የመጀመሪያው ዙር የ12ኛ ክፍል ብሔራዊ ፈተና ዛሬ መሰጠት ይጀምራል ***** የመጀመሪያው ዙር የ12ኛ ክፍል ብሔራዊ ፈተና ከዛሬ መስከረም 30 ቀን 2015 ዓ.ም አንስቶ መሰጠት ይጀምራል። በመጀመሪያው ዙር ፈተናውን የሚወስዱት የማኅበራዊ ሳይንስ ተማሪዎች ሲሆኑ፣ ፈተናው ከመስከረም 30 እስከ ጥቅምት 2 ቀን 2015 ዓ.ም ባለው ጊዜ ውስጥ የሚሰጥ መሆኑን የትምህርት ሚኒስቴር ያወጣው መርሐ-ግብር አመላከቷል። የተለያዩ ዩኒቨርሲቲዎች ተፈታኞቹን ተቀብለው ፈተናውን ለመስጠት ዝግጅታቸውን ማጠናቀቃቸው ተገልጿል። @TMIHIRT_MINISTER @TMIHIRT_MINISTER 25 viewsedited 06:20