Get Mystery Box with random crypto!

ፍልስፍና ከዘረያቆብ እስከ ሶቅራጥስ የሚለውን መፅሐፍ እየገዛሁት ' የዓለማየሁ ገላጋይን መፅሐፍ | ትዝታዊ🐣

ፍልስፍና ከዘረያቆብ እስከ ሶቅራጥስ የሚለውን መፅሐፍ እየገዛሁት

" የዓለማየሁ ገላጋይን መፅሐፍ እንዴት አየሽው? " አለኝ

"አሌክስዬ ከተለመደው ውጪ ከፍ ብሎ መጥቶዋል" አልኩት

"እረ ብዙ ሰው ግን በዚህ መፅሐፉ ተናዶበታል ፣ የመለሰውም አለ " ብሎኝ እርፍ አለ . .

ይባስ ብሎ እዳለ ጌታ ከበደ በሚያዘጋጀው ዝግጅት ላይ ያለፈው ሳምንት እንግዳ "አሌክስዬ " ነበር (ምፅ ባልገኝም ፣ ዝግጅቱን በዩቲዩብ ገፃቸው ላይ ማየት ችያለው )

ከታዳሚ ውስጥ አንዷ "ሸልፌ ላይ እዳይኖር ማልፈልገው መፅሐፍ ነው" ብላ ክው አርጋኛለች(ያው መብቷ ነው ፣ በልኩ ነው ሰው ሚያስበው !)


. . . . ለምኑም ሰው ክፍቱ ሲነገረው ይደነግጣል እስቲ እራሳቹን ታዘቡ . . ስበከቶችን ወይም ሃዲሶችን የሚስማሙን የማይነኩንን ነገር ሲነግሩን ነው. . . . ስለ ጉድፋችን ሲነገረን እንደ ደነበረ ጥጃ እንፈረጥጣለን. . . .

ለምኑም እኔ መፅሐፉ እልል አርጎኛል. . .
ያለንበትን እውነት ቁልጭ አርጎ የነገረን ይመስለኛል. . . .

ከፈለጋቹት አንብቡት . . .



#የተማሩ መሃይም የሆኑት የብሄር ፖለቲካ አስጨፋሪዎቻቹን አስተሳሰብ እምቢ ማለት እስካለመዳቹ ድረስ በተማረ መሃይም ትመራላቹ . . . !!! (መልዕክቱ አለን አለን ምትሉ በሁሉም አቅጣጫ ያላቹን ብሔርተኞችን ይመለከታል)

ይኼን አለች ብላቹ እኮ ቻናሉን በንዴት ምለቁም አጠፉም ባትለቁ ግን ጥሩ ነው

/ትዝታ/



❀:✧๑♡๑✧
@tiztawe
@tiztaw
❀:✧๑♡๑✧