2022-05-12 09:16:29
በኢዮብ መጽሐፍ ውስጥ አሁንም እንቆያለን
#ጥበብ እና #እድሜ ምን ያገናኛቸዋል?
የኢዮብ ወዳጆች በኢዮብ ሕይወት ላይ የሆነውን ለማየት መጥተው ኢዮብን ስወቅሱት "እግዚአብሔር ይህን ሁሉ ያመጣብህ በኀጥያትክ ምክንያት ነው" በማለት ስሟገቱት እንመለከታለን።
ኢዮብም ስመልስ፦
እግሬ ወደ እርምጃው ተጣብቆአል፤ መንገዱንም ጠብቄአለሁ፥ ፈቀቅም አላልሁም። ኢዮብ 23:11
ነገር ግን ላነሳ የፈለኩት የእድሜ እና የጥበብን ግንኙነት ነው። የኢዮብ ጓደኞች በእድመያቸው የሸመገሉ ስሆን ከኢዮብም ጋር ብዙ ምዕራፎችን በጽኑ ስከራከሩ ነበር፤ ነገር ግን ብዙ የመከራን ክርክር ያሳጠሬ በእድሜ ከእነርሱ አነስ የምል ምናልባትም ወጣት የነበረ ኤሊሁ ከምዕራፍ 32- 37 ተናገረ።
የቡዛዊውም የባርክኤል ልጅ ኤሊሁ ተናገረ እንዲህም አለ፡— እኔ በዕድሜ ታናሽ ነኝ፥ እናንተ ግን ሽማግሌዎች ናችሁ፤ ስለዚህም ሰጋሁ፤ እውቀቴን እገልጥላችሁ ዘንድ ፈራሁ። እንደዚህም አልሁ፡— ዓመታት በተናገሩ ነበር፥ የዓመታትም ብዛት ጥበብን ባስተማረች ነበር። ነገር ግን በሰው ውስጥ መንፈስ አለ፥ ሁሉንም የሚችል የአምላክ እስትንፋስ ማስተዋልን ይሰጣል።
ኢዮብ 32:6-8
ይሁን እንጅ በዚሁ መጽሐፍ ላይ ተቃራን ያልሆነ ነገር ተቃራን ምመስል ጥቅስ እናገኛለን፦
በሽምግልና ጊዜ ጥበብ፥ በዘመንስ ርዝመት ማስተዋል ይገኛል።
ኢዮብ 12 ፡12
እርግጥ ነው በእድሜ ርዝመት ብዙ ነገር ማወቅ ይቻላል ነገረ ግን ይህ የምሆነው እድሜ እንድያስተምረን ስንፈቅድ ብቻ ነው። ጥበብ እና ማስተዋል ከእድሜ ጋር ያላቸው ግንኙነት እኛ ለመማር ባለን ፍላጎት ላይ ይመሠረታል እንጅ እድሜያችን ቁጥር በራሱ ጥበብ ልሰጠን አይችልም።
እና ይገርማችኋል ከኤሊሁ ንግግር በኋላ ማንም ሳይሆን እግዚአብሔር ነበር የተናገረው፤ እግዚአብሔር ተናግሮ የኢዮብ መከራና አጠቃላይ ምዕራፉ ያበቃል።
#ተባረኩ ሰሞኑን በኢዮብ መጽሐፍ ላይ እንቆያለን።
...................................
@truelight_reflection
552 views06:16