Get Mystery Box with random crypto!

በአፍሪካ ለነዳጅ እና ጋዝ ፕሮጀክቶች ብድር የሚያቀርበው የአፍሪካ ኢነርጂ ባንክ በዚህ አመት ስራ | TIKVAH-MAGAZINE

በአፍሪካ ለነዳጅ እና ጋዝ ፕሮጀክቶች ብድር የሚያቀርበው የአፍሪካ ኢነርጂ ባንክ በዚህ አመት ስራ ይጀምራል ተባለ

አፍሪካ የነዳጅ እና ጋዝ ፕሮጀክቶችን በገንዘብ የመደገፍ  ስራ ይሰራል የተባለው የአፍሪካ ኢነርጂ ባንክ በዚህ አመት በ5 ቢሊዮን ዶላር መነሻ ካፒታል በ2024 ስራ ሊጀምር መሆኑን ሮይተርስ ዘግቧል።

ባንኩ የተቋቋመው በአፍሬክሲም ባንክ እና በአፍሪካ ፔትሮሊየም አምራቾች ድርጅት (ኤፒፒኦ) ሲሆን ዋናዎቹ ባንኮች በአየር ንብረት ላይ ተጽዕኖ የሚያሳድሩ የነዳጅ ፕሮጀክቶችን በመተው ኢንቨስትመንቶቻቸውን ወደ ሌላ ቦታ እንዲቀይሩ ከአካባቢ ጥበቃ ተሟጋቾች ከፍተኛ ጫና እያጋጠማቸው በመሆኑ ዘርፉ የፋይናንስ እጥረት ችግር ውስጥ ገብቷል ተብሏል።

ይህ ባንክ በአፍሪካ ኢነርጂ ዘርፍ ያለውን ይህንን የፋይናንስ እጥረት ለመቅረፍ ሚና ይኖረዋል ሲባል ካፒታሉን ለማሰባሰብ እያንዳንዱ የአፍሪካ አባል ሀገር ቢያንስ 83 ሚሊዮን ዶላር መለገስ እንደሚጠበቅበትና ቀሪው ገንዘብ ከመካከለኛው ምስራቅ አማራጭ የፋይናንስ ምንጮች ይሰበሰባል ተብሏል።

@TikvahethMagazine