በጠዋቱ --- 2 : 30 ላይ . . . ክሊኒካችን በህ
መምተኛ በተጨናነቀበት ወቅት ነበር አንድ አረጋ
ዊ ወደ ክሊኒካችን የገቡት። በግራ ክንዳቸው ላይ
የቁስል እሽግ ይታያል። በግምት 70 ዓመት የሚ
ሆናቸው አዛውንት ናቸው። በቀስታ አግዳሚው
ወንበር ላይ ተቀምጠው ሰዓታቸውን ማየት ጀመ
ሩ። የቸኮሉ ይመስላሉ።

"ምን ልርዳዎት" አልኳቸው።

የቀስሉ እሽግ እንዲቀየርላቸው ነው የመጡት።
ከ30 ደቂቃ በኃላ ግን ቀጠሮ ስላላቸው ቸኩለዋል

በህክምና ሊያገኙ የሚችሉት ገና ከ1 ሰዓት በኃላ
እንደሆነ ይገባኛል።ምን ማድረግ እችላለሁ! ግን
እስቲ ቢያንስ ቁስሉን ፈትቼ ልየው ብዬ እሽጉን
ስፈታው ቁስሉ ደርቋል።

በጣም ጥሩ!

ከአንዱ ዶክተርጋ ተነጋገሩክ።አስፈላጊውን መድኃ
ኒቶችና የህክምና የህክምና ቁሳቁሶች ወስጄ ህክ
ምናውን አከናወንኩላቸው። አረጋዊው ወደ ቀጠሯ
ቸው በጣም በመቸኮላቸው ምክንያት ትዕግስት
አጥተዋል።አሁንም የሚያዩት የእጅ ሰዓታቸው
ቁስሉ ያለበት ግራ ክንዳቸው ላይ ነው ያለው።
ስለዚህ እንዴት ሰዓታቸውን ይዩ . . .። ቁስሉን እየ
ፈታሁላቸው እሳቸው አሰግገው ሰዓታቸውን ለማየ
ት ይጣጣራሉ።

"ለመሆኑ ይሄ ያህል የቸኮሉበት ቀጠሮዎት የት
ነው . . ."አልኳቸው እንደ ጨዋታ ያህል።

"3 : 00 ሰዓት ላይ ከባለቤቴ ጋር ቁርስ ለመብላት
ቀጠሮ አለኝ" አሉኝ።

"አሀ . . ."

ቁስላቸውን መልሼ አያሸግኩላቸው አረጋዊው ታሪ
ካቸውን አጫወቱኝ። እንዳሉኝም እንዲህ የቸኮሉት
ከሚስታቸው ጋር 3 : 00 ሰዓት ላይ ቁርስ የመ
ብላት ቀጠሮ ስላላቸው ነው። ሚስታቸው ግን
ቤት አይደለም ያሉት።ህመምተኛ ናቸው። ሆስፒታ
ል ነው ያሉት።

"ባለቤትዎ ሀይለኛ ሴት ናቸው ማለት ነው . . ስለ
ዚህ ነው ላለማርፈድ ይሄን ያህል የቸኮሉት" አልኳ
ቸው።

"አይ . . . እሷ እንኳን ምንም አትለኝም"አሉኝ አረጋ
ዊው ፤ "እኔው ነኝ . . "

"እንዴት . . ." አልኳቸው እንዲጫወቱ ፈልጌ።

"አይ ልጄ ፣ ባለቤቴማ ላለፉት አምስት ዓመታት
አልዛይመር በተባለ የመርሳት በሽታ ተይዛ ባለቤ
ቷ እንደሆንኩ እንኳን አታውቅም" አሉኝ ትክዝ ብለ
ው።

ገረመኝ። አረጋዊው ላለፉት አምስት አመታት አን
ድም ቀን ሳያስተጓጉሉ ሆስፒታል እየሄዱ ከባለቤ
ታቸው ጋር ቁርስ ቆርሰዋል።ባለቤታቸው ግን
እያንዳንዱን ቀን ከተለያየ ሰው ጋር ቁርስ እንደበሉ
ነው የሚያውቁት።

ግማሽ ምዕተ ዓመት በዘለቀው ትዳራቸው . . .
የትዳር አጋራቸው የሆኑትን ባለቤታቸው ፈፅሞ
ረስተዋል። ምስኪኑ አረጋዊ ግን ሁልቀን ሳያረፍዱ
ሆስፒታል እየተገኘ ጨርሶ ከማያስታውሷቸው ባለ
ቤታቸው ጋር ፍቅርን ይቆርሳሉ።


ውብ አሁን

╭══•❀|❀:✧๑♡๑✧❀|❀: ══╮
@tsihofoch
@tsihofoch
╰══•ೋ•✧๑♡๑✧•ೋ ══╯