በጉራጌ ዞን እዣ ወረዳ በደረሰ የመኪና አደጋ የ6 ወጣቶች ህይወት አለፈ በጉራጌ ዞን እዣ ወረዳ በደረሰ የመኪና አደጋ በ10 ሰዎች ላይ ቀላልና ከባድ ጉዳት ሲደርስ የ6 ወጣቶች ህይወት ማለፉን የወረዳው ፖሊስ ፅ/ቤት አስታውቋል። አደጋው የደረሰው በእዣ ወረዳ ወርት ቀበሌ እንጨት ጭኖ ወደ ከተማ በመጓዝ ላይ የነበረ ሲኖ የጭነት ተሽከርካሪ በደረሰበት የመገልበጥ አደጋ ነው። ጉዳት የደረሰባቸው ሰዎች በሆስፒታል ህክምና እየተደረገላቸውም እንደሚገኝ ተገልጿል። @TikvahethMagazine 29.3K views09:06