Get Mystery Box with random crypto!

ሲኦልን አስመለሰው አፍ የተባለ (መቃብር) ሁልጊዜ ይበላል ። በአፉ ያላምጥ በጨጓራውም (የ | ማኅሌት ሚዲያ

ሲኦልን አስመለሰው

አፍ የተባለ (መቃብር) ሁልጊዜ ይበላል ። በአፉ ያላምጥ በጨጓራውም (የሲኦል እሳት) ይፈጭ ነበር (በርደተ መቃብር ላይ ርደተ ሲኦል) ። ከዕለታት አንድ ቀን አፍ የተባለ (መቃብር) ከዚህ ቀደም ሲመገብ እንደ ነበራቸው ጥሬ ሥጋዎች (ሙታን) መስሎት የሕይወት ምግብ የተባለ (ክርስቶስን) ባየ ጊዜ ሊበላው ጎመጀ ። አገኘው ብሎ ተሰገብግቦሞ በላው ፤ ነገር ግን ሥጋው እንደዚህ ቀደሞቹ ሥጋ አልነበረም ። ሥጋው ኢመዋቲ ከሚባል የሥጋ ቅመም (መለኮት) ጋር ተዋሕዶ ተሰርቶ ነበርና ለአፉ (ለመቃብር) አልጣፈጠውም ። ሆድ የተባለም (ሲኦል) ውጦት የነበረው የሥጋ ማባያ (ነፍስም) ኢመዋቲ ከሚባል ቅመም (መለኮት) ጋር ተዋሕዶ ነበርና ለሆድ( ሲኦል) አልተስማማውም ። ስለዚህም ሆድ (ሲኦል) ተረበሸ ፣ ተጨነቀ ፣ ወደ ላይ ወደ ላይ ይለውም ጀመር ፤ አልቻለምና አስመለሰው ፤ ያን ጊዜ አስቀድሞ የበላቸው ምግቦች (ነፍሳት) ግልብጥ ብለው ወጡ ። ዛሬ! ሞት በእውነት ክርስቲያን ሲሞት ያስፈራዋል ። አሁንም ያስመልሰዋልና ።

መልካም በዓል ወዳጄ
+++++++++++
ዲ/ን ዘአማን
16/08/2014
አዲስ አበባ