Get Mystery Box with random crypto!

ተዝኪራ - ትውስታ እና አደራ ስለ አኺራ - التذكرة فى الأمور الآخرة

የቴሌግራም ቻናል አርማ tezkirachannel — ተዝኪራ - ትውስታ እና አደራ ስለ አኺራ - التذكرة فى الأمور الآخرة
የቴሌግራም ቻናል አርማ tezkirachannel — ተዝኪራ - ትውስታ እና አደራ ስለ አኺራ - التذكرة فى الأمور الآخرة
የሰርጥ አድራሻ: @tezkirachannel
ምድቦች: ያልተመደበ
ቋንቋ: አማርኛ
ሀገር: ኢትዮጵያ
ተመዝጋቢዎች: 158

Ratings & Reviews

4.00

3 reviews

Reviews can be left only by registered users. All reviews are moderated by admins.

5 stars

2

4 stars

0

3 stars

0

2 stars

1

1 stars

0


የቅርብ ጊዜ መልዕክቶች 3

2020-07-31 14:47:46
198 views11:47
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2020-07-30 18:35:30
198 views15:35
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2020-07-29 23:48:43
158 views20:48
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2020-07-26 10:51:52 አስርቱ የዙል ሒጃህ ቀናት (ኡስታዝ ሻሚል ሙዘሚል)
201 views07:51
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2020-06-21 09:14:51 ከፀሐይ ግርዶሽ ጋር የተያያዙ ህግጋት

ክፍል 1

በሸይኽ ኢልያስ አሕመድ
እና
በኡስታዝ ሙሐመድ ሐሰን ማሜ

ሊንኩን ትጭነው በዩትዩብ ቻናላችን መከታተል ይችላሉ


290 views06:14
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2020-06-18 23:45:23
ታላቁ ዓሊም ሙሐመድ ቢን ሷሊህ አልዑሠይሚን እንዲህ ይላሉ፦
.
የሰው ልጅ ሩሁ በሰውነቱ እስካለች ድረስ ለፊትና የተጋለጠ ነው። ስለዚህ ራሴንና እናንተን አደራ የምለው ሁሌም አላህ ፅናት ይሰጠን ዘንድ መማፀንን ነው።
.
« መፍራት ይኖርብናል » ምክንያቱም እግሮች የቆሙት ሸርታታ (የሚያንሸራትት) ላይ ነው። አላህ ካላፀናን በቀር አንሸራቶን እንወድቃለን።
.
አላህ ለመልክተኛው ﷺ ፦
.
وَلَوْلَا أَنْ ثَبَّتْنَاكَ لَقَدْ كِدْتَ تَرْكَنُ إِلَيْهِمْ شَيْئًا قَلِيلًا
.
« ባላፀናንህም ኖሮ ወደነሱ ጥቂትን (ዝንባሌ) ልትዘነበል በእርግጥ በተቃረብክ ነበር።” ይህ ለመልክተኛው ﷺ ከሆነ ለኛስ ታዲያ.??
.
ኢማናችን ደካማ፣ ለእውነት የምናንገራግር፣ የአደናጋሪዎች ማደናገሪያ እና ስሜትን መከተል በቀላሉ ክፍተት የሚፈጥሩብን ሆኖ ሳለ አላህ እንዲያፀናን መለመን አይገባንምን.??
.
ከባድ አደጋ ላይ ነን በሀቅ ላይ ያፀናን ዘንድ ልንለምነው ይገባል። ልቦናችንን እንዳያዘነብልብንም መማፀን አለብን።
.
የአእምሮ ባለቤቶችም ዱዓ ይህ ነው፦
.
رَبَّنَا لَا تُزِغْ قُلُوبَنَا بَعْدَ إِذْ هَدَيْتَنَا
.
« ጌታችን ሆይ! ቅኑን መንገድ ከመራኸን በኋላ ልቦቻችንን አታዘምብልብን” ይላሉ።
.
[ ሸርሁል ሙምቲዕ - 5/388 ]
.
.
----------------------------------
ሁዳ መልቲሚዲያ- 🅗🅤🅓🅐
https://t.me/huda4eth
529 views20:45
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2020-06-16 09:18:51 ከረመዳኑ በኋላ ምን؟
ክፍል 3

ከረመዳን በኋላ ዋናው ቁም ነገር ፅናት ነው።

ሀ/ የፅናት ምንነት ትርጓሜ

ፅናት ማለት ባሉበት መልካም ነገር ላይ እስከ ዕለተ ሞት ድረስ በጎውን እየሠሩ ክፉውን እየራቁ ያለማቋረጥ መዘውተር ማለት ነው።

ለ/የፅናት አስፈላጊነት

1/የተፈጠርነው እላህን አዘውትረን እንድንገዛው ነው።

2/የአላሁ تعالى እና የመልዕ ክተኛው ﷺ ትዕዛዝ ነው።

አላህ تعالئ እንደተናገረው: "እርሱን ብቻ ተገዛው ለርሱም በመገዛትህ በፅናት ታገስ። "

ዓኢሻ رضي الله عنها እንደተናገሩት
"የአላህ መልዕክተኛ ሥራን ሲሰሩ ያፀኑት(ይዘወትሩበት) ነበር። "
ዘግበው ቡኻሪና ሙስሊም

መ/የሥራዎች ፍርያማነት/ ተቀባይነቱ ከጅምሩ ማማሩ ሳይሆን እስከመጨረሻው በመፅናት ድምዳሜው ላይ በማድረሱ ነው።

አላህ سبحانه وتعالى በክቡር ቁርኣን እንዲህ ይላል፦

وَاعْبُدْ رَبَّكَ حَتَّىٰ يَأْتِيَكَ الْيَقِينُ
"እርግጠኛው (ሞት) እስኪመጣህ ጌታህን ተገዛ!"
አል ሒጅር: 99

ሠ/ የአላህ መልዕክተኛ ﷺ የሥራን ተቀባይነት መሥፈርት ያደረጉት በመጨረሻዎቹ በድምዳሚያቸው ላይ ስለመሆኑ እንዲህ ብለዋል:-

"የሥራዎች ተቀባይነትና ትክክለኝነት በመጨረሻቸው ብቻ ነው። "

ረ/ ፅናት የመልካም ተግባር (የረመዳናችን)ተቀባይነት መስፈርቱ ነው

"የአንድ መልካም ሥራ ምንዳው (ጀዛእ) (የተቀባይነት ምልክቱ) ከዚያ (ከመልካሙ ሥራ በኋላ) ቀጣይነት ያለው ጥሩ ተግባር ማስከተሉ ነው።

"የመጥፎ ሥራ ቅጣቱ(ጀዛው) ክፉ አድራጎትን (መጥፎን ተግባር) ማስከተሉ ነው። "
ሐሰነል በስሪ رحمه الله

ልብ ያለው ልብ ይበል

ፅናት የሙእሚን ባህሪይ ሲሆን
ወረተኝነት የሙናፊቅ ባህሪ ነው።

ይህች ዓለም

የውጣ ውረድ
የመነሳትና የመውደቅ
የትግል ሜዳ ናት

መልካምን ወደራሳችን በማምጣት ማንነታችንን (ስብእናችንን) በኢማን ማጠንከሩ ባንዳፍታ የምናመጣው ሳይሆን ቀስ በቀስ በሂደት የሚመጣ ነው።

አንዴ ተነስተን በዚያው መውደቅ ሳይሆን ፦

አየተነሱ እየወደቁ
ተስፋ ሳይቆርጡ
በፅናት መቀጠል ነው።

ከረመዳን በኋላ ምን?
ክፍል 3
ከረመዳን በኋላ ዋናው ቁም ነገር ፅናት ነው።

1. የፅናት ምንነት ትርጓሜ

ፅናት ማለት ባሉበት መልካም ነገር ላይ እስከ ዕለተ ሞት ድረስ በጎውን እየሠሩ ክፉውን እየራቁ ያለማቋረጥ መዘውተር ማለት ነው።

ለ/የፅናት አስፈላጊነት

1/የተፈጠርነው እላህን አዘውትረን እንድንገዛው ነው።

2/የአላሁ تعالى እና የመልዕ ክተኛው ﷺ ትዕዛዝ ነው።

አላህ تعالئ እንደተናገረው: "እርሱን ብቻ ተገዛው ለርሱም በመገዛትህ በፅናት ታገስ። "

ዓኢሻ رضي الله عنها እንደተናገሩት
"የአላህ መልዕክተኛ ሥራን ሲሰሩ ያፀኑት(ይዘወትሩበት) ነበር። "
ቡኻሪና ሙስሊም ዘግበውታል

መ/የሥራዎች ፍርያማነት/ ተቀባይነቱ ከጅምሩ ማማሩ ሳይሆን እስከመጨረሻው በመፅናት ድምዳሜው ላይ በማድረሱ ነው።

አላህ سبحانه وتعالى በክቡር ቁርኣን እንዲህ ይላል፦

وَاعْبُدْ رَبَّكَ حَتَّىٰ يَأْتِيَكَ الْيَقِينُ
"እርግጠኛው (ሞት) እስኪመጣህ ጌታህን ተገዛ!"
አል ሒጅር: 99

ሠ/ የአላህ መልዕክተኛ ﷺ የሥራን ተቀባይነት መሥፈርት ያደረጉት በመጨረሻዎቹ በድምዳሚያቸው ላይ ስለመሆኑ እንዲህ ብለዋል:-

"የሥራዎች ተቀባይነትና ትክክለኝነት በመጨረሻቸው ብቻ ነው። "

ረ/ ፅናት የመልካም ተግባር (የረመዳናችን)ተቀባይነት መስፈርቱ ነው

"የአንድ መልካም ሥራ ምንዳው (ጀዛእ) (የተቀባይነት ምልክቱ) ከዚያ (ከመልካሙ ሥራ በኋላ) ቀጣይነት ያለው ጥሩ ተግባር ማስከተሉ ነው።

"የመጥፎ ሥራ ቅጣቱ(ጀዛው) ክፉ አድራጎትን (መጥፎን ተግባር) ማስከተሉ ነው። "
ሐሰነል በስሪ رحمه الله

ልብ ያለው ልብ ይበል

ፅናት የሙእሚን ባህሪይ ሲሆን
ወረተኝነት የሙናፊቅ ባህሪ ነው።

ይህች ዓለም

የውጣ ውረድ
የመነሳትና የመውደቅ
የትግል ሜዳ ናት

መልካምን ወደራሳችን በማምጣት ማንነታችንን (ስብእናችንን) በኢማን ማጠንከሩ ባንዳፍታ የምናመጣው ሳይሆን ቀስ በቀስ በሂደት የሚመጣ ነው።

አንዴ ተነስተን በዚያው መውደቅ ሳይሆን ፦

አየተነሱ እየወደቁ
ተስፋ ሳይቆርጡ
በፅናት መቀጠል ነው፡፡

وَالَّذِينَ جَاهَدُوا فِينَا لَنَهْدِيَنَّهُمْ سُبُلَنَا ۚ وَإِنَّ اللَّهَ لَمَعَ الْمُحْسِنِينَ

እነዚያም በኛ መንገድ የታገሉ መንገዳችንን በርግጥ እንመራቸዋለን፡፡
በርግጥም አላህ ከመልካም ሰሪዎች ጋር ነው፡፡

አላህ ፅናትን ይስጠን

@tezkiraChannel
223 views06:18
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2020-06-12 01:27:53 "እነሆ ልታውቁት የሚገባ ነገር ቢኖር
በነቢያችን ሙሐመድ ﷺ አንድ ሙስሊም ሰለዋት ያበዛ እንደሆነ

አላህ ቀልቡን ኑር ያደርግለታል
ወንጀሉን ይምረዋል
ልቡን ያሰፋዋል
ገዳዪን ያገራለታል(ሀኔታውን ያመቻችለታል

"ስለዚህ

ሰለዋት አብዙ
አላህ ከትክክለኞቹ
ኡመታቸው አንዲያደርጋችሀ

በሱናቸው ላይ እንዲያውላችሁ

በቀያማ ቀን አብሯቸው እንድትሆኑ
ሰለዋት አብዙ

{ኢብነል ጀውዚይ رحمه الله}

ቡስታኑል ዋዒዚ,,ን 1/292


@tezkiraChannel
‏.
326 views22:27
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2020-06-11 13:01:24 በእኔና በአንተ ሞት
ምን ነገር በሰዎች ላይ ይጎድላል
ምንስ የሚታጣ ነገር አለ ???

❍ ሞት የሰው ልጆች ሁሉ የሚቀምሱት በጣም ለብዙዎቹ መራራ በጣም ለጥቂቶቹ ደግሞ አሳማሚና ጣፋጭ የሆነ ነገር ነው። በሞቱ አለምን የሚጎዳና ብዙ ነገርን የሚቀንስ ሰው እንዳለ ሁሉ በሞቱ አለምን አንዳች ነገር የማይጎዳና ምንም የማይቀንስ ሰው አለ።

❍ ከመቃብር ስር ሆነው በመልካም ስራቸውና ባበረከቱት በጎ አስተዋፅኦ ታሪክ ከመቃብር በላይ የሚያስታውሳቸው ሰዎች እንዳሉ ሁሉ ከመቃብር በላይ ሆነው የሚፈፅሙት መልካም ስራና የሚያበረክቱት በጎ አስተዋፅኦ ባለመኖሩ ሰው ከመቃብር ስር እንዳሉ የሚያስባቸው ሰዎች አሉ።

❍ በህይዎት መኖሩ ለራሱ፣ ለቤተሰቡ፣ ለማህበረሰቡ በጣም ብዙ የሆነን ነገር የሚፈጥር ሰው እንደሚገኝ ሁሉ በህይዎት መኖሩ ለራሱ፣ ለቤተሰቡ፣ ለማህበረሰቡ ምንም አይነት ጥቅም የሌለው፤ መኖሩ ከሞቱ እኩል የሚሆንበትና የሚመዝንበት ሰው አለ።

ሞታችን ሰዎችን ይጎዳል
ወይንስ እኛኑ ብቻ ይጎዳል.??

ሞታችን ብዙ ነገርን ያሳጣል
ወይንስ እኛኑ ብቻ ያሳጣል.??
╔═════════╗
Length - 08 : 39 Min
Size - 3.9 MB
╚═════
201 views10:01
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2020-06-11 12:58:28
341 views09:58
ክፈት / አስተያየት ይስጡ