Get Mystery Box with random crypto!

የሺህ ዘመን ቀጠሮ ደራሲ - - - እሙሼ ክፍል - - - 'ፍስሃዬ አርፏ' ብላ ልት | የተፃፉ ሃሳቦች•°•°•°•

የሺህ ዘመን ቀጠሮ

ደራሲ - - - እሙሼ

ክፍል - - -


"ፍስሃዬ አርፏ" ብላ ልትቀጥል ስትል ንጉሱ አንገቷ
ን ጨምድዶ "ኖ ኖ ኖ!በፍፁም እዳትጨርሽው!ፍሰ
ሃ ይመጣል!"አለ አፍጥጦባት።

ዳንኤል በእግሮቹ ጫፍ ቁጢጥ ብሎ ተቀምጦ
አቀርቅሮ ማልቀስ ጀመረ። ድንጋጤ ከሸነቆራቸው
አይኖቹ የሚንጠባጠበው እንባ አዋራ ላይ እያረፈ
የአፈር ገንፎ የመሰለ የላቆጠ ጭቃ ይሰራል።

"አዎ ፍሰሃዬ ይቺን ቀን እንደናፈቀ አግኝቷችሁ ተቃ
ቅፎ ማልቀስ እንዳለመ ነው ለዘላለሙ ያሸለበው"
አለች ልጅቷ ስቅስቅ ብላ እያለቀሰች።


ኡሞጃ - ናይሮቢ - ኬንያ - 1998ዓ.ም

ፍሰሃ በጀርባው ከተኛበት ቀና ለማለት እየሞከረ
"እሺ በይኝ ሂጂ . . .እኔ ምንም አልሆንስልሽ። በኔ
ምክንያት ያንቺ ሂወት መበላሸት የለበትም። እባክ
ሽ እሺ በይኝ!" ከሚቆራረጥና ከሚያቃስት ድምፅ
የወጣ ልመና።

"ምናለበት ፀጥ ብለህ ራስህን ብታስታምመው!
አንተ በኔ ቦታ ብትሆን የማታደርገውን ነገር ለምን
እኔ እንዳደርገው ትጠይቀኛለህ !? አንተ ብትሆን
እኔ ታምሜ ትተህኝ ትሄድ ነበር!?"ሆድ ብሷት ማል
ቀስ ጀመረች።

"አንቺ ሴት ነሽ ለኔ ብለሽ እድልሽን ማበላሸት የለ
ብሽም። ይሄን እድል ካሳለፍሽ ሌላ እድል ለማግኘ
ት ብዙ ዓመት መጠበቅ አለብሽ።ለዛ ነው አይ ኦ
ኤም ሄደሽ ምርመራሽን አድርገሽ ሂጂ የምልሽ።"
ተናግሮ ሲጨርስ አቃስቶ በጀርባው ተዘረረ።

"ይሄውልህ ፀጥ ብለህ ተኛ ስልህ እምቢ ብለህ
አመመህ አይደል!?"አለች እያለቀሰች።
ፈገግ ብሎ ሊያያት ሞከረ።

"ብዙ ስታወራና ስትጨነቅ እንደሚያምህ ታውቃለ
ህ ለምን ፀጥ ብለህ አትተኛም።ምናለበት የምልህ
ን ብትሰማኝ" ልመናዋን የኬንያታ ሆስፒታል ነርስ
ሰላምታ አቋረጣት።

"ኔያጅ ገብረ ስላሴ" አለች ነርሷ የልቡን ምት ለመ
ለካት የፍሰሃን እጅ ሳብ እያደረገች።ብዙ ኬንያውያ
ን ሁሉንም ወንድ አበሻ ወይም ገብረ ስላሴ ወይ
ም ቀነኒሳ ብለው ነው የሚጠሩት።ነርሷ የፍሰሃን
እጅ እንደያዘች "በቅርብ ሰሃት የወሰደው ነገር አለ
እንዴ?" አለች ወደ ሰላም እያየች። ሰላም በአሉታ
ራሷን በፍጥነት እየተራመደች ፍሰሃ የተኛበትን መ
ኝታ ክፍል ለቃ ወጣች።

"አየህ አይደል? አየህ!"ሰላም ሳትጮህ በቁጣ
ድምፅ ተናገረች።

ነርሷ ከሁለት ዶክተሮች ጋር ተመልሳ መጣች።ነር ሷ ሰላምንና ከፍሰሃ ጎን የተኛ ኬንያዊ ታማሚ አስ
ታማሚዎች ክፍሉን ለቀው እንዲወጡ ጠየቀች።

ከደቂቃዎች በኃላ ፍሰሃ የተኛበትን አልጋ እያጣደ
ፉ እየገፉ በአጠገቧ ሲያልፉ ሰላም በህልም
ውስጥ ያለች ያህል ፍዝዝ ብላ ነበር የምታየው።

ፍሰሃ እንደምንም ታግሎ አፉን ከፈት አድርጎ . . .
"ሂጄ!" . . የምትል ቃል ተነፈሰ በሰላም አጠገብ
ሲያልፍ።

"ምናለበት አሁን እንኳን ፀጥ ብትል።"አለች ሰላም
ወደ ቀዶ ጥገና ክፍል የተወሰደ ያለውን ፍሰሃ በዳ
መኑ አይኗ እያየች።

"ከፍሰሃዬ አንደበት የሰማሁት የመጨረሻ ቃል
"ሂጂ!" የሚል ቃል ነበር" አለች እያለቀሰች።

ዳንኤልና ንጉሱ በእውንና በቅዠት መሃል ሆነው
እያለቀሱ ያዳሞጧታል።

"እናም ዘመድና ጓደኛ እንደሌለው ለብቻሽ ቀበርሽ
ው?" ዳንኤል ጠየቀ።

"የት ነው የተቀበረው?"ንጉሱም ጠየቀ።

"እሱ እኮ ነው ከሆዴ አልወጣ ብሎ ሁሌም የሚያ
ስለቅሰኝ" አለች አፍንጫዋን በነጠላዋ እያበሰች።

"ምኑ ነው ከሆድሽ ያልወጣው"ጠየቀ ንጉሱ

"አለመቀበሩ! ፍሰሃ አልተቀበረም"ድንገት ጮሃ
ማልቀስ ጀመረች።

ዳንኤልና ንጉሱ ግራ በመጋባት ተያዩ። ሁለቱም
ተመሳሳይ ነገር እያሰቡ ነበር፤ የልጅትዋ የአእምሮ
ጤንነት አጠራጣሪ ስለመሆኑ።

"ጤነኛ አልመሰልኳቹም አይደል?" አለች በማያቋ
ርጥ ለቅሶዋ መሃል። ዳንኤል በአዎንታ ራሱን ከነቀ
ነቀ በኃላ ነው ያደረገው ነገር ስህተት እንደሆነ
የገባው።

"የፍሰሃዬ አስክሬን በህክምና ወጪ እዳ ተይዞ
አልተቀበረም።እዳው ካልተከፈለ መቅበር አይቻል
ም . . "ንግግሯ ድንገት በገነፈለ ለቅሶ ተቋረጠ።

"ምም እእእእንን?" አከታትለው ተመሳሳይ ጥያቄ
ጠየቁ የሰሙትን ማመን ባልቻለ ድምፅ።

"አዎ የ ፍስሀዬ አስክሬን በእዳ ተይዟል።በአንድ
ሚሊዮን የህክምና ወጪ እዳ ተይዟል"ብላ ማልቀ
ስዋን ቀጠለች። ማልቀሷ የምታቆመው ለፍሰሃ
ጓደኞች ምላሽ ስትሰጥ ብቻ ነው።

"አንድ ሚሊዮን ሽልንግ!?" በዶላር ስንት ማለት
ነው?" ጠየቀ ዳንኤል።

"ወደ አስር ሺ የአሜሪካ ዶላር አካባቢ ይመስለኛ
ል።" አለች።

"እንዴት አስክሬን በእዳ ተይዞ ሳይቀበር ለሁለት
አመት ይቀመጣል!?" ግራ ገብቶት ጠየቀ ዳንኤል

"የፍሰሃዬ አስክሬን ብቻ አይደለም በእዳ የተያዘው
የፍሰሃዬ አስክሬን ያለበት ቦታ ብቻ የሌሎች የአራ
ት ኢትዮጵያውያን አስክሬን በእዳ ተይዞ ሳይቀበር
ተቀምጧል"አለች እያለቀሰች።

"ነገ ሄጄ የወንድሜን አስክሬን ይዤው እመጣለሁ
!" አለ ዳንኤል ሰውነቱ እየተንቀጠቀጠ።

"ሄደን እናመጣዋለን!"አለ ንጉሱ

ዳንኤልና ንጉሱ ጊዮን ሆቴል ላሊበላ ባር ቁጭ
ብለው ቢራ በእንባው ተያይዘውታል።ሊጎነጩ
ብርጭቆዋቸውን ሲያነሱ የእንባ አንኳር የቢራ
ብርጭቆዋቸው ውስጥ ጠብ ይላል።በጉንጫቸ
ው ላይ የሚፈሰው እንባም አልፎ አልፎ ወደ አፋ
ቸው ይሰርጋል።

ነገ በጠዋት ወደ ናዮሮቢ ይሄዳሉ።በእዳ የተያዘ
የጓደኛቸውን አስክሬን ለማስለቀቅና ለአገሩ አፈር
ለማብቃት።ከስምንት ዓመት በፊት ሶስት ጓደኛሞ
ች ነበሩ!ዛሬ ግን ሁለት ቀርተዋል።ስደት ጓደኛቸ
ውን ብቻ ሳይሆን ደስታቸውንም ነበር. . . .
የነጠቃቸው።

*አለቀ ! ?********

ውብ አሁን

╭══•❀|❀:✧๑♡๑✧❀|❀: ══╮
@tsihofoch
@tsihofoch
╰══•ೋ•✧๑♡๑✧•ೋ ══╯