Get Mystery Box with random crypto!

Tariku Abera

የቴሌግራም ቻናል አርማ tarikuabera — Tariku Abera T
የቴሌግራም ቻናል አርማ tarikuabera — Tariku Abera
የሰርጥ አድራሻ: @tarikuabera
ምድቦች: ሃይማኖት
ቋንቋ: አማርኛ
ተመዝጋቢዎች: 6.00K
የሰርጥ መግለጫ

ኦርቶዶክሳዊ የወንጌል አገልግሎት

Ratings & Reviews

2.50

2 reviews

Reviews can be left only by registered users. All reviews are moderated by admins.

5 stars

0

4 stars

0

3 stars

1

2 stars

1

1 stars

0


የቅርብ ጊዜ መልዕክቶች

2022-08-31 18:47:32
1.1K views15:47
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-08-31 18:47:08
1.1K views15:47
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-08-31 18:45:28 † ቅዱስ ፓትርያርኩ ለቤተክርስቲያንና ለሕዝብ ታምነዋል።†

ለ4ኛ ጊዜ የተላከው ሽምግልና አልሠራም ቅዱስነታቸው ጳጉሜን 1 ቀን 2014 ዓ/ም ወደ ኢትዮጵያ ይመለሳሉ "እሺ መቅረት እንኳን ባይችሉ ጳጳሳትን ሹመውልን ይሄዱ"? ብለው ሊያታልሏቸው ሞከሩ እሳቸው ግን አይ በእኔ ዘመን እና በዚህ ዕድሜዬ ቤተክርስቲያንን ለሁለት አልከፍልም ። እናንተም ቤተክርስቲያንን አክብሩ ለሚያልፍ ችግር የማያልፍ መከራ ቤተክርስቲያን ላይ አንትከል አሁን ወደ መጣችሁበት ተመለሱ አሏቸው።

ቅዱስ ፓትርያርኩ ቤተክርስቲያንን ለሁለት እንዲከፍሉ በተደጋጋሚ ቢጠየቁም ሞቴን ያስቀድመው ቤተክርስቲያን ድጋሚ አትከፈልም ብለው በአቋማቸው ጸንተው ቤተክርስቲያንን አስከብረዋል።ሁላችን ልናከብራቸው ይገባል።ኢትዮጵያ ሲገቡም በክብር እንቀበላቸው።

ቅዱስ ፓትርያርኩ በዚህ የአቋም ጽናታቸው ከውስጥ የሚገፏቸውን የብልጽግና ተላላኪ ቅጥረኛ ባንዳዎች አንገት አስደፍተዋል፤ ከውጪም ሆነው እያባበሉ የሚጎትቷቸውን የቤተክርስቲያንና የሃገር ገነጣጣዮችን አንገት አስደፍተው ተስፋ አስቆርጠዋል።ለቤተክርስቲያን ክብር በጽናት መታገል ማለት ይሄ ነው።

ለሌሎችም ሼር አድርጉት

መ/ር ታሪኩ አበራ
1.1K views15:45
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-08-31 08:44:24
1.3K views05:44
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-08-31 08:43:55 ★ መንግሥት እጅህን ከቤተክርስቲያን ላይ አንሳ !! ★

† ለፓትርያርክ አቡነ ማትያስ የክብር አቀባበል እንዳይደረግ መንግሥት ክልከላ እያደረገ ነው።†

★ ትናንት ማክሰኞ ዕለት የቅዱስ ፓትርያርኩ ቢሮ በመንግሥት ደህንነቶች ተከቦ ያመሸ ሲሆን የቅዱስ ፓትርያርኩን ልዩ ፀሐፊና ፕሮቶኮል እንዲሁም አንዳንድ ሠራተኞችን ለማሰር ቀኑን ሙሉ ሲሯሯጡ ውለዋል። ወደ መንበረ ፓትርያርክ ዘለው በድፍረት በመግባት የተወሰኑ ሰዎችን አፍነው የወሰዱ ሲሆን እስከ ሌሊቱ ስድስት ሰዓት ድረስ ግቢው ውስጥ ሲሰልሉ አምሽተዋል።★

★ በዳንኤል ክብረት ፣በ"ቄስ"በላይ መኮንንና በአባ ሕጻን አስተባባሪነት በቅዱስ ፓትርያርኩ ላይ እየተዶለተ ያለው ከፍተኛ አድማና ሴራ ፓትርያርኩን ከሥልጣናቸው በማፈናቀል ለብልጽግና ፓርቲ የሚላላክ ቅጥረኛ ፓትርያርክ ቤተክርስቲያን ላይ አምጥቶ ለመጫን የሚፈጸም እኩይ ሴራ በመሆኑ ሕዝበ ክርስቲያን አጥብቀን ልንቃወም ይገባል።★

ቅዱስ ፓትርያርኩ ለሕክምና ወደ ውጭ እንደ ሚወጡ መግለጫ በተሰጠበት ወቅት ዳንኤል ክብረት በግልጽ ፓትርያርኩ ከኢትዮጵያ ከወጡ አይመለሱም ብሎ የሐሰት ሟርት ተናግሮ በኤርፓርት ከፍተኛ መጉላላት እንዲደርስባቸውና የቤተክርስቲያንን ክብር በሚያዋርድ መልኩ በድብቅ ካሜራ የቀረጹትን ወሬ ለፕሮፓጋንዳ ፓትርያርኩ ጽላትና መስቀል ይዘው ሊወጡ ሲሉ ተያዙ ብለው ሕዝብን በፓትርያርኩ ላይ ለማነሳሳት የሐሰት ዜና ቢያሰራጩም ያሰቡት ሴራ ከንቱ ሆኖ ሳይሳካላቸው በመቀርቱ በዚህ የተበሳጩት የመንግሥት ቅጥረኛ ተላላኪዎችና የቤተክርስቲያን የውስጥ ባንዳዎች አሁን ደግሞ ቅዱስ ፓትርያርኩ ሕክምናቸውን ጨርሰው በሰላም መምጣታቸውን በማስመልከት ሕዝብ የደስታ አቀባበል እንዳያደርግ ከፍተኛ የማጨናገፍ ተግባር እየፈጸሙ ነው።ይህ ሁሉ የቅድስት ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያንን ብሔራዊ ክብርና ሉዓላዊነት የሚዳፉር አጸያፊ ተግባር በመሆኑ ሕዝበ ክርስቲያን ለማንም ሳይሆን ለሃይማኖቱ ክብር ሲል ይህንን መንግሥታዊ ነውረኛ ተግባር ጠንክሮ ሊቃወምና ሊታገል ይገባል።

መላው የኦርቶዶክስ ተዋሕዶ እምነት ተከታይ የሆናችሁ ምዕመናን፣ካህናት፣የሰንበት ት/ቤት ወጣቶች፣የቤተክህነት ሥራተኞችና ማኅበራት ቅዱስ ፓትርያርኩ ወደ ኢትዮጵያ የሚገቡት ጷግሜ 1 ቀን በመሆኑ እንኳን ደህና መጡ ለማለት ሁላችሁም ወጥታችሁ እንድትቀበሉና ለአንድ ቤተክርስቲያንን ለሚወክል መንፈሳዊ አባት የሚደረግ የክብር አቀባበል እንድታደርጉ ከወዲሁ እናሳስባለን።መንግሥትና የውስጥ ባንዳዎች ይህ እንዳይደርግ ስለሆነ እየተሯሯጡ ያሉት እናንተ የቤተክርስቲያን አገልጋዮችና ምዕመናን ከወዲሁ ነቅታችሁ የአድመኞችን ሴራ በእግዚአብሔር ኃይል ታከሽፋ ዘንድ መልዕክታችንን እናስተላልፋለን።

መ/ር ታሪኩ አበራ

ለሌሎችም ሼር በማድረግ ሕዝባችንን እናንቃ በየጉሩፑም ለጥፋት።
1.3K views05:43
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-08-30 12:44:17
824 views09:44
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-08-30 12:44:09
816 views09:44
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-08-30 12:43:54 † ጥያቄ ለኦርቶዶክስ አገልጋዮች †

★ በየሆቴሉና በየአዳራሹ ጉባዔ ማድረግ የተወገዘ ነው ስትሉ የነበረ ለእናንተ ችርቻሮ ጊዜ የተቀደሰ ያደረገው ማነው ? ★

" የተለሰኑ፡መቃብሮችን፡ስለምትመስሉ፥ወዮላችኹ።
እንዲሁ፡እናንተ፡ደግሞ፡በውጭ፡ለሰው፡እንደ፡ጻድቃን፡ትታያላችኹ፥በውስጣችኹ፡ግን፡ግብዝነትና፡
ዐመፀኝነት፡ሞልቶባችዃል።" ማቴ 23 ፥ 27

ከጊዜ ወደ ጊዜ በኦርቶዶክስ አገልጋዮች ዘንድ የምናየው ነገር እጅግ የሚያሳፍርና በሕዝብ ዘንድ የሚያስተዛዝብ ነው።
ሁላችን እንደምናስታውሰው ከጥቂት ዓመታት በፊት በርካታ የኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ሰባክያንና ዘማርያን ከእናት ቤተክርስቲያናቸው ተወግዘው እንዲወጡ ተደርገዋል።ከቤተክርስቲያን እንዲወጡም ከፍተኛ ጫናና ግፊት ተደርጓል ለዚህም እንደ ዋነኛ ምክንያት የነበረው በየአዳራሹና በየሆቴሉ ጉባዔ እያዘጋጁ ወጣቱን ከቤተክርስቲያን መዓዛ እየለዩት ነው የሚል ነበር።

የአዳራሽ ጉባዔ ሲቃወሙ የነበሩት የዛሬ ነጋዴ ሰባክያንና ዘማርያን በወቅቱ ምክንያታቸውን ሲያቀርቡ የዕጣኑ መዓዛ ወደ ማይሸተትበት ፣የካህናቱ ዜማ ወደ ማይሰማበት፣ኪዳን ወደ ማይደረስበት ፣ቅዳሴ ወደ ማይቀደስበት አዳራሽና ሆቴል ሕዝቡን እየወሰዱ ከቤተክርስቲያን ዓውደ ምሕረት ሊለዩት ነው ብለው ከፍተኛ ሁሁታና አድማ በማድረግ አገልጋዮቹ ከቤተክርስቲያን እንዲወጡ አስደርገዋል።

ለመሆኑ የዛኔ እንደ ርኩስ ይቆጠር የነበረው የአዳራሽ ጉባዔ ዛሬ ቅዱስ የሆነው ለእናንተ የካሴትና የመጽሐፍ ችርቻሮ ሲሆን ነው እንዴ ? በየሆቴሉ አትሂዱ ስትሉ የነበራችሁ ግብዞች ዛሬ ለእናንተ ንግድ ሲሆን ሆቴሉ ቤተመቅደስ ሆነ እንዴ? የአዳራሽ ጉባዔ የተወገዘ ነው ስትሉ የነበረ እናንተ የተለሰነ መቃብር የመሰላችሁ ግብዞች ዛሬ ለእናንተ ቢዝነስ መስሪያ ሲሆን አዳራሹ ገዳም ሆነ እንዴ ?

መጽሐፍ ቅዱስ እንዲህ ይላል ፦ "አንተ፡የምትፈርድ፡ሰው፡ዅሉ፡ሆይ፥የምታመካኘው፡የለኽም፤በሌላው፡በምትፈርድበት፡ነገር፡ ራስኽን፡ትኰንናለኽናእንደዚህም፡በሚያደርጉት፡ላይ፡የእግዚአብሔር፡ፍርድ፡እውነተኛ፡እንደ፡ኾነ፡እናውቃለን።" ሮሜ 2፥1

እውነት ለመናገር እናንተ ግብዝ አገልጋዮች በወቅቱ እንደዛ ያዙን ልቀቁን እያላችሁ ወንድሞቻችሁን ስታሳድዱ የነበረው የቤተክርስቲያን ክብርና የወንጌል ፍቅር ልባችሁን አቃጥሎት ሳይሆን ክፋ ሰይጣናዊ ቅናት አዕምሯችሁን አደንዝዞት በምቀኝነት ነው።እንደዛ ባይሆንም ኖሮ ዛሬ በየሆቴሉና በየአዳራሹ ስትልከሰከሱ አትታዩም ነበር።በሰይጣናዊ ቅናት ተበለጥን የሚል ክፋ ምቀኝነት እንቅልፍ ነስቷችሁ ስለነበር የገዛ ወንድምና እህቶቻችሁን ካደጉበት ከእናት ቤተክርስቲያናቸው አሳዳችሁ ለአውሬ ሰጣችኋቸው፣አንድም ቀን ቁጭ ብለን እንወያይ ብላችሁ መጽሐፍ ቅዱስ ገልጣችሁ ያላነጋገራችኋቸውን ወንድም እህቶቻችሁን ገፍታችሁ አስወግዛችሁ ከበሮ ስትደልቁ ነበር እግዚአብሔር ግን ይፈርዳል።በእግዚአብሔር ልጆች ላይ ስለፈጸማችሁት ግፍ እግዚአብሔር በእያንዳንዳችሁ በምትወልዷቸው ልጆች ላይ ፍርዱን ያሳያችኋል በልጆቻችሁ ታገኙታላችሁ ጠብቁ።

ከቤተክርስቲያን አሳዳችሁ ስላስወጣችኋቸው አገልጋዮችና ምዕመናን መጽሐፍ ቅዱስ እንደሚናገረው እግዚአብሔር ደሙን ከእጅህ እፈልጋለሁ ብሎ በግልጽ ይጠይቃችኋል።ፍርድን ከእግዚአብሔር ጠብቁ።

እናንተ የተለሰነ መቃብር የምትመስሉ ግብዝ አገልጋዮች የቤተክርስቲያን ልጆችን አሳዳችሁና በረሃብ ቀጥታችሁ ለሌሎች አሳልፋችሁ ከሰጣችሁ በኋላ አንዳንዶቻችሁ የቤተመንግሥት ፍርፋሪ ለመለቃቀም ከዓቢይ አህመድ መንግሥት ጋር ተጣብቃችሁ ቤተክርስቲያን ላይ የመከራ ዶፍ ሲወርድ በየሥርቻው ድምጻችሁን አጥፍታችሁ ትቀመጣላችሁ ለሲዲና ለመጽሐፍ ችርቻሮ ሲሆን ግን ተለቃቅማችሁ ትመጣላችሁ።አንዳንዶቻችሁ ወንጌል እየሰበኩና እየዘመሩ ወጣቱን ይዘው የነበሩ አገልጋዮችን በሰይጣናዊ ቅናት አሳዳችሁ አስወጥታችሁ ዛሬ በዘር ፓለቲካ ውስጥ ገብታችሁ ስትጨመላለቁ እያየን ነው።ወጣቱ ከቤተክርስቲያን እየፈለሰ ሲሄድ ጉዳያቹ ስላልሆነ እናንተ የዩቱዩብ ምጽዋታችሁን ለመለቃቀም ፓለቲካ ስታንቦጫርቁ ትውላላችሁ።የቤተክርስቲያን አምላክ ይፈርድባችሁ።በጣም ርካሾች ናችሁ።

ዛሬ እኮ ብዙ ወጣት ከቤተክርስቲያን እየኮበለለ እየወጣ ያለው እናንተ መድረኩን እንጂ የወጣቱን ልብ መያዝ ስላልቻላችሁ ነው።ሲጀመር በሥጋዊ ቅናት የእግዚአብሔርን መንፈስ እያሳዘናችሁ የምትሰብኩት ስብከት ለእናንተ ንግድ እንጂ ለወጣቱ ሕይወት አይሆንም ለዚህ ነው የቤተክርስቲያን አማኞች ቁጥር ቁልቁል እየወረደ ያለው።

ሌላው የገረመኝ ጉዳይ ኢሊሌ ሆቴል ከፓስተሮችና ሁስታዞች ጋር ስለ ሃገራዊ ጉዳይ እንወያያለን ብላችሁ የለጠፋችሁት ማስታወቂያ ነው።እውነት እናንተ በመወያየት የምታምኑ ከሆኑ ከጥቂት ዓመታት በፊት ስንቱን የወንጌል አገልጋይና ዘማሪ ነው ከቤተክርስቲያን ካልወጣ ካልተወገዘ እያላችሁ አድማ እያሳደማችሁ ስታሳድዱ የነበረው ? አታስመስሉ እግዚአብሔር ያያል፣ልብና ኩላሊትንም ይመረምራል።በመወያየት የምታምኑ ከሆነ ለመሆኑ የትኛውን አገልጋይ ነው ጠርታችሁ ያወያያችሁት ፣የት ቦታ፣በምንጊዜ፣በምን ርዕሰ ጉዳይ ? በጅምላ አይደል እንዴ የቅድስት ቤተክርስቲያንን ልጆች በአድማ አሳዳችሁ ለአውሬ የሰጣችኋቸው እግዚአብሔር ግን ይፈርዳል የማንም ዕንባ ፈሶ አይቀርም።

አሁንም ከፓስተርና ከሁስታዝ ጋር የውይይት ፕሮግራም ብላችሁ ሕዝቡን በየሆቴሉ እንደ ከብት የምትነዱት ለሃገር ተጨንቃችሁ፣ለቤተክርስቲያን አስባችሁ ሳይሆን ከዓቢይ አህመድ መንግሥት ጋር ተመሳስላችሁ ለመኖር እንደ ውሻ እየተላላሳችሁ ለመኖር የነደፋችሁት ርካሽ ሥጋዊ ዕቅድ ነው።

ስለዚህ ኦርቶዶክሳውያን ክርስቲያኖች በጣም አስተውሉ ዛሬ ቤተክርስቲያንን ከበው ያሉት አስመሳይ ነጋዴዎች ፣በሥጋዊ ቅናትና ፣ሥጋዊ አድማ ልባቸው የደነደነ ክፋዎች እንጂ እንደ ቅዱሳን ሐዋርያት ለጨበጡት ወንጌል ታምነው ክርስቶስ ኢየሱስን በጽድቅ የሚያገለግሉ የጽድቅ አጉልጋዮች አይደሉም።የሰው ደም በየቦታው ሲፈስ ግድ የማይላቸው፣ኦርቶዶክሳውያን ብሔራቸውና ሃይማኖታቸው እየተለየ እንደ ከብት ሲታረዱ ለምን ብለው አጥብቀው የማይታገሉ አስመሳዮች ፣ለአንድ ሐሰተኛ ነቢይ የኦርቶዶክሳውያን መኖሪያ ቤት ፈርሶ ሜዳ ላይ ሲበተኑ ሄደው የማያጽናኑ ለምን ብለው የማይሟገቱ ሐሞተ ቢስ ግብዞች ናቸው።ሕዝቡን ለገንዘቡ ሲሆን እንጂ በመከራው ሰዓት ዞር ብለው አያዩትም።

በርግጥ እውነተኛ የቤተክርስቲያን አገልጋዮች አሉ ትናንትም አድማና ተንኮል ውስጥ ያልነበሩ ዛሬም ክርስቶስ ኢየሱስን በሰው ልብ ውስጥ እስኪሳል ድረስ በጭንቅ የሚሰብኩ ብርቱ አገልጋዮች አሉ።አስመሳይ ነጋዴዎቹ ግን ሸቀጣቸውን ለማረገፊያ በየሆቴሉና በየአዳራሹ ኑ ሲሏችሁ ለምን ? ብላችሁ መጠየቅን ልመዱ ።

መ/ር ታሪኩ አበራ

ለሌሎችም ሼር አድርጉት
743 views09:43
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-08-29 10:10:09
1.1K views07:10
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-08-29 10:10:00 Eventually he was dragged through the streets of Diospolis (now Lydda) in Palestine and beheaded. It's said that Diocletian's wife was so impressed by George's resilience that she became a Christian and that she too was executed for her faith.

በመጨረሻም ቅዱስ ጊዮርጊስን በዛሬዋ ልዳ ከተማ ጎዳና ላይ እየጎተቱ ወስደው እስዛው በፍልስጠኤም ምድር አንገቱን ሰየፉት።የንጉሡ ዲዮቅልጢያኖስ ሚስት ግን በቅዱስ ጊዮርጊስ የእምነት ጽናት ውስጥዋ እጅግ ተማርኮ ነበርና እርሷዋም በመጨረሻ ክርስቲያን ሆነች። ስለ ክርስትናዋም ብዙ መልካም ተግባራትን ትፈጽም ነበር።

ወገኖቼ በጣም እናስተውል ሰው ወንጌል ሲገባው ቅዱሳንን ያከብራል፣ስለ ክርስቶስ ፍቅር ዋጋ ከፍለው በሰማዕትነት ያለፉ የእምነት ጀግኖችን እያሰበ ሕይወታቸውን አብነት አድርጎ ይጓዛል፣ለዚህ ነው ቅዱስ ጳውሎስ «የእግዚአብሔርን ቃል የተናገሯችሁን ዋኖቻችሁን አስቡ የእምነታቸውንም ፍሬ እየተመለከታችሁ በእምነታቸው ምሰሏቸው ያለው።»ዕብ 13፥7
የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን የሰማዕታትን የተጋድሎ ሕይወትና ወንጌልን በሕይወታቸው እንዴት እንደተረጎሙ ትውልዱ በየጊዜው እያሰበ እንዲኖር ቀናት በቅዱሳን ስም ሰይማ ተጋድሎና ታሪካቸውን ስታስተምር መኖሯ ከትክክል በላይ ትክክል ነው። ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ እግዚአብሔር ሁሌም በክብር ይጠብቅሽ። ዛሬ አንዳንድ ሰዎች ወንጌል ገብቶናል፣ እውነት በርቶልናል እያሉ ቅዱሳንን ሲያቃልሉና ሰማዕታትን ሲያብጠለጥሉ ይውላሉ፤ ነገርግን ስለ ክርስትና አንዲትም መከራ በሕይወታቸው አልተቀበሉም። በግል በሥጋ ድካማቸው የሚመጣባቸውን መከራ ስለ እምነታቸው እንደተቀበሉት አድርገው ይጠመዝዙታል ይሄ በጣም ስህተት ነው።እውነት ወንጌል የበራላችሁ ከሆነ እስቲ እስላም መስኪድ ሄዳችሁ ስበኩ፣እስቲ ጠንቋይ ቤት ያሉትን የማምለኪያ መሰዊያዎች ሄዳችሁ አፍርሱ፣ፌስቡክ ላይ ተጥደው እየዋሉ ቅዱሳንና ሰማዕታትን የሚነቅፉ፣ የቤተክርስቲያንን ክብር ለማዋረድ የሚወራጩ ሰዎች መንፈሰ እግዚአብሔር የተለያቸው የአጋንንት መንፈስ በልባቸው ሰልጥኖ ምላሳቸውን የተከራያቸው የጥፋት ልጆች ናቸው እግዚአብሔር ልባቸውን ይፈውስ።

ወገኖቼ የክርስቶስ ፍቅር ሲገባን እንደነ ቅዱስ ጊዮርጊስ እሳትና ስለቱን ሳንፈራ ስለ ወንጌል እንመሰክራለን፣ ኢየሱስ ክርስቶስ የአማልክት አምላክ፣የጌቶች ጌታ ፣የነገሥታት ንጉሥ መሆኑን ሳንፈራና ሳናፍር እንመሰክራለን።የሰማዕታት ደም የእምነት ዘር ነው ጥቂት ፈሶ ብዙ ምርኮን ወደ እግዚአብሔር መንግሥት ያስገባል።

የሰማዕቱ በረከት ከሁላችን ጋር ይሁን።

" ...ጻድቅን በጻድቅ ስም የሚቀበል የፃድቅን ዋጋ ይወስዳል ማንም ከነዚህ ታናናሾቹ ለአንዱ ቀዝቃዛ ውኃ ብቻ በደቀ መዛሙርቱ ስም የሚያጠጣ እውነት እላችኃለሁ ዋጋው አይጠፋበትም ..." (ማቴ.10፥41)

እባካችሁ ለሌሎችም ሼር አድርጉት በየጉሩፑም ለጥፋት

ለበረከት ሁኑ።

መ/ር ታሪኩ አበራ
1.1K views07:10
ክፈት / አስተያየት ይስጡ