የ20 ጊዜ የግራንድ ስላም ሻምፒዮን አሸናፊው ሮጀር ፌደረር ራሱን ከቴኒስ አገለለ ስዊዘርላንዳዊው ታሪክ አይሽሬ የሜዳ ቴኒስ ተጫዋች ሮጀር ፌደረር ዛሬ ሌሊት የመጨረሻው ጨዋታውን በላቨር ካፕ ካደረገ በኋላ ራሱን ከውድድር አለም ማግለሉን አሳውቋል። 369 ጨዋታዎችን ያሸነፈው፤ 103 የኤቲፒ የነጠላ ውደድር ባለድል፤ የ2 ጊዜ የኦሎምፒክ የወርቅ ባለሜዳሊያ ፤ ለ237 ተከታታይ ሳምንት የአለም ቁጥር አንድ የተባለው የ20 ጊዜ የግራንድ ስላም ሻምፒዮን አሸናፊው ሮጀር ፌደረር በመጨረሻም ራኬቱን ሰቅሏል። • @ThinkAbyssinia • 6.5K views12:48