ሳፋሪኮም ኢትዮጵያ የሞባይል ገንዘብ አገልግሎት ፈቃድ አገኘ። የፋይናንስ ሚኒስትር አቶ አህመድ ሺዴ በወዳጅነት አደባባይ እየተካሄደ ባለው የሳፋሪኮም ኢትዮጵያ የብሔራዊ አገልግሎት ማስጀመሪያ ስነ ስርዓት ላይ ድርጅቱ በኢትዮጵያ የሞባይል ገንዘብ አገልግሎት እንደተሰጠው አስታውቀዋል። ሳፋሪኮም ኢትዮጵያ በሀገሪቱ ከሚጀምረው የቴሌኮም አገልግሎት በተጨማሪ M-Pesa የተባለውን ታዋቂና አለም አቀፍ የሞባይል ገንዘብ አገልግሎቱን በኢትዮጵያ ለመጀመር የብሔራዊ ባንክ የሞባይል ገንዘብ አገልግሎት መመሪያ ማሻሻያ እስኪደረግበትና ፈቃድ እስኪሰጠው በመጠበቅ ላይ እንደነበር ይታወሳል። via - አዲስ ዘይቤ • @ThinkAbyssinia • 4.0K views16:27