Get Mystery Box with random crypto!

የ2015 ዓ/ም ብሔራዊ ፈተናን #በግንቦት ወር ለመስጠትም ታቅዷል ፦ የትምህርት ሚኒስትር ፕ/ር ብ | Ministry of education®

የ2015 ዓ/ም ብሔራዊ ፈተናን #በግንቦት ወር ለመስጠትም ታቅዷል ፦ የትምህርት ሚኒስትር ፕ/ር ብርሃኑ ነጋ

የትምህርት ሚኒስቴር በ " ኮቪድ-19 ወረርሽኝ " ምክንያት የተዛባውን የትምህርት ካላንደር በዘንድሮው ዓመት እንደሚያስተካክል ጠቁሟል።

" በ2015 ሁለት ፈተና ነው የምንሰጠው። አሁን የምንሰጠው ፈተና (ከመስከረም 30 ጀምሮ) የ2014ን ፈተና ነው።

ከኮቪድ ጊዜ ጀምሮ መርሀ ግብሩ እየተበላሽ በአጠቃላይ የትምህርት ስርዓታችን ግልፅ የሆነና ሁሉም የሚያውቀው የአካዳሚክ ካላንደር ሊኖረን አልቻለም ፤ እሱን በዚህ ዓመት እናስተካክላለን አሁን መስከረም 30 የምንሰጠው የ2014ን ነው ግንቦት ላይ የ2015 ተማሪዎችን እንፈትናለን።

ከዛ በኃላ ባሉት ጊዜያት የአካዳሚክ ካላንደሩ ከሞላ ጎደል ወደ ስርዓቱ ይገባል። "

መረጃዎችን በፍጥነት ለማግኘት ቴሌግራም ገፃችንን JOIN እና ሼር ያድርጉ!

@TMIHIRT_MINISTER
@TMIHIRT_MINISTER