Get Mystery Box with random crypto!

ብሪታኒያ ከኢትዮጵያ የሚላኩ የአበባ ምርቶች ያለ ቀረጥ ወደ ሀገሪቱ እንዲገቡ ፈቀደች ብሪታኒያ ከ | TIKVAH-MAGAZINE

ብሪታኒያ ከኢትዮጵያ የሚላኩ የአበባ ምርቶች ያለ ቀረጥ ወደ ሀገሪቱ እንዲገቡ ፈቀደች

ብሪታኒያ ከኢትዮጵያ እና ከምስራቅ አፍሪካ  ሀገራት ጋር የሚደረገውን የንግድ ልውውጥ ርካሽና ተመጣጣኝ ለማድረግ በማለም ከቀጠናው ሀገራት የሚላኩ አበቦች ትቆርጥ የነበረውን የቀረጥ ክፍያ ለ2 አመት አነሳች።

ከዚህ በፊት የአበባ ምርቶች ወደ ብሪታኒያ ሲገቡ 8 በመቶ ቀረጥ መክፈል የሚጠበቅባቸው ሲሆን ከዛሬ ሚያዚያ 2 ቀን 2016 ዓ.ም ጀምሮ የቀረጥ ክፍያው የሚነሳ መሆኑን ብሪታኒያ ባወጣችው መግልጫ አስታውቃለች።

ይህ የ 8 በመቶ የቀረጥ ክፍያ ከመላው ዓለም የአበባ ምርቶችም ወደ ሀገሪቱ የሚልኩ ሀገራትን ተጠቃሚ ያደርጋል ሲባል ነገር ግን ኬንያ፣ ኢትዮጵያ፣ ሩዋንዳ፣ ታንዛኒያ እና ዩጋንዳ ላሉ ዋና የአበባ አምራች ሀገራት ትልቅ አጋጣሚ ይፈጥራል ተብሏል።

ኢትዮጵያ ከሰሃራ በታች ካሉ የአፍሪካ ሀገራት 23 በመቶ የሚሆነውን የአበባ ምርት ወደ ውጪ የምትልክ ሲሆን በአፍሪካ ሁለተኛዋ ትልቅ የአበባ አምራች ነች። በ 2023 ወደ ብሪታኒያ  የላከችው የአበባ ንግድ ዋጋ 12.6 ሚሊዮን ፓውንድ እንደሆነም የብሪታኒያ መንግስት አሳውቋል።

@TikvahethMagazine