ፍልስፍና ከዘረያቆብ እስከ ሶቅራጥስ የሚለውን መፅሐፍ እየገዛሁት
" የዓለማየሁ ገላጋይን መፅሐፍ እንዴት አየሽው? " አለኝ
"አሌክስዬ ከተለመደው ውጪ ከፍ ብሎ መጥቶዋል" አልኩት
"እረ ብዙ ሰው ግን በዚህ መፅሐፉ ተናዶበታል ፣ የመለሰውም አለ " ብሎኝ እርፍ አለ . .
ይባስ ብሎ እዳለ ጌታ ከበደ በሚያዘጋጀው ዝግጅት ላይ ያለፈው ሳምንት እንግዳ "አሌክስዬ " ነበር (ምፅ ባልገኝም ፣ ዝግጅቱን በዩቲዩብ ገፃቸው ላይ ማየት ችያለው )
ከታዳሚ ውስጥ አንዷ "ሸልፌ ላይ እዳይኖር ማልፈልገው መፅሐፍ ነው" ብላ ክው አርጋኛለች(ያው መብቷ ነው ፣ በልኩ ነው ሰው ሚያስበው !)
. . . . ለምኑም ሰው ክፍቱ ሲነገረው ይደነግጣል እስቲ እራሳቹን ታዘቡ . . ስበከቶችን ወይም ሃዲሶችን የሚስማሙን የማይነኩንን ነገር ሲነግሩን ነው. . . . ስለ ጉድፋችን ሲነገረን እንደ ደነበረ ጥጃ እንፈረጥጣለን. . . .
ለምኑም እኔ መፅሐፉ እልል አርጎኛል. . .
ያለንበትን እውነት ቁልጭ አርጎ የነገረን ይመስለኛል. . . .
ከፈለጋቹት አንብቡት . . .
#የተማሩ መሃይም የሆኑት የብሄር ፖለቲካ አስጨፋሪዎቻቹን አስተሳሰብ እምቢ ማለት እስካለመዳቹ ድረስ በተማረ መሃይም ትመራላቹ . . . !!! (መልዕክቱ አለን አለን ምትሉ በሁሉም አቅጣጫ ያላቹን ብሔርተኞችን ይመለከታል)
ይኼን አለች ብላቹ እኮ ቻናሉን በንዴት ምለቁም አጠፉም ባትለቁ ግን ጥሩ ነው
/ትዝታ/
❀:✧๑♡๑✧
@tiztawe
@tiztaw
❀:✧๑♡๑✧