Get Mystery Box with random crypto!

Tariku Abera

የቴሌግራም ቻናል አርማ tarikuabera — Tariku Abera T
የቴሌግራም ቻናል አርማ tarikuabera — Tariku Abera
የሰርጥ አድራሻ: @tarikuabera
ምድቦች: ሃይማኖት
ቋንቋ: አማርኛ
ተመዝጋቢዎች: 6.00K
የሰርጥ መግለጫ

ኦርቶዶክሳዊ የወንጌል አገልግሎት

Ratings & Reviews

2.50

2 reviews

Reviews can be left only by registered users. All reviews are moderated by admins.

5 stars

0

4 stars

0

3 stars

1

2 stars

1

1 stars

0


የቅርብ ጊዜ መልዕክቶች 2

2022-08-29 10:09:59 † ሰማዕቱ ቅዱስ ጊዮርጊስ †

† ቅዱስ ጊዮርጊስ ታማኝ የክርስቶስ አገልጋይ ነው።†

★ሼር በማድረግ የቅዱሳንን ክብር እንመስክር ★

መ/ር ታሪኩ አበራ

★ Saint George The Martyer★

ቅዱስ ጊዮርጊስ ከክርስቲያን ቤተሰብ የተገኘ ወጣት ነው። በሕይወት ዘመኑ እግዚአብሔርን ደስ ያሰኘ፣ የወጣትነት ዘመኑን እግዚአብሔር እንዲከብርበት በቅድስና የኖረ፣ ከባድ የሰማዕትነትን ተጋድሎ በጽናት የፈጸመ ታማኝ የክርስቶስ ጃንደረባ ነው። ቅዱስ ጊዮርጊስ ፍቅርን፣ትህትናን፣ሰብአዊ ርኅራኄንና በጎነትን ወላጅ እናቱ ከቅዱሳት መጻሕፍት በሚገባ ታስተምረው ስለነበር ለሰዎች ሁሉ እጅግ መልካምና ቀና አሳቢ ወጣት ሆኖ አደገ። የነበረውን መልካም ባህሪና በጎ አስተሳሰብ ተመልክተውም በሀገሩ ላይ ለሕዝብ ዕንባ ጠባቂነት አድርገው ለሹመት እንዳበቁት የወጣትነት ዘመን ታሪኩ በሰፊው ይገልጻል።ቅዱስ ጊዮርጊስ ገና በወጣትነቱ የክርስቶስ ፍቅር በልቡ የተሳለበት፣ የመስቀሉ ውለታ በኅሊናው የታተመበት ጠንካራ ክርስቲያን ነበር።በዚህ ዘመን በዘር ፣በብሔር ተከፋፍለን በዓለም ርኩሰት ውስጥ ለወደቅን ወጣቶች ብዙ ቁም ነገር ሕይወቱ ያስተምረናልና ጽሑፋን በጥንቃቄ እናንብ።

#Early life
George was born in Cappadocia, an area which is now in Turkey, in the 3rd century; that his parents were Christians; and that when his father died, George's mother returned to her native Palestine, taking George with her. George became a soldier in the Roman army and rose to the rank of Tribune.

ቅዱስ ጊዮርጊስ በጥንትዋ ካፓዶቂያ በአሁኗ ቱርክ በሦስተኛው መቶ ክፍለ ዘመን ከክርስቲያን ቤተሰቦች ተወለደ።አባቱ በሞት ሲያልፍ እናቱ ቅዱስ ጊዮርጊስን ይዛ ወደ ትውልድ ሀገሯ ወደ ፍልስጠኤም ምድር ተመለሰች።ጊዮርጊስም በዚያው አደገ ኋላም የሮም ወታደር ሆኖ ሳለ ለሕዝብ ዕንባ ጠባቂነት ማዕረግ ተሾመ።

#Persecution of Christians
The Emperor of the day, Diocletian (245-313 AD), began a campaign against Christians at the very beginning of the 4th century. In about 303 AD George is said to have objected to this persecution and resigned his military post in protest.

በወቅቱ የሮም ግዛት ንጉሥ የነበረው ዲዮቅልጢያኖስ ክርስቲያኖችን ለማሳደድ ከፍተኛ ዘመቻ ጀመረ። በ303 ዓ.ም ቅዱስ ጊዮርጊስ ንጉሡ በክርስቲያኖች ላይ የሚፈጽመውን ማሳደድ እንዲያቆም አጥብቆ ይቃወመ ስለነበር የነበረውን ስልጣን በተቃውሞ ለቀቀ።

እዚህ ላይ ማስተዋል ያለብን ንጉሡ ሮም ታስተዳድራቸው በነበሩ ሀገራት ሁሉ ላይ ክርስቲያኖችን ያስጨንቅ ያነበረው ጣዖት አምላኪ በመሆኑ ነው።በግዛቱ ላይ ታላቅ አምባገነናዊ አዋጅ አውጆም ነበር «አብያተ ክርስቲያን ይትሃጸዋ አብያተ ጣዖታት ይትርሃዋ»« አብያተ ክርስቲያናት ይዘጉ አብያታ ጣዖታት ይከፈቱ» የሚል መመሪያ በየሀገሩ አስተላለፈ ይህንን የተቃወሙ ክርስቲያኖችን ሁሉ ወታደሮች ይዘው በግፍ እያሰቃዩ እንዲገድሏቸው፣ሰውነታቸውን ሰም እየለቀለቁ በአደባባይ እንደ ጧፍ እንዲያቀልጧቸው፣ከአንበሶች ጋር እያታገሉ ሰባብረው እንዲበሏቸው ያደርግ ነበርና ቅዱስ ጊዮርጊስ ይህንን ክፉ የአጋንንት ሥራ አጥብቆ ተቃወመ።
ክርስቲያኖች ልብ በሉ ክርስትና እኛ ዘመን የደረሰው አልጋ በአልጋ ሆኖ አይደለም በብዙ መከራና ስቃይ ስለ ክርስቶስ ፍቅር ዋጋ እየተከፈለበት ነው።፣የክርስቶስን ጌትነትና አዳኝነት ሳይፈሩና ሳያፍሩ በነገሥታትና በአሕዛብ ፊት ወንጌልን በሰበኩ እውነተኛ አማኞች ታላቅ ተጋድሎ ዛሬ በክብር የምንጠራበት ክርስትና የጨለማውን ዘመን በመንፈስ ቅዱስ ኃይልና ሥልጣን ተሻግሮ በብርሃን ሰረገላ የክብሩን ወንጌል ለእኛ አድርሷል።የቀደሙ ክርስቲያኖች ወንጌልን በአፍ ብቻ ሳይሆን በሕይወታቸው የኖሩ፣ በደሙ የዋጃቸውን ጌታ በደማቸው ያከበሩ ታላቅ የእምነት አርበኞች ናቸው።

#Torture and martyrdom
George tore up the Emperor's order against Christians. This infuriated Diocletian, and George was imprisoned and tortured - but he refused to deny his faith.

ቅዱስ ጊዮርጊስ በክርስቲያኖች ላይ የወጣውን የንጉሡን ትህዛዝ ቀዶ ስለጣለው ይህ ድርጊት ንጉሥ ዲዮቅልጢያኖስ አጅግ አናደደው ጊዮርጊስ እስር ቤት ውስጥ እንዲጣልና በዚያም ከፍተኛ ስቃይ እንዲፈጸምበት አደረገ፤ ሰማዕቱ ግን እምነቱን ፈጽሞ አልካደም።

In the stories George have been tortured in a number of gruesome and hideous ways. He was forced to swallow poison; crushed between two spiked wheels; boiled in a cauldron of molten lead. None of these attempts killed him and his wounds were healed in the night by Christ himself.

በታሪክ እንደተመዘገበው ቅዱስ ጊዮርጊስ እጅግ አሰቃቂና አስከፊ በሆነ መንገድ በርካታ ስቃዮችን ተቀብሏል።መርዝ እንዲጠጣ አስገድደውታል፣ሁለት የሾለ ብረት ባለው መንኮራኩር መሐል አስገብተው ሰባብረውታል፣በትልቅ ድስት ውስጥ የቀለጠ ብረት አፍልተው ጊዮርጊስን እዛ ውስጥ ጨምረው አሰቃይተውታል።ሰማዕቱን ለመግደል ያልሞከሩት ሙከራ አልነበረም፤ነገር ግን በድንቅ ተአምር ሌሊት ቁስሉን ክርስቶስ ራሱ ይፈውሰው ነበር።

George was told his life would be spared if he would offer sacrifice to the Roman gods. The people assembled to see him do so but instead George prayed to the Christian God.

ሰማዕቱ ለጣዖት መስዋዕት እንዲያቀርብ በንጉሡ በተገደደ ጊዜ ቅዱስ ጊዮርጊስ ግን ለሮም ጣዖታት መስዋዕትን ከማቀረብ ይልቅ ሕይወቴ ቢያልፍ እመርጣለሁ ብሎ ተናገረ። ሕዝቡም በእርሱ ላይ የሚሆነውን ለማየት ተሰብስበው ሲመለከቱ ፤ጊዮርጊስ ግን የክርስቲያኖች አምላክ ወደ ሚሆን ወደ እግዚአብሔር ይጸልይ ነበር።

Immediately, fire came down from heaven, an earthquake shook the ground, and priests, idols, and the temple buildings were destroyed. However, by this time it was God's will that St. George should die for his faith, and he was beheaded without further trouble

እየጸለየም ሳለ ወዲያውኑ እሳት ከሰማይ ወደቀ፣ታላቅ የምድር መናወጥም ሆነ፣የጣዖት ካህናቱ፣ጣዖታቱና የጣዖታቱ መቅደሶቹ ሁሉ ወደሙ።ሆኖም እግዚአብሔር ሰማዕቱ ከዚህ በላይ እንዲሰቃይ አልፈለገምና ስለ እምነቱ ጽናት በሰማዕትነት ክብር እንዲያልፍ ሆነ።
1.0K views07:09
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-08-28 10:16:09
1.4K views07:16
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-08-28 10:15:43 ★ አሳዛኝ ዜና ★

★ የት*ግ*ራ*ይ ወታደሮች እባካችሁ ልብ ግዙ ቅድስት ቤተክርስቲያን አልበደለቻችሁም የምትፈጽሙትን ግፍ አቁሙ!! ኦርቶዶክሳውያን እርስ በርስ እንድንተላለቅ ለሚፈልጉ ቆሻሻ ፓለቲከኞች መጠቀሚያ አትሁኑ በዓቢይ አህመድ በኩልም ሆነ በእናንተ ክልል በኩል ብዙ ፀረ ኦርቶዶክስ ከሃዲ ፓለቲከኞች አሉ።ለእነርሱ መጠቀሚያ አትሁኑ።እግዚአብሔር ይፈርዳል አይዘገይም።★

የህ*ወ* አ*ት ቡድን ዓለም በቃኝ ብለዉ በዋልድባ ገዳም የሚገኙ የበቁ አባቶች ላይ ስቃይና እንግልት መፈፀሙንና ገዳሙን መዝረፉን ቀጥሏል ።

በትላንትናው ዕለት ወደ ገዳሙ በመግባት በርካታ ንዋየ ቅድሳትን ከመዝረፋ በተጨማሪ ቅዱሳት ስዕሎችን ማቃጠላቸዉን ፣ አባቶችን ባገኙት ነገር መደብደባቸዉን፣ ክብረ ነክ ድርጊቶችን መፈፀማቸዉን ከስፍራው ባገኘነው መረጃ ለማረጋገጥ ችለናል ።

ይህ ገዳም በጣም ሰፊ ሲሆን የክርስቶስን መከራ በልባቸው እያሰቡ ዓለምንና ምኞቱን ሁሉ ንቀው በጾም ፣በጸሎት፣በስግደት ተወስነው ስለሃገር ና ስለ ሕዝብ የሚጸልዩ በርካታ መናንያን ያሉበት ገዳም ነው። የአራቱ ገዳማት መገኛ ከሆኑ ከሰንሰለታማ ተራሮች በስተጀርባ በኩል ባሉ ተራሮች የሚመጣዉ ጨፍጫፊ ቡድን በተደጋጋሚ እያጠቃዉ ይገኛል ። በመነኮሳቱ ላይም ከፍተኛ ግፍ እየፈጸሙባቸው ነው።

★ የት*ግ*ራይ ሕዝብ ራሱ ይህንን አጸያፊና ነውረኛ ተግባር በይፋ ሊቃወምና ሊያወግዝ ይገባል።እስከ መቼ በሃይማኖት ላይ ግፍ ሲፈጸም ይኖራል።በት*ግ*ራ*ይ ክልል ውስጥ ፀረ ኦርቶዶክስ የሆኑ ፓለቲከኞች፣ካድሬዎች፣የጦር አመራሮችና የጦር ሠራዊት አሉ በተደጋጋሚ በቅድስት ቤተክርስቲያን ላይ ጥቃት እንዲፈጸም የሚያደርጉ እነዚሁ ሃይማኖት የለሽ ከሃድያን ናቸው። ለስሙ ከሃይማኖተኛ ሕዝብ መሐል እየኖሩ በልባቸው ግን እግዚአብሔርን የካዱ፣የሃይማኖት ዕውቀትና እምነት የሌላቸው አሁንም ድረስ የኮሚኒስት አስተሳሰብ አዕምሯቸውን ደፍኖት ያለ ከሃድያን በት*ግራ*ይ ክልል በብዛት አሉ። የት*ግ*ራ*ይ ሕዝብ ልብ በል የዓቢይ አህመድ መንግሥትም ሆነ በእናንተ ክልል ውስጥ ያሉ ሃይማኖት የለሽ አስመሳይ ከሃድያን ሁለቱም ፀረ ኦርቶዶክስ የአጋንንት ማደሪያዎች ናቸው፤ ስለሆነም ሁለቱም የቤተክርስቲያን የጋራ ጠላቶች መሆናቸውን አውቀን አጥብቀን ልንታገላቸውና ልናስወግዳቸው ይገባል።የዛኔ ነው ክልል ት*ግ*ራ*ይም ሆነ መላው ኢትዮጵያ ሰላም የምታገኘው እነዚህን የቤተክርስቲያን ነቀርሳዎች ተሸክመን መቼም ሰላም አናገኝም።

የ*ት*ግ*ራ*ይ ሕዝብ በሌላው የኢትዮጵያ ሕዝብ እንዲጠላ እያደረጉ ያሉት እነዚሁ ነቀርሳዎች ናቸው ።ሕዝብ ሆይ ንቃና ነቅለህ ጣላቸው።

አንዳንድ የት*ግ*ራ*ይ ተወላጆች በፓለቲከኞችና በአክቲቪስቶች የአዕምሮ እጥበት/Brain wash / ስለተደረጉ በተደጋጋሚ ቅድስት ቤተክርስቲያን ላይ በትግራይ ወታደሮች ጥቃት እየተፈጸመ እያዩ መነኮሳትና ኦርቶዶክሳውያን ላይ ግፍ መፈጸሙን እየተመለከቱ የእኛ ሠራዊት ይሄን አያደርግም እያሉ ዓይኔን ግንባር ያድርገው በማለት ይጨቃጨቃሉ። ልብ በሉ ! እግዚአብሔር ደጋግሞ ሲቀጣችሁ እያያችሁ መማር ካልቻላችሁ ነገ በእያንዳንዳችሁ ሕይወት ውስጥ እግዚአብሔር ፍርዱን ማምጣቱ አይቀርምና ለቤተክርስቲያን ነቀርሳዎች አትከራከሩ ይልቅ ንቀሉና ጣሏቸው።

ሼር በማድረግ ለቤተክርስቲያን ድምጽ እንሁን።

መ/ር ታሪኩ አበራ

ለሌሎችም ሼር አድርጉት በየጉሩፑም ለጥፋት

የቴሌግራም ቻናሌ ቤተሰብ ይሁኑ።

ኦርቶዶክሳዊ የወንጌል አገልግሎት
https://t.me/TarikuAbera

ይህንን ፔጅ ላይክና ፎሎው በማድረግ ጠቃሚ ትምህርቶችንና መረጃዎችን ያግኙ።
1.3K viewsedited  07:15
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-08-24 22:07:02
2.3K views19:07
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-08-24 22:06:44 ★ መንግሥት በአስቸኳይ ይህንን የርኩሰት ፊልም ያስቁም !

★ ክርስቲያኖች ተጠንቀቁ!! " ፍልሰት" በሚል ርዕስ በቃና ቲቪ የሚተላለፈውን የሴት ሰዶማውያን /ሌዝብያን / ፊልም ፈጽሞ እንዳታዩ።★

እጅግ በሚያሳዝን ሁኔታ ኢትዮጵያ ውስጥ ለገንዘብ የሚስገበገቡ፣የራሳቸውን ጥቅም እንጂ በትውልድ ሕይወት ላይ የሚያመጣውን መጥፎ ተድኅኖ የማያገናዝቡ ስግብግብ ግለሰቦች ያገኙትን የውጪ ፊልም ሁሉ በገንዘባቸው እያስተረጎሙ ትውልድን እያረከሱ ሃገርን እያቆሸሹ ይገኛሉ።

ይህ "ፍልሰት" የሚል የማታለያ ትርጉም የተሰጠው ፊልም Orfaos da Terra ከሚል የስፔናውያን ቋንቋ የተወረሰ ሲሆን የፊልሙ ዋና ዓላማ በፍቅር ስም የሴት ሰዶማዊነትን/ሌዝቢያዊነትን /በትውልድ ልብ ውስጥ ለማስገባትና ወጣቶችን በረከሰ ተግባር ለማጨመላለቅ በምሥጢር ታቅዶ የተሰራ ፊልም ነው።ፊልሙ እጅግ በረቀቀ ዘዴ ወጣቶችን በመሳብ ልባቸውን እያንጠለጠለ የአዕምሮ እጥበት/Brain wash/ በማድረግ ሴት ከሴት ጋር በዝሙት መጨመላለቅን እንደ ዘመናዊነትና እንደ ሥልጣኔ ለማሳየት የተዘጋጀ አጋንንታዊ ፊልም ነው።

እኛ ኢትዮጵያውያን የተከበረ ባህል፣የተቀደሰ ሃይማኖትና የተለየ ሥርዐት ያለን ክቡር ሕዝቦች ነን ይህንን የተከበረ ማንነታችንን በፊልም፣በሙዚቃ፣በተለያዩ ፋሽኖች በማርከስ ሙሉ ለሙሉ ለሰይጣን ተገዥዎች ለማድረግና ከእግዚአብሔር ሕግ ለማውጣት የውጭና የውስጥ ባንዳ ጠላቶቻችን በብዙ ዓይነት ስልት እየተንቀሳቀሱ ስለሆነ ይህንን ትውልድ ገዳይ ርኩስ ተግባር ጠንክረን ልንታገልና ልናስቆም ይገባል።

ስለዚህም ይህ" ፍልሰት " በሚል ርዕስ በተከታታይ ለሕዝብ በይፋ በቃና ቲቪ የሚተለለፍ ነውረኛ ፊልም በአስቸኳይ መቆም አለበት። ወላጆች ልጆቻችሁን የሚያረክስ ፊልም ስለሆነ በአስቸኳይ እንዲቆም አድርጉ ልጆቻችሁም እንዳያዩ ከልክሉ ፣ክርስቲያኖች ይህ ዲያብሎስ ቀስ በቀስ እያታለለ ልባችሁን የሚያሸንፍበትና ከእግዚአብሔር እቅፍ የሚለይበት ወጥመድ ስለሆነ አጥብቃችሁ በመቃወም አስቁሙ ፈጽሞ እንዳታዩ። የሃይማኖት አባቶች፣መምህራነ ወንጌል ፣የሃይማኖት ተቋማት ጉባዔ ይህንን ትውልድ ገዳይ የርኩሰት ፊልም አጥብቃችሁ ተቃወሙና አስቁሙ።ውሃ ሲወስድ አሳስቆ ነውና እንደ ኖርማል ፊልም አቅልላችሁ የምታዩ ሰዎች መጨረሻ ላይ ሕይወታችሁን በለየለት ርኩሰት ውስጥ ገብቶ ስለምታገኙት ከወዲሁ ነቅታችሁ አቁሙ፣ተለዩ፣ተቃወሙ።

1ቆሮ 6 ፥9

"አመንዝራዎች፡ወይም፡ቀላጮች፡ወይም፡ከወንድ፡ጋራ፡ዝሙት፡
የሚሠሩ፡
10፤ወይም፡ሌባዎች፡ወይም፡ገንዘብን፡የሚመኙ፡ወይም፡ሰካሮች፡ወይም፡ተሳዳቢዎች፡ወይም፡ነጣቂዎች፡
የእግዚአብሔርን፡መንግሥት፡አይወርሱም።
11፤ከእናንተም፡አንዳንዶቹ፡እንደ፡እነዚህ፡ነበራችኹ፤ነገር፡ግን፥በጌታ፡በኢየሱስ፡ክርስቶስ፡ስም፡
በአምላካችንም፡መንፈስ፡ታጥባችዃል፥ተቀድሳችዃል፥ጸድቃችዃል።"

መ/ር ታሪኩ አበራ

ለሌሎችም ሼር አድርጉት በየጉሩፑም ለጥፋት

የቴሌግራም ቻናሌ ቤተሰብ ይሁኑ።

ኦርቶዶክሳዊ የወንጌል አገልግሎት
https://t.me/TarikuAbera
Valéria and Camila in Órfãos da Terra
Órfãos da Terra (Earth Orphans) is a Brazilian telenovela produced and broadcast by Rede Globo. It premiered on 2 April 2019, replacing Espelho da Vida. It tells the story of refugees and immigrants, mostly victims of the Syrian war, who have left their countries of origin for various reasons. Some of them try to rebuild their lives in Brazil and Europe, although they are consistently caught up by family secrets and problems of inheritance. Valéria Augusta and Camila Nasser came closer to each other quite naturally in the series, they are portrayed by Bia Arantes and Anajú Dorigon. This playlist is focused on their friendship/romance.
2.2K viewsedited  19:06
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-08-23 22:41:20
1.7K views19:41
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-07-13 17:43:01
927 views14:43
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-07-13 17:42:52 #ካቶሊክ_እና_ኢትዮጵያ

በ15ተኛው ክፍለ ዘመን በኦቶማን ቱርክ የሚደገፈውን የግራኝ አህመድን ወረራ ለመመከት ሲባል ካቶሊካዊቷ ሀገር ፖርቹጋል በኢትዮጵያው ንጉስ በዓፄ ልብነ ድንግል የቀረበላቸውን የእርዱኝ ጥያቄ ተከትሎ ወደ 400 የሚጠጉ በጄኔራል የሚመራ ጦር ወደ ኢትዮጵያ ስትልክ ቅድመ ድርድር አድርጋ ነበር ጦሯን ለእርዳታ የላከች ያም ድርድር የሃይማኖት ማስቀየር ድርድር ነበር ማለትም ንጉሱን ከኦርቶዶክስ ተዋህዶነቱ ወደ ካቶሊክ ካልቀየረ ምንም አይነት እርዳታ እንደማይሰጠው በፖርቹጋል በኩል ትዕዛዛዊ ድርድር ቀርቦ ነበር። ንጉሱም ልብነ ድንግል
በዚህ ተስማምቶ ነበር ነገር ግን የፖርቱጋል ጦር ኢትዮጵያ እስከሚደርስ ግን ንጉሰ ነገሥት አፄ ልብነ ድንግል በህይወት መቆዬት ዓልቻለም ነበር። አፄ ልብነ ድንግል ሲሞት ልጁ አፄ ገላውዲዎስ ስልጣነ መንበሩን ተቆጣጠረ እና የፖርቱጋል ወታደሮች ተቀብሎ ውጉያውን አጧጥፎ ግራኝ አህመድን ድል ነሱት። የዛን ጊዜ ጀምሮ ካቶሊክ ወደ ኢትዮጵያ በነፃነት መግባት ጀመረች።

ከዛም ወደ 16ተኛው ክፍለዘመን ስንሻገር ካቶሊክ በኢትዮጵያ ለመስፋፋት ያላትን የመጨረሻ እድል የሞከረችበት ክፍለዘመን ነበር። በዚህም ክፍለ ዘመን የነበረው ንጉስ አፄ ሱሲኒዮስ ወይም የአፄ ፋሲለደስ አባት ነበር ስልጣኑን የጨበጠው አፄ ሱሲኒዮስ ስልጣን ላይ እንደወጣ ለፖርቱጋል ወታደራዊ ሳይንስ
(ለጦር መሳሪያቸው) ተማረከላቸው የጦር ዘመናዊነታቸውን በጣም ወድዶት ነበረና። በዚህም ምክንያት እነርሱ የታጠቁት መሳሪያ በሙሉ ለመታጠቅ እለት በዕለት ጉጉት አደረበት። ከዛም ካቶሊካዊቷን ፖርቹጋልን የጦር መሳሪያ አስታጥቂኝ ጥያቄ አቀረበላት ፖርቹጋልም ለአንተ ጥያቄ መልስ እንድንሰጥህ ( እንድናስታጥቅህ ) ከፈለክ የእኛንም ጥያቄ ተቀበል አሉትና የእነርሱን ጥያቄ አቀረቡለት የእነርሱ ጥያቄ በመጀመሪያ አፄ ሱሲኒዮስ እምነቱን ከኦርቶዶክስ ተዋህዶነት ወደ ካቶሊክ ከለወጠ ዘመናዊ የጦር መሳያዎችን እንደሚያስታጥቁት ቃል ገቡለት።
አፄ ሱሲኒዮስም በፖርቹጋል የጦር መሳሪያ ዘመናዊነት ምክንያት ልቡ ታውሮ ነበርና ሃይማኖቱን ወደ ካቶሊክነት ለወጠና እና የናፈቃቸውን ዘመናዊ የጦር መሳሪያዎችን ታጠቀ። ከዛም እርሱ ብቻ ሃይማኖቱን ለውጦ አልቀረም የካቶሊክ እምነትን ብሔራዊ የሀገሪቱ ሃይማኖት እንዲሆን በአዋጅ አወጀ። በጉልበት ብዙ ሞከረ ብዙ ሺዎችን አሰየፈ ፣ አስገደ ፣ አሳደደ ፣ ፈርተው ሃይማኖታቸውን የለወጡትም ለወጡ አንለውጥም ብለው በኦርቶዶክስነታቸው የፀኑትም በግፍ ተገደሉ ሊቃውንቶች ፣ አባቶች ፣ ሰባኪዎች ፣ መነኩሴዎች ፣ ዲያቆናትና ካህናት ሁሉ እስከ ምዕመኑ ድረስ ከግድያ እስከ ከባድ ድብደባ የግፍ ፅዋን ተጎነጩ።

የሮማዋ ካቶሊክም በፖርቹጋል የጦር መሳሪያ እርዳታ መልክ ብዙ ሺህ ኦርቶዶክሳዊያንን በአፄ ሱሲኒዮስ እጅ አስጠፋች። ካቶሊክ በኢትዮጵያ ብሔራዊ ሃይማኖት ተብላ ታውጃ እስከ ሁለት አምስት አመታት ድረስ ዘለቀች። እስከዚያም ድረስ ኦርቶዶክሳዊያን ሲገደሉ ፣ ሲሳደዱ ፣ ሲታሰሩ ፣ ሲንገላቱ ብዙ አመታትን አሳለፉ። እስከ ዚያም ጊዜ ብዙ የቤተክርስቲያን ሰዎች ሱሲኒዮስን ለማጥፋት በብዙ አይነት መንገዶች ሲሞክሩ ቆይተው ነበር። ከዛም አንድ የቤተክህነት ሰው አፄ ሱሲኒዮስን ልክ እንደ ዲዳ ምላሱ እንደተቆለፈ አድርጎ (በጠቅላላው ፓራላይዝድ) ይመስል አይነት አድርጎ መንፈሳዊ በሆነ መናፍስታዊ
ጥበብን ተጠቅሞ ሱሲኒዮስን በሽተኛ አደረገው። ብዙዎቹም በዚህ ደስ አላቸው። ከዛም ሱሲኒዮስ በዚህ በከባድ በሽታ ምክንያት ከመንበረ ሥልጣኑ ገለል ተደርጎ የእርሱ የመጀመሪያው ልጅ የሆነው አፄ ፋሲለደስ የንግስና ስልጣኑን ተቆጣጠረው። ከዛም የመጀመሪያ ሥራ ያደረገው አባቱ (ሱሲኒዮስ) ከታመመበት ደዌ ነፃ እንዲሆን ፈልጎ ነበርና። በጎንደር ቤተመንግሥት በኩል አንድ መግለጫ ወጥቶ ነበር የመግለጫውም ጭብጥ ሀሳብ "አፄ ሱሲኒዮስን በደዌ የመታው የቤተክህነት ሰው ራሱን በፈቃደኝነት አጋልጦ እንዲሰጥና አባቱን በደዌ እንደቆለው እንዲፈታው እና ሽልማቱን እንዲቀበል የሚል መግለጫ ወጣ" ከዛም ሱሲኒዮስን እንዲህ ያደረገው የቤተክህነት ሰው ራሱን አጋልጦ አፄ ሱሲኒዮስን ከደዌው ነፃ አደረጋቸው ከዛም አፄ ሱሲኒዮስም አፉን እንዲህ በሚል ቃል ፈታ " #ኦርቶዶክስ_ትንገስ_ካቶሊክ_ትፍለስ" ብሎ ተናገረ ብዙዎቹም ተደነቁ። ይሄም ቃል በልጁ በአፄ ፋሲለደስ ተደገመ። ከዛም በኢትዮጵያ የሚገኙት ከፖርቹጋል የመጡት የካቶሊክ ሚሲዮኖችን አባረረ። ከዛም ልጁ ሃይማኖቱን ወደ ኦርቶዶክስ ተዋህዶነት እንዲለውጥ ተደረገ የብዙ ሺህዎች ነብስም በሰላም አረፈች። የሚገርመው ካቶሊክ በሱሲኒዮስ በኩል ወደ ኢትዮጵያ ስትገባ በመጨረሻም ላይ እንደምትባረር ታውቅ ነበረና። በኦርቶዶክስ ተዋህዶ ላይ ከራሷ ልጆች ሌላ የምዕራባውያን የፍልስፍና ትምህርት አስገብተው ነበረ። ከዛም #ኦርቶዶክስ-ቅባት እና #ፀጋ ብለው በ16ተኛው ክፍለዘመን የኑፋቄ ሃይማኖት አቋቁመው ነበር። እነዚህ የኑፋቄ ትምህርቶች ለብዙ መቶ አመታት ዉስጥ ለውስጥ ሲያነሰራሩ ቆይተው በአፄ ቴዎድሮስ (በ18ኛው ክ/ዘ) ላይ ንጉሰ ነገሥቱ የሀገሪቱን የሃይማኖት ሊቃውንቶች ሰብስበው የሃይማኖታዊ ክርክር የኦርቶዶክስ ተዋህዶ ፣ የቅባትና ፀጋ የሚባሉትም በንጉሱ ቴዎድሮስ ፊት ቀርበው ብዙ ጊዜ የፈጀ ክርክር ሲያደርጉ በተመልካቹ ህዝብና በንጉሱ ዘንድ አሳማኝ ሁና የተገኘችው ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ነበረች።

ከዛም ህዝቡም በእልልታ ንጉሰ ነገሥቱ ዳግማዊ አፄ ቴዎድሮስም ከዙፋናቸው ሆነው የኦርቶዶክስ ተዋህዶ ሊቃውንትን አመሥግነው ብሔራዊ ኃይማኖት ሆና ባለችበት እንድትጸና ተደርጋለች። ከ16ተኛው መቶ ክፍለዘመን በፊት የጥንት እርሷ ተዋህዶ ነበረችና አሁንም በዚሁ እንድትፀና ተደርጋ በንጉሰ ነገሥቱ በዳግማዊ አፄ ቴዎድሮስ ዘንድ ታወጀ። ከዛም በካቶሊክ ሚሽነሪ በኩል በ16ኛው ክፍለዘመን የገቡት ቅባትና ፀጋ የሚባሉ ኑፋቄዎች በሀፍረት ቀርተው ኦርቶዶክስ ተዋህዶነት አሁን እስካለችው ድረስ ልትለመልም ችላለች። በዚህ ታሪክ ሁለት አንኳር ነጥቦችን መመልከት እንችላለች፦ አንደኛው ካቶሊክ ለኦርቶዶክስ ተዋህዶ ያላችን ከልክ በላይ ጥላቻ የተመለከትን ሲሆን ሌላው ደግሞ እዉነትን እስከያዘች ድረስ የማትረታው ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ከተራ ምዕመን እስከ ንጉሳዊ አገዛዝ ድረስ የተካደችበትን
ከባዱን ፈተና በድል መወጣቷን ልንገነዘብ ችለናል።

ክፍል ሁለት ይቀጥላል................

Ørthodox Apøløgetic
932 viewsedited  14:42
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-07-12 09:14:09
1.2K views06:14
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-07-12 09:13:30 ★ፍትሕ ያጣው የድሆች ዕንባ ★

★ አጭበርባሪው ዮናታን አክሊሉ በመንግሥት ድጋፍ የሕዝብ ቤት በግፍ አስፈርሶ አዳራሽ ለመገንበት እየተዘጋጀ ነው።★

★ ሐሰተኛው ነቢይ ዮናታን አክሊሉ ሕዝብን በማጭበርበር ከታች በፎቶ እንደምንመለከተው ለራሱ ገርጂ ቤት ሰርቶ በሰላም እየኖረ ነው ምስኪን ድሆች ግን ቤታቸው ፈርሶ ሜዳ ላይ እንዲበተኑ አድርጓል የአዲስ አበባ ሕዝብ ይህንን ዘግናኝ ግፍ እያየ ዝም ብሎ መቀመጥ የለበትም።ለሕዝቡ የሚደርስ መንግሥትና ፍትሕ ስለሌለ ሕዝቡ ራሱ እርምጃ ሊወስድ ይገባል።ከንፈር እየመጠጡ መቀመጥ መፍትሔ አይደለም።

ጨካኝና አረመኔን ሰው በዛው ልክ ካልቀጣኽው ሌላ የከፋ ግፍ ከመፈጸም ስለማይመለስ ሕዝቡ ራሱ እርምጃ ይውሰድ።ለሰነፍ ሰው እንደ ስንፍናው መልስለት አሊያ ጠቢብ የሆነ ይመስለዋል።ተብሎ ተጽፏል።

"ቤቱን፡በግፍ፡ሰገነቱንም፡በዐመፅ፡ለሚሠራ፥ባልንጀራውንም፡እንዲያው፡በከንቱ፡ለሚያሠራ፥ዋጋውንም፡
ለማይሰጠው፤
14፤ለራሴ፡ሰፊ፡ቤት፡ትልቅም፡ሰገነት፡እሠራለኹ፡ለሚል፥መስኮትንም፡ለሚያወጣ፥በዝግባም፡ሥራ፡
ለሚያሳጌጥ፥በቀይ፡ቀለምም፡ለሚቀባው፡ወዮለት።"ኤር 22 ፥ 13

★ የአዲስ አበባ ሕዝብ እርምጃ ውሰድ !!

በየፌስቡኩ ሼር አድርጋችሁ ለሕዝብ አድርሱት
1.2K viewsedited  06:13
ክፈት / አስተያየት ይስጡ