የመንበረ ጸባኦት ቅድስት ስላሴ ካቴድራል እድሳት 75 በመቶ መድረሱ ተገለፀ የመንበረ ጸባኦት ቅድስት ስላሴ ካቴድራል እድሳት በ172 ሚሊየን ብር እየተከናወነ ሲሆን የጥገና ሥራው 75 በመቶ መድረሱ ተገለፀ። እድሳቱ በውሉ መሰረት መጋቢት 30 ቀን 2016 ዓ.ም መጠናቀቅ ቢጋባውም በገቢ ማነስ እና ህንፃውን ለማጠናቀቅ የሚረዱ ግብአቶች ከውጭ ለማስገባት የውጭ ምንዛሬ እጥረት ችግር መሆኑ ተገልጿል። የካቴድራሉ እድሳት ለማጠናቀቅ 85 ሚሊየን ብር መሰብሰብ እንደሚጠይቅ የተገለፀ ሲሆን የካቴድራሉን እድሳት ከፍጻሜ ለማድረስ አስተዋጽኦ እንዲደረግ ጥሪ ቀርቧል። @TikvahethMagazine 19.7K views10:58