#4_ነገሮችን_ምንጊዜም_ቢሆን_አትርሳ!
#አንድ
መጥፎ ቀን ማሳለፍ ማለት ሙሉ ህይወትህ አብቅቶለታል ወይም ቀሪ ህይወትህ መጥፎ ይሆናል ማለት አይደለም።
#ሁለት
ፍጹም መሆንን ከራስህ አትጠብቅ፤ ነገር ግን በምትችለው ሁሉ የተሻለና ምርጥ ለመሆን ሁሌም የነቃ ሁን!
#ሶስት
ሰዎች ስላንተ ላላቸው አሉታዊ አስተሳሰብ አንተ ሃላፊነቱን መውሰድ የለብህም። ያ ችግርህ ሊሆን በፍጹም አይገባም።
#አራት
ሁሌም እያንዳንዷን በህይወት የምታጋጥምህ ፈተና አንድ እርምጃ ወደ ፊት የምታራምድህ፣ ለስኬትህ የምታቀርብህ መንደርደሪያ በመሆኗ፣ በፍጹም ተስፋ ለመቁረጥ ምክንያት አድርገህ እንዳታያት።
ፈገግታ ከፊትህ የማይለይ ለሌሎች ሰላምን የምታንጸባርቅ ሁን!!!
#የስኬት_አቡጊዳ መጽሐፍ በገበያ ላይ
በየመጽሐፍት መደብሩና በአዟሪዎች እጅ ይገኛል
(በየቀኑ አነቃቂ መልእክቶችን፣ ከምናሳትማቸው መጽሐፍት ፒዲኤፍ፣ የገንዘብና የመጽሐፍት ሽልማቶችን ለማግኘት የፌስቡክና ቴሌግራም ገጾቻችንን ይቀላቀሉ።)
Telegram- https://t.me/teklu_tilahun
Facebook- https://www.facebook.com/booklandbook/?