Get Mystery Box with random crypto!

ኢትዮጵያዊው ጃንደረባ የአንባብያን ኅብረት

የቴሌግራም ቻናል አርማ theethiopianjandereba — ኢትዮጵያዊው ጃንደረባ የአንባብያን ኅብረት
የቴሌግራም ቻናል አርማ theethiopianjandereba — ኢትዮጵያዊው ጃንደረባ የአንባብያን ኅብረት
የሰርጥ አድራሻ: @theethiopianjandereba
ምድቦች: ስነ-ጽሁፍ
ቋንቋ: አማርኛ
ተመዝጋቢዎች: 5.60K
የሰርጥ መግለጫ

በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን የአዲስ አበባ ሀገረ ስብከት ሥር በበየኢትዮጵያዊው ጃንደረባ ትውልድ (ኢጃት) በኅዳር 2013 ዓ.ም. የተቋቋመ የአንባቢያን ኅብረት ሲሆን የጃንደረባውን የንባብ አሠረ ፍኖት በመከተል የመጻሕፍት ዳሰሳና የንባብ ባሕልን የሚያዳብሩ ወርኀዊ ሁነቶችን ከሰ/ት/ቤቶች ጋር ያዘጋጃል::
መልዕክት ለመላክ ፣ ለአስተያየት እና ለመመዝብ @Endalk9

Ratings & Reviews

2.00

2 reviews

Reviews can be left only by registered users. All reviews are moderated by admins.

5 stars

0

4 stars

0

3 stars

0

2 stars

2

1 stars

0


የቅርብ ጊዜ መልዕክቶች

2022-09-01 11:06:50 ሰላም!

ስምዎ በዚህ "ፋይል" ውስጥ የሚገኝ ከሆነ የውድድር ጉባኤውን ለመሣተፍ ከላይ የተለቀቀውን ቅጽ ከሞሉት የመጀመሪያዎቹ 200 ሰዎች ውስጥ አሉ ማለት ነው። የፊታችን እሑድ፣ ነሐሴ 29 ቀን 2014 ዓ.ም ከቀኑ 7:30 በቀነኒሳ ሆቴል (ቦሌ) በሚደረገው የፊልጶስና ባኮስ የአሸናፊዎች አሸናፊ ውድድር ላይ እንዲገኙ በማክበር ጋብዘንዎታል።

ጃንደረባው መጻሕፍት
1.1K viewsElilta, 08:06
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-09-01 09:59:32
292 viewsElilta, 06:59
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-08-31 06:37:17 ሰላም የጃንደረባው መጻሕፍት ቤተሰቦች!

22ኛው ወርኃዊ የመጻሕፍት ዳሰሳ ጉባኤ እና የፊልጶስና ባኮስ የ2014 ዓ.ም የአሸናፊዎች አሸናፊ የጥያቄና መልስ ውድድር የፊታችን እሑድ፣ ነሐሴ 29 ቀን 2014 ዓ.ም ከቀኑ 7:30 ጀምሮ በአዲስ አበባ፣ ቀነኒሳ ሆቴል (ቦሌ) ይካሄዳል።

በጉባኤው ላይ ለመሣተፍ ከዚህ በታች ያለውን ቅጽ ሞልተው የመግቢያውን ካርድ ይውሰዱ። ቅጹን የሞሉ የመጀመሪያዎቹ 200 ሰዎች በጉባኤው ላይ ተሣታፊ ይሆናሉ።

እናመሰግናለን።

https://forms.gle/qgy7VWTsVYFbMbxXA
879 viewsElilta, 03:37
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-08-29 21:56:34
1.4K viewsElilta, 18:56
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-08-24 06:57:02
1.5K viewsDejene Korsa, 03:57
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-08-24 06:34:33
1.4K viewsElilta, 03:34
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-08-24 06:34:33 10ኛው እና የዓመቱ የመጨረሻው የጃንደረባው መጻሕፍት ጉባኤ በድሬዳዋ በድምቀት ተካሄደ::

ነሐሴ 15 ቀን 2014 ዓ.ም
ድሬደዋ፣ ኢትዮጵያ

10ኛው እና ለዓመቱ የመጨረሻው የሆነው የጃንደረባው መጻሕፍት ጉባኤ የኢትዮጵያዊውን ጃንደረባና የቅዱስ ፊልጶስን የንባብ ፈለግ የተከተሉ ወጣቶችን አሣትፎ በድሬዳዋ ደብረ ታቦር እግዚአብሔር አብ ቤተ ክርስቲያን ጽርሐ ጽዮን ሰንበት ት/ቤት አዳራሽ ብዙ አንባብያን በተገኙበት በድምቀት  ተካሄዶአል።

በዕለቱ ጉባኤው በደብሩ አገልጋይ ካህናት እና ዲያቆናት በውዳሴ ማርያም ጸሎት የተጀመረ ሲሆን መርሐግብሩ የተመራው በሰ/ት/ቤቱ ም/ሰብሳቢ ወጣት ኤልያስ ነበር። ጉባኤው መክፈቻውን ያደረገው የሐዋርያት ሥራ ምዕራፍ 8ን በማንበብ ሲሆን በሰ/ት/ቤቱ ዘማርያን ዕለቱን እና በዓሉን የሚያመለክት ጥዑም ዝማሬ ቀርቧል።

በመቀጠል ዝግጅቱ "የበረሃ ምንጮች - ማላንካራውያን" በተሰኘው የመኮንን ኃብተ ሚካኤል መጽሐፍ ላይ ዳሰሳን በማቅረብ ቀጥሎአል።

በዲ/ን ብንያም አድማሱ የቀረበው የመጽሐፉ ዳሰሳ በመጽሐፉ ውስጥ ያሉትን አሳቦች በሚያስደንቅ ሁኔታ ከመተንተን በተጨማሪ ቀጣይ የቤት ሥራዎቻችንን እንዲሁም እስከ ዛሬ ያልሠራናቸውን ሥራዎች በማንሣት ለሰ/ት/ቤት፣ ለምዕመናን፣ ለካህናት፣ ለወጣቶች፣ ለወላጆች እንዲሁም ለሕፃናት በየዕድሜ ደረጃቸው የሚጠበቅባቸውን ነገር አቅጣጫ በመስጠት ጭምር የቀረበ በመሆኑ በታዳሚዎች ሕሊና ውስጥ የማይጠፋ ምስልን የቀረፀ፣ ቁጭትን የፈጠረና "እኛስ ለእኛ ቤተ ክርስቲያን በዚህ ዘመን ምን ልናደርግ ይገባናል?" የሚለውን ጥያቄ የጫረ ነበር።

በመቀጠል መድረኩን የተረከበው በመጽሐፉ ዳሰሳ ዙሪያ በተሣታፊዎች የሚደረግ ውይይት እና ጥያቄ የመጠየቅ መርሐግብር ነበር። በተነሡት ጥያቄዎች ላይ የዳሰሳው አቅራቢ በቂ ማብራሪያ በመስጠት አጥጋቢ በሆነ መልኩ ጥያቄዎቹን መልሰዋል።

በመጨረሻም የኢትዮጵያዊው ጃንደረባ ትውልድ ከድሬ አስተባባሪዎች መካከል ወጣት ዳዊት ዘገየ ባለፉት 10 ዙሮች ጉባኤውን የተሣተፉትን ሁሉ አመስግነው የዚህን ዓመት የመጽሐፍ ዳሰሳ ፍጻሜ መሆኑን አስታውቀዋል። በተጨማሪም እንደ እግዚአብሔር ፈቃድ በ2015 ዓ.ም የመጻሕፍት ጉባኤው ሌሎቹን የኢትዮጵያዊውን ጃንደረባ ትውልድ ሁነቶች በመጨመር ከፍ ባለ ደረጃ ዝግጅቱን እንደሚቀጥል አስታውቀዋል ።

የሚቀጥለው ጉባኤ የኢትዮጵያዊው ጃንደረባ ሠረገላ ማረፊያው በደብረ ምሕረት ቅዱስ ሚካኤል ካቴድራል መስከረም 29 ቀን 2015 ዓ.ም መሆኑ ታውቋል። የሚዳሰሰውም መጽሐፍ በዲ/ን ሚክያስ አስረስ የተጻፈው "ማስያስ" የተሰኘው መጽሐፍ ይሆናል።

ለመሆኑ በዚህ የጃንደረባ ሠረገላ ላይ ተሳፍረን ከማንበብ፣ ከመጠየቅና ከመመራመር የሚከለክለን ምንድር ነው?

ቸር ያገናኘን!
1.3K viewsElilta, 03:34
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-08-22 04:49:03
1.7K viewsElilta, 01:49
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-08-18 08:41:55
2.7K viewsElilta, 05:41
ክፈት / አስተያየት ይስጡ