2022-08-29 06:56:04
"#ምሥጢር ሦስት" በሚል ርእስ የተዘጋጀው መጽሐፍ ተመረቀ!
༺ ༻
"#ምሥጢር ሦስት"በሚል ርእስ በልሳነ ክርስቶስ መ/ር ጳውሎስ መልከዓ ሥላሴ የተዘጋጀው መጽሐፍ ነሐሴ ፳፪ ቀን ፳፻፲፬ ዓ.ም ቦሌ በሚገኘው በዮድ አቢሲኒያ የምግብ አዳራሽ ብፁዕ አቡነ ፊልጶስ የቅድስት ሥላሴ ዩኒቨርስቲ ፕሬዘዳንትና የደቡብ ኦሞ ሀገረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ ፣ ሊቀ ኅሩያን ይልማ ጌታሁን የኢትዮጵያ መጽሐፍ ቅዱስ ማኀበር ጠቅላይ ጸሐፊ ፤ሊቀ ትጉሃን ቀሲስ ታጋይ ታደለ የኢትዮጵያ ሃይማኖቶች ጠቅላይ ጸሓፊ ፣ መልአከ መዊዕ ቀሲስ ሳሙኤል እሸቱ በጠቅላይ ቤተ ክህነት የቤቶች እና ሕንጻ አስተዳደር ልማት ድርጅት ዋና ሥራ አስኪያጅ፤የቅኔ ሊቃውንት ፣ አንጋፋ ሰባክያነ ወንጌልና ዘማርያን ፤ በሀገር ውስጥና በውጭ ዓለማት ያሉ የአድባራትና ገዳማት አስተዳዳሪዎች በተገኙበት በድምቀት ተመረቀ !
#"#ምሥጢር ሦስትን " መጽሐፍ የተጻፈበት የተመለከቱትን አንድ ክፍተት ለመሙላት፤ያልታወቀው እንዲታወቅ፤የተሠወረው ገሀድ እንዲወጣ፤ጸሓፊው ትንተና አድርጓል።
ማር ይስሐቅ "#መጻሕፍትን አዘውትረህ አንብብ መጻሕፍት እግዚአብሔር ን ወደ ማድነቅ ልብህን ይመሩታልና "ይላል።
ሊቅ መልአከ ብርሃን አድማሱ ጀንበሬ በንጉሡ ዘመን አያሌ ሊቃውንትን ሲያስተምሩ “#ንግበር ሰብአ በአርአያነ ወበአምሳሊነ ፣ ሰውን በመልካችንና በአርአያችን እንፍጠር….”(ዘፍ.፩ ፥ ፳፮ ) በሚል ርእሰ ተነሡና ይህን ኃይለ ቃል በመያዝ የቅድስት ሥላሴን አንድነትና ሦስትነት መተንተን ለቀባሪ ማርዳት ነው፡፡ይህን ኃይለ ቃል እኛንም እንደሚመለከት ልነግራችሁ እፈልጋለሁ! እኛም በአርአያችን እና በአምሳላችን ለታላቋ ቤተ ክርስቲያን በትምህርት ሰው እንፍጠርላት ፡ብለዋል፡፡
_ልሳነ ክርስቶስ መ/ር ጳውሎስ መልከዓ ሥላሴ ለምሥጢረ ሦስት መጽሐፍ የቃላት አመራረጡ፣የዕረፍተ ነገር መዋቅርና የአንቀጽ አደረጃጀቱ በሞዴልነት ይወሰዳል።
_የመጽሐፉ መታሰቢያነት፦ "የእግዚአብሔርን ቃል የተናገሩአችሁን ዋኖቻችሁን አስቡ"(ዕብ.፲፫÷፯) እንዳለ ቅዱስ ጳውሎስ ፣ልሳነ ክርስቶስ መ/ር ጳውሎስ መልከዓ ሥላሴምየመጽሐፉን መታሰቢያነት ፩ ዓመት ባልሞላ ጊዜ ውስጥ በተከታታይ ከዚህ ዓለም ለተለዩን ፬ቱ አባቶቻችን መሆኑ ተገልጧል ።
_የኅትመት ዘመን _ሰኔ ፳፻፲፬ ዓ.ም
_የመጽሐፉ መሸጫ ዋጋ_220( $20 )
_የገጽ ብዛት_238
#"ምሥጢር ሦስትን " መጽሐፍ በ፲፭ ክፍላት ተካተውበታል ፣የዘመኑ ወጣቶች ሊገባቸው በሚችሉት መልኩ በግልጽ ቋንቋ የቀረበ ሥራ ነው። መጽሐፉ በኀዳግ ማስታወሻ በሥነ ሥርዓት የተዘጋጀ ፣ብዙ ምሥጢራትን አምቆ የያዘ ፣ውስጠ ትርጉም ያላቸው ቃላትን እንዲሁም ክርስትና ሲነኩት ጣዕሙ የሚታወቅ እና መዓዛው የሚያውድ መሆኑን የምንረዳበት መጽሐፍ ነው።
በአጠቃላይ የመጽሐፉ ይዘት፦
1.ነገረ ሃይማኖት (ለምሳሌ ከገጽ 9_15)
2.ሥርዐተ ቤተ ክርስቲያንን በመዳሰስ የቤተ ክርስቲያናችን የፀጋው ግምጃ ቤት መሆኗን ያሳያል።
3.በትምህርተ ሃይማኖት ዙሪያ ቅድሚያ ስለሚሰጠው ስለ ሦስት ቁጥር የማናውቀውን ለማሳወቅ ፣የምናውቀውን በምሥጢርና በማስረጃ በማስደገፍ ያቀርባል።
4.መንፈሳዊ ሕይወትን የተመለከቱ ጉዳዮች ተካተውበታል ።
“#ዛሬም ቅድስት ቤተ ክርስቲያን የ፳፬ ሰዓት አገልግሎቷ ከመጽሐፍ ቅዱስ ያልወጣ ነው፡፡ ……የእርሷ በሆነው ቅዱስ ያሬድ ትምህርቷ በሙሉ በዜማ ቀርቦ የትውልዱን ልብ እያረካ ኅሊናውን ወደ ሰማይ እንዲያሻግር ታደርጋለች”( ገጽ -129)
“#ስለጾምና የሰዓት ገደብ ሲነገር ማስተዋል የሚገባን ቁም ነገር ከእኽል ውኃ ከመከልከል አኳያ ጾም በቍጥርና በጊዜ የተወሰነ ይኹን እንጂ ከክፉ ተግባር ከመራቅ አንጻር ክርስቲያን እስኪሞት ድረስ ጾመኛ ነው” ይላሉ ፡( ገጽ-142)
"#ምሥጢረ ሦስት" ርቀው የነበሩትን ከመንፈሳዊ ሕይወት ጋር የሚያገናኝ መጽሐፍ ነው።ሰለዚህ መጽሐፉ እንድናነበው እየፈለገን እንዳንጠፋ፤እየተመኘን እንዳንሸሸው መልእክቴ ነው።
ቅዱስ አግናጥዮስ "ሰው በቀመሳቸው ጊዜ ከሚመሩ ፍሬዎች ሽሹ፤እነዚህ ፍሬዎች የእግዚአብሔር አብ ተክሎች አይደሉምና"ይላል።
★ ★ ★
መ/ር ተመስገን ዘገዬ
ነሐሴ ፳፪ ቀን ፳፻፲፬ ዓ.ም
ዩቲዩብ subscribe and share https://www.youtube.com/channel/UCJKl-fJ4qKtLKfva2ufSc-A
ሰብስክሪያብ በማድረግ ቤተሰብ ይሁኑ!
392 viewstemesgen Zegeye, 03:56