Get Mystery Box with random crypto!

ተዝኪራ - ትውስታ እና አደራ ስለ አኺራ - التذكرة فى الأمور الآخرة

የቴሌግራም ቻናል አርማ tezkirachannel — ተዝኪራ - ትውስታ እና አደራ ስለ አኺራ - التذكرة فى الأمور الآخرة
የቴሌግራም ቻናል አርማ tezkirachannel — ተዝኪራ - ትውስታ እና አደራ ስለ አኺራ - التذكرة فى الأمور الآخرة
የሰርጥ አድራሻ: @tezkirachannel
ምድቦች: ያልተመደበ
ቋንቋ: አማርኛ
ሀገር: ኢትዮጵያ
ተመዝጋቢዎች: 158

Ratings & Reviews

4.00

3 reviews

Reviews can be left only by registered users. All reviews are moderated by admins.

5 stars

2

4 stars

0

3 stars

0

2 stars

1

1 stars

0


የቅርብ ጊዜ መልዕክቶች 4

2020-06-07 19:23:04 ከረመዳኑ በኋላ ምን? …
ክፍል 2

ረመዳንን በብዛት ቁርኣንን ስንቀራ ፣ ዚክር ስናደርግ ፣ ሰደቃ ስንሰጥ ፣ ስናበላ ፣ ስናጠጣ ፣ በተራዊሕና በተሐጁድ ለይል ስንቆም እንዲሁም ባብሮነት የመተጋገዝ መንፈስ የኸይር ሥራዎች ላይ በመሳተፍ ስንረባረብ ነበር።

ከዚያስ?

ከዚያማ በነበርንበት ሙሉ ለሙሉ እንኳን ባይሆን በከፊሉ ትንሽ ትንሽ እየሠሩ እንኳን በዒባዳው ላይ መገኘቱ አላህ سبحانه وتعالى ላለላቸው ፣ ላዘነላቸው እንጂ ለሌሎቻችን የገራልን አይመስልም፡፡ አንዳንዶቻችን ወደ ኸይር መሯሯጡን እርግፍ አድርገን ትተነው ረመዳንን የሥራ መደምደሚያና የመጨረሻው ፌርማታ ያደረግነው ይመስላል።

ዒባዳው ላይ በርትቶ መገኘቱ ይቅርና ተነሳሽነቱም ተቀዛቅዞ ኸይር ሥራን የተውን ስንቶቻችን ነን?

የአንድ ሙእሚን የመልካም ሥራ ማብቂያ ከሞት ውጪ ምንም አይደለም!

አልሰማንም ወይ?

አላህ سبحانه وتعالى በክቡር ቁርኣን እንዲህ ይላል፦

وَاعْبُدْ رَبَّكَ حَتَّىٰ يَأْتِيَكَ الْيَقِينُ
"እርግጠኛው (ሞት) እስኪመጣህ ጌታህን ተገዛ!"
አል ሒጅር: 99

ይህንን የቁርኣን አንቀፅ አላስተዋልንም?

የዕድገትና የክስረት ሚዛኑ በመፅናትና በወረተኝነት ነው የሚለካው!

"የአንድ መልካም ሥራ ምንዳው (የተቀባይነቱ ምልክት) ከዚያ (ከመልካሙ ሥራ) በኋላ ቀጣይነት ያለው ጥሩ ተግባር ማስከተሉ ሲሆን የመጥፎ ሥራ ምንዳው ደግሞ ክፉ አድራጎትን ማስከተሉ ነው። "

@tezkiraChannel
217 views16:23
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2020-06-03 19:56:02
221 views16:56
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2020-06-02 13:35:52 ለስኬታማ ቤተሰብ

አሁኑኑ ጆይን አድርገን ትምህርቶችን በመከታተልና ቤታችንን ኢሰላማዊ በማድረግ ትዉልድን እናድን!

t.me/nesiha_ouserya
244 views10:35
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2020-06-02 02:34:55 ሙስሊሞች በሙሉ -
እውነቷን እንወቅ

ከሐቋ እንግጠም -
ሌላን እንጠንቀቅ

ማስረጃን እንውደድ -
ይቅር መረበሹ

ለሸዋል ፍቺ
በዓሉን ለሚሹ

የዒድ ትልቅ
እንጂ- የለውም ትንሹ!

መፈብረክ አንወድም -
ከሱናው ነን እኛ

መመሪያ ደርሶናል -
ከሰማዩ ዳኛ

ሐቁን እንሰብካለን -
ሂዳያን አንሰርቅም

ዒዳችን ታላቅ ነው -
ትንሽ ዒድ አናውቅም!

t.me/tezkiraChannel
219 views23:34
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2020-05-31 06:11:08 ዒድ ሲባል የራሱ የሆነ

(የዒዱ )



* ኹጥባ
* ሰላት

አለው።

ሁለቱን ዒዶች
(ዒደል ፊጥርና ዒደደል አድሃን)

በሰፊው ሜዳ ወይም በስታዲየም ከሰገድን…

ትንሹን ዒድ

በትንሽ ሜዳ ወይም
በትንሿ አስታድየም
ልንሰግድ ነው

ይህን ለማለት ካላስቻለ
ፈፅሞ ዒድም አይደለ




ጥንቃቄን እንደግፍ
በማስረጃ እንሳተፍ
በቁርኣን እንሳተፍ
በ ሀዲስ እንታቀፍ



ዒባዳ ያለ ማስረጃ
ያደርጋልና ገልጃጃ
ካልተገኘ ማስረጃ
እሺ ሳይሆን እንበል እንጃ

ይሄኔ ያስተውሉ

ጥምረት ከሌለን
ማስረጃን ለመከተሉ

ሰው ያለውን
በጭፍን የመከተሉ

መዘዝ ነው
ለአንጃነት ለመከፋፈሉ




@tezkiraChannel
236 views03:11
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2020-05-30 08:41:15
ኡስታዝ ጀማል ያሲን ራጁ
209 viewsedited  05:41
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2020-05-28 07:20:55
****,,,**,,,****

ከረመዳን ቡኋላ ምን,,,,,,,,?

1/ደስተኛ መሆን

ረመዳንን ለማጠናቀቅ ስለተወፈቅን ይህን ታላቅ ፀጋ በማግኘታችንደስተኛ ልንሆን ይገባል።
አላህ سبحان وتعال ክቡር በሆነው ቃሉ እንዲህ አለ : -

"በአላህ ችሮታ(ትሩፋት)ና በእዝ ነቱ ይደሰቱ። በዚህም መክንያት ይደሰቱ ። ከሚሰበስቡት ሀብት በላጭ ነው በላቸው"
አር ረዕድ:58

ረሱል - ﷺ - እንዲህ ብለዋል፦
" ለፆመኛ ሁለት ደስታ አለው
አንደኛው ደስታ በሚያፈጥርበት (ፆሙን በሚያጠናቅቅበት) ጊዜ

ሌላኛው ደስታ ከአምላኩ ጋር በሚገናኝበት ጊዜ። "

1/በሚያፈጥርበት ጊዜ ያለው ደስታ

ሀ/ የረመዳንን ፆም የዕለቱን ቀኑን ሙሉ ዒባዳ እና ባጠቃላይ የወሩን ሙሉውን ሳይበላሽበት ወይም ችግር ሳይገጥመው ባግባቡ ሳይጎልበት በማጠናቀቅ ለማፍጠር በመብቃቱ

ለ/(እና) ከተከለከለው ምግብ መጠጥና ,,, ተፈቅዶለት ስለ በላና ስለ ጠጣ ።

ነፍስያ ከተከለከለችው ነገር ሲፈቀድላት ደስተኛ ትሆናለች
ይህ ደስታ አጅር የሚያስገኘው ፁሞ ለማፍጠር በመጓጓቱ ነው።

ረሱል - ﷺ - እንዲህ ብለዋል፦
"ሰዎች ፈጡርን እስካቻኮሉና ስሑርን እስካዘገዩ(መጨረሻ ወቅት ላይ ሲበሉ) በመልካሙ ይዘወትራሉ(በኸይር ላይ ሆነው ይቆያሉ) ።"

በቀኑ ክፍለ ጊዜ የከለከለውን ምሽቱ ክፍለ ጊዜ ተፈቀደለት እንዲያው ም በፍጥነት መፍጠራ ቸውን ወደደላቸው።

ፆመኛ ስው ምግብ መጠጡን ,,,, ,,, የተወው ለአላህ ብሎ እስከሆነና በተመገበ ቁጥር አላህን ካመሰገነ በማፍጠረም አጅር ያገኛል።

ረሱል - ﷺ - እንዲህ ብለዋል፦
"ባሪያው አንዲትን ጉርሻ ጎርሶ ሲያመሰግነው ፣ አንዲትን ጉንጭ ጠጥቶ ሲያመሰግነው አላህ ይወድለታል።"

ረሱል - ﷺ - እንዲህ ብለዋል፦
"ተመግቦ አመስጋኝ የፁሞ ታጋሽ (ሰብረኛ) ደረጃ አለው።"

በማፍጠሪያው ሰዓት ዱዓው ተቀባይነት አለው።

ረሱል - ﷺ - እንዲህ ብለዋል፦
"አንድፆመኛ በማፍጠሪያው ወቅት ተመላሽ የማይሆን(ፍፁም ተቀባይየሆነ) ዱዓ አለው።"

በመብላቱ,,, በዒባዳ ላይ ለመጠናከር ብሎ ከሆነ አጅር አለው።

"እኔ ከአልጋዬ ላይ ተኝቼ አጅር የማገኝበት ዒባዳ(አምልኮት) ምንኛ ያማረ የሚያስደስት መገዛት ነው። "
(ሐፍሳ رضي الله عنها)

" ፆመኛ ሰው ዒባዳ ላይ ነው ምንም እንኳ በአልጋው ላይ ቢተኛም። "
( رحمه الله አቡል ዓሊያ)

ይህን የተረዳ በማፍጠሪያው ጊዜ ደስታው ከላይ በተገለፀው መልኩ ሲሆን:የደስታው ምንጭ ከአላህ ችሮታና እዝነት በመሆኑ ነው።

በመፆሙ እየተበሳጨ አያጉተ መተመ በማፍጠሩ የሚደሰት ሰው አጅር የለውም።

2/ከአላህ ጋር ሲገናኝ ያለው ደስታ

ለፆመኞች የተዘጋጀውን ስፍር ቁጥር የሌለውን ታላቅ ምንዳ በሚያገኝ ጊዜ,,, ይደሰታል

ፆመኞች እንጂ ሌሎች የማይገቡበትን የረያንን ጀነት በሚገባ ጊዜ ይደሰታል

3/የፆመኞች እርከን (ደረጃዎች)
ሁለት ደረጃዎች ናቸው

1ኛውከአላህ ዘንድ ያለውን ታላቅ አጅር ለማግኘት ከምግብ መጠጥና ስሜት ራሳቸውን አቅበው ከርሱ ምንዳን ሸምተው ትርፋማ የሆኑት ሲሆኑ

ሌሎቹ ፆመኞች በዚህ ዓለም ባዱንያ ላይ ስለ አላህ ብለው በርሱ መንገድ ላይ ሁነው ከሀራም ነገሮች ታቅበው በመፆም የአኼራ ዒድ ሲደርስ በጀነት አላህ سبحان وتعالى ባዘጋጀላቸው ዓይን አይቶ የማያውቀውን ፣ ጆሮም ሰምቶ ያላወቀውንና ከሰው ልቦና ውስጥ ውል ማይለውን ፀጋ በልዩ መስተንግዶ በማፍጠራቸው ይደሰታሉ።

ውድ ወንድሜ

ነገ በአኼራ የማፍጠሪያ ዒዳችን ቋሚና ዘላቂ የሆነ የዘላለም ደስታ ለማግኘት ዛሬ ከስሜት ዝንባሌያችን እንፁም

'ገና ነው ፤ እደርስበታለሁ' የሚለውን ከንቱ ምኞት ከራሳችን እናሽቀንጥር፡፡ ከቀኑ ቀሪው ክፍለ ጊዜ ሊጠናቀቅ ሰዓቱ ረፋፍዷል፡፡ ጊዜ የለንም ገና ነው እደርስበታለሁ የሚለውን ከንቱ ምኞት ትተን ከቀኑ የቀረን ጥቂቱን ብቻ መሆኑን እናስታውስ።

መቼ እንደምንሞት አናውቀውም።

በዚች አላፊ ጠፊና ረጋፊ የዱንያ ህይወታችን ፁመን በነገው ዘላለማዊ እውነተኛ ህይወት በአኼራው የማፍጠር አውነተኛ መስተንግዶ ደስተኞች እንሁን

አላህ ደስተኛ
ከሚሆኑት ያድርገን
ኣ,,ሚ,,,,,ን


t.me/tezkiraChannel
240 viewsedited  04:20
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2020-05-25 23:29:12 6ቱንሸዋል ወይም ዓሹራእ በመፆም ለረመዳንን አንዳንድ ቀናት ቀዷእ መነየት ይቻላልን

6ቱን መፆም ለረመዳን ቀዳእ ማድረግ አይቻልም።
ምክንያቱም 6ቱን መፆም ረመዳንን መፆሙ መሠረቱ በመሆኑ በርሱ ላይ የቆመ ነው እንደ ፈርድ ሰላት ለራቲባ (ለቋሚ ሱና/ቀብሊያና በዕዲያ/) ያለውን ዓይነት ነው።

ረሱል - ﷺ - እንዲህ ብለዋል ፦

[[ ረመዷንን የፆመ ከዛም ረመዷኑን ከሸዋል ስድስትን ቀን (በመፆም) ያስከተለው ከሆነ ፤ ልክ እንደ አመት ፆም ይሆንለታል። ]]

በዚህ ሐዲስ ሸዋልን የረመዳን ተቀጥላ መሆኑን ያመላክታል።; ተቀጥላ(የሸዋሉ) ምንም ከዋናው (ከረመዳን) አያብቃቃም።

# ቀዳእ ላለበት 6ቱን ፆም ከቀዳእ ማስቀደሙ በተመለከተ በርካታ ጥያቄዎች ይቀርባሉ።

#መልሱ:-
ይህ ምንም አይጠቅምም ማለ ትም:-ከረመዳን ቀዳ 6ቱን ማሰቀደሙ አጅር አያስገኝም:
ነቢያችን صلى الله عليه وسلم
አጅር ለማግኘት ያስቀደሙት ፈርዲን መፆም ነውና።

ረሱል - ﷺ - እንዲህ ብለዋል ፦

[[ ረመዷንን የፆመ ከዛያም ረመዷኑን ከሸዋል ስድስትን ቀን (በመፆም) ያስከተለው ከሆነ ልክ እንደ አመት ፆም ይሆንለታል። ]]



በዚህ ሐዲስ ቀዳ ያለበት ሰው ረመዳንን የፆመ ሰው አይባልም። ይልቁንም ወሩን በወቅቱና ቀዳውን ፁሞ መጨረስ አለበት።
ከዚያም 6ቱን ይፆማል።


#የዐሹራን ፆም በመ ፆም ቀዳእ ቢነይት ቀዳ ውንም መክፈል የዕለቱንም የአሹራውንም አጅር ያገኛል።

"ሸይኽ ሷሊህ ብኑ ዑሰይሚን"

http://iswy.co/e292j5
200 views20:29
ክፈት / አስተያየት ይስጡ