Get Mystery Box with random crypto!

S֮t֮r֮o֮n֮g֮ I֮m֮a֮n֮

የቴሌግራም ቻናል አርማ strong_iman — S֮t֮r֮o֮n֮g֮ I֮m֮a֮n֮ S
የቴሌግራም ቻናል አርማ strong_iman — S֮t֮r֮o֮n֮g֮ I֮m֮a֮n֮
የሰርጥ አድራሻ: @strong_iman
ምድቦች: ሃይማኖት
ቋንቋ: አማርኛ
ተመዝጋቢዎች: 13.74K
የሰርጥ መግለጫ

❥ሁሌም ቢሆን ለዲንህ ትልቁን ቦታህን ስጥ!!
«ያ አላህ! ባልሰራበት እንኳ ወደ በጎ ነገር
ያመላከተ ሰው የሚያገኘውን አጅር አታሳጣኝ፡፡»
Channelu ሚሰጣቸው አገልግሎቶች👇
🌟የ ታላቁ አሊም የመሀመድ ሀሰናት ሀዲሶች
✨ውቡ ድንቅ አና አስተማሪ ታሪኮች
ኢስላማዊ አጀንዳዎች ,islamic qoutes &others
4 any comment at 👉 @strong_iman_bot

Ratings & Reviews

1.00

2 reviews

Reviews can be left only by registered users. All reviews are moderated by admins.

5 stars

0

4 stars

0

3 stars

0

2 stars

0

1 stars

2


የቅርብ ጊዜ መልዕክቶች 2

2022-09-01 20:41:15 "ሀዋን ማን ገደላት"
( አብዲ ኢኽላስ)

ክፍል አስራአንድ(11)

... በሰሚር መንቃት ሁሉም እየተሯሯጡ ወደ ዶክተሩ እና ወደ እትዬ መርየም ሄዱ።እትዬ መርየምን ይዞ እየሄደ ያለው ዶክተር ያሉትን ሲሰማ እየሮጠ ወደ ኋላ ተመለሰ። ሁሉም ውጪ እንዲጠብቁት አድርጎ ብቻውን ወደ ሰሚር ክፍል ዘንድ ገባ ሁሉም በፍርሀት እና በጭንቀት ተሞልተው የደስታ ስሜት ወሯቸዋል። ደስታ የፈጠረባቸው የሰሚር መንቃት እና የልብ ምቱ መስተካከል እንዲሁም በህይወት መኖሩ ሲሆን ጭንቀቱ ደግሞ ሲነቃ ነው ምናውቀው በጭንቅላቱ ላይ የደረሰ ጉዳት እንዳለ ይሆን ያለው ቃል የዶክተሩ ንግግር ረብሿቸዋል ጭንቀት ፈጥሮባቸዋል ። ምን ይሆን?ጭንቅላቱ ላይ ምን ደርሶበት ይሆን? ምን ክፉ አደጋ አጋጥሞት ይሆን? የሁሉም ጥያቄ ነው

ጥቂት ሰከንዶችን ኮሪደሩ ላይ ሆነው ወደ ቀኝ እና ወደ ግራ እየተንቆራጠጡ የዶክተሩን መውጣት በእጅጉኑ ተጠባበቁ። ከጥቂት ደቂቃዎች በኋላ ዶክተሩ ሰሚር ያለበትን ክፋል በሩን ከፍቶ ድንገት ብቅ አለ። ይሄኔ ሁሉም እየተሯሯጡ ወደ ዶክተሩ ሄደው ምን እንደተፈጠረ ያለውን ሁኔታ እንዲያስረዳቸው ጠየቁት። ግን የዶክተሩ መልስ እጅጉን ያስገርማል። ከሁሉም ነጥሎ "አንቺ ነይ! አንቺ ነይ ግቢ!" አላት ሙናን። እትዬ መርየም ኻሊድ እና ሱመያ እርስ በእርስ ተያዩ ከሁሉም አንፃር እሷኮ በጣም ሩቅ ነች። ለማስታመምም ሆነ ለከባድ ነገር ሀላፊነት ምትወስድ አይደለችም። እንዴት ሙናን ሊጠራት ቻለ? በፍርሀት ተውጠዋል። ልምድም ስለሌላቸው ተናግረውም ችግር እንዳይፈጥሩ ግራ በተጋባ ስሜት አፋቸውን ይዘው በዝምታ ተውጠዋል። ዶክተሩ ሙናን ወደራሱ ከጠራት በኋላ በርጋታ በሹክሹክታና በለሆሳስ አንዳች ነገር ካላት በኋላ ወደ ሰሚር ክፍል ይዟት ገባ። እትዬ መርየም ይበልጥ ግራ ተጋቡ ኻሊድ እና እትዬ መርየም በፍርሀት ተያዩ ማታ ይሀን ስልክ ቁጥር የሀዋ ስልክ ላይ ተመልክተዋል። ሙናን በገዳይነት ወይም በእኩይ ተግባር ፈፃሚነት እየተጠራጠሯት ባሉበት በዚህ ሰአት የቅርብ ተጠሪ አስታማሚ ሆና እንዴትስ ልትገባ ቻለች?

ግራ ያጋባል።ወይንስ በሀዋ ጉዳይ ያለውን ሰሚር ያውቃል እንዴ? ከሙና ጋር ይተዋወቃል እንዴ? ግራ አጋባቸው። ብዙ ሀሳብ ውስጥ ገቡ። ዶክተሩ ሙናን አስገብቷት እሱ ተመልሶ ወጥቶ ወደ መንገዱ ቀጠለ። እትዬ መርየም አስከትለው ከመንገዳቸው እትዬ መርየም ግራ በተጋባ ስሜት ለምን ሙናን ወደ ውስጥ እንዳስገባት አበክረው ጠየቁት። ዶክተሩም እሷን ያስገባት ሰሚር ገና ከመንቃቱ ባለቤቴን አምጡልኝ ፤የልጆቼን እናት፤ እያለ ስለተጣራ እንደሆነ ነገራቸው። ታድያ እትዬ መርየም ባለቤቴን አለ እንጂ መቼ የባለቤቴን እህት አለ? ብለው ጠየቁት። ዶክተሩም ምሽት ላይ ሙና የሰሚር ባለቤት ነኝ እኔ የልጆቹ እናት ነኝ ብላው እንደነበር ነገራቸው። ይሄኔ እትዬ መርየም ደንግጠው በሩጫ ወደ ሰሚር ክፍል አቀኑ። ዘልቀው እንደገቡም ሙና የሰሚርን እጆች ይዛ በፈገግታ እየተጨዋወቱ አገኙ። ይሄኔ በጣም ደነገጡ በጣምም ግራ ተጋቡ። ምን እየሆነ እንዳለ ማመን አልቻሉም። ሰሚር ራሱን ስቶ የወደቀው ሀዋን ስላጣ እንጂ ሙናን ፈልጎ አይደለም። ራሱን ከሳተበት ሲነቃ ያገኘው ሀዋን ሳይሆን ሙናን ነው። ታድያ ሊጨነቅ ፣ ሊናደድ፣ ሊያለቅስና ግራ ሊጋባ ባስ ሲልም ሊታመም እንጂ እንዴት በፈገግታ ከሙና ጋር ሊያወሩ ከሙና ጋር ሊጫወት ቻለ ግራ ገብቷቸዋል። ምንም ቃል መተንፈስ አልፈለጉም። የትኛውም የሚናገሩት ቃል ሰሚርን መጥፎ ስሜትና ህመም ላይ ሊጥል እንደሚችል ስላሰቡ ብዙም ማውራት አልፈለጉም።ብቻ ኻሊድ እና ሱመያ ወደ ውስጥ እንዲገቡ አደረጉ። ከአባታቸው ጋር አገናኟቸው ። ኻሊድ ና ሱመያ እየተንፈቀፈቁ በጣም እያለቀሱ አባታቸውን እቅፍ አደረጉ በሀይል ሳሙት አጠገቡም ሆነው ብዙ ተጫወቱ። ኻሊድ ግን ከለቅሶው እና ከጭንቀቱ እንዱሁም አባቱን ከማግኘቱ ደስታ ጎን ለጎን ከሙና ጋር እየሆነ ባለው ነገር ግራ ተጋብቷል።መልስ ስላላገኘ አይኖቹ ይማትራሉ። ልቡ ብዙ ይላል አይምሮው ጥያቄ ያዘንባል። ሙና በፈገግታ ተሞልታ በአሸናፊነት ስሜት ሰሚርን የቅርቡ ሆናዋለች። አጠገቡ ሆና ይሄን እየቀዳች ያሀን እያጠጣች እያለበሰችው ትንከባከበዋለች። ነገሩ ግራ ያጋባል። ዶክተሩ አንዲት ነርስን ልኮ እባኮትን እትዬ መርየም ይምጡልኝ የሚል ትእዛዝ አስተላለፈ እትዬ መርየም በግራ መጋባት ስሜት አይን አይኗን አያዩዋት ተከትለዋት ሄዱ። ዶክተሩም እትዬ መርየም ወደ ክፍሉ እንደገቡ አንድ ከባድ መርዶ አረዳቸው። ይሄንን ማመን አልቻሉም። እትዬ መርየም የዶክተሩን ንግግር ሲሰሙ እጅጉን ግራ ተጋብተው እንደሰሚር ራሳቸውን ስተው አልወደቁም እንጂ ራሳቸውን መቆጣጠር ግን አልቻሉም። በሀይል ተዝለፈለፉ በጣም ግራ ተጋቡ የሚሉትን አጡ ዶክተሩን ደግመው ደጋግመው ጠየቁት። ዶክተሩ ግን የሚናገረውን ከመድገም ዉጪ ሌላ አዲስ ነገር የለውም። ያላቸውን እንደሰሙ የሚያደርጉት ግራ ገብቷቸው ከክፍሉ ተነስተው ወጡ። ወደ ሰማር ሄደው ነገሮችን ሲመለከቱ እየሆነ ያለው ነገር ግልፅ ሆነላቸው ግን በጣም ፈሩ ምን ሊከሰት እንደሚችል ማሰብ አልቻሉም መፍትሄ አልመጣላቸውም እትዬ መርየም ዶክተሩ የነገራቸውን ንግግር ለማንም ለምንም ትንፍሽ ማለት አልፈለጉም።ምክንያቱም ይሄ ለንግግር የሚከብድ በጣም ከባድ ነው ጭራሹኑ ሙና ራሷን በንግስት ልክ ስላ ከሰሚር ጎን ልክ እንደ ዙፋን ተሰይማ ሲመለከቱ ላይ ታቹ ግራገባቸው መፍትሄ ሊመጣላቸው አልቻለም አሁንስ ከማን ጋር ሊወያዩ ይችላሉ ከማንስ ጋር ስለምን ይመካከራሉ በጣም በጣም ጨነቃቸው ዶክተሩ እትዬ መርየምን ወደ ክፍሉ ይዟቸው የገባው የነበረው ከዚህ በኋላ ለሰሚር ሊደረግለት የሚገባውን ከባድ የሆነ ጥንቃቄ ሊያረዳቸው ሊያስረዳቸው ነበር ነገር ግን እሳቸው ለምን ሙናን ወደ ክፍሉ እንዳስገባት ሲጠይቁት እሷ የሰሚር ባለቤት ስለሆነችና ሰሚርም እየጠየቀ ያለው ባለቤቱን ስለሆነ ታማሚ ከህመሙ እንደነቃ የሚፈልገውን ሰው ሲያገኝ ህመሙ ስለሚረጋጋለት አይምሮውም እረፋትና ሰላም ስለሚሰማው እንደሆነ ነግሯቸው ነበር ነገር ግን እትዬ መርየም የሰሚር ሚስት የት እንዳለች እንደማይታወቅና ይህቺ የባለቤቱ እህት እንደሆነች ሲነግሩት እጅግ በጣም የሚያስፈራውን መርዶ ያኔ ነው ያረዳቸው። ዶክተሩም አለ እንደዛ ከሆነ እያላቹኝ ያላችሁት እእእ ከባድ ነገር ተፈጥሯል ማለት ነው ይሄ ማለት ብሎ ቀጠለ ዶክተሩ ለእትዬ መርየም መርዶ አረዳቸው እእእ ከዚህ በኋላ አንድ ከበድ ያለ ነገር መከሰቱ አልቀረም አዝናለው እትዬ መርየም ሰሚር ከዚህ በኋላ በደረሰበት ከባድ ጉዳት እና ጭንቅላቱ አካባቢ በተፈጠረው ነገር ሙናን አዝናለው ልክ እንደ ሀዋ ነው ሚመለከታት ከዚህ በኋላ ሙናን ሲያይ ባለቤቱን ሀዋን ያየ ያህል ነው ሚሰማው ስለዚህ ለሱ ነገሮችን ማስረዳት ከባድ ነው ሙና እንደ ሀዋ ልትሆንለት ይገባል ምክንያቱም ለሱ ሙና ምትባል ሴት የለችም ሚስቱ ሙና እንደሆነች አምኗል በማለት ከባድ መርዶ እጅግ ከባድ መርዶ አረዳቸው ሰሚር ሙናን እንዴት እንደ ሀዋ

ክፍል 12 ይቀጥላል

#ልዩ_ምስጋና ለሂክማ

@Strong_iman
679 views𝐒̧𝐔𝐃€𝐘𝐒, 17:41
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-09-01 20:41:10 #ሀዋን ማን ገደላት ልብ አንጠልጣይ ታሪክ

#ክፍል 11

#ደራሲና_ተራኪ:– አብዲ ኢኽላስ

@Strong_iman
651 views𝐒̧𝐔𝐃€𝐘𝐒, 17:41
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-09-01 18:15:40 https://vm.tiktok.com/ZMN3peUc8/
877 views𝐒̧𝐔𝐃€𝐘𝐒, 15:15
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-09-01 15:46:48
አላህ መጨረሻችን ያሳምረው
መደመጥ ያለበት አስደንጋጭ ክስተት
@strong_iman
1.0K views𝐒̧𝐔𝐃€𝐘𝐒, 12:46
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-09-01 08:26:55 አነስ ረ.ዐ እንዳስተላለፉት ነብዩ ﷺ እንዲህ ብለዋል 'አንዳችሁ እምነት ሊኖረው አይችልም ለራሱ የወደደውን ለወንድሙ እስካልወደደ ድረስ'

[ቡሀሪ ዘግበውታል]
1.1K views𝐒̧𝐔𝐃€𝐘𝐒, 05:26
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-08-31 22:16:30 #ብርቱዎች ሱብሂን ይሰግዳሉ
#ብልሆች ኢልም ይኮመኩማሉ
#ጀግኖች ባጢልን ይፋለማሉ
#ቅኖች በኸይር ያዛሉ
#ምርጦች ሀቢቢን ይወዳሉ
#ምሁሮች ጥቂት አውርተው ብዙ ዝም ይላሉ
#ልዩዎች ጌታቸውን ያልቃሉ
#ወዳጆች በሙሀባ ይመታሉ


አላዋቂዎችስ ምን ያደርጋሉ?

መልሳቹን comment ላይ አሪፉ መልስ እዚ ይለቀቃል
1.4K views𝐒̧𝐔𝐃€𝐘𝐒, 19:16
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-08-31 21:00:51 "ሀዋን ማን ገደላት" ( አብዲ ኢኸላስ) ክፍል አስር(10) እትዬ መርየም እና ኻሊድ የሀዋ ስልክ ላይ የተመለከቱትን ነገር በፍጹም አላመኑም።ከተመለከቱት ረጅም ሰአታት ቢቆጠርም እኩለ ለሊት ቢያልፍም እንኳን እንቅልፍ አልወስድ ብሏቸዋል።ግና የሆነውን ሳያጣሩ በመደዋወል ብቻ አይታመንም እና ምንም ማወቅ አልቻሉም።ለሀዋ የተደወለላት የመጨረሻ ቁጥር የሙና በመሆኑ ግራ ተጋብተዋል። ለሀዋ የተደወለላት…
1.3K views𝐒̧𝐔𝐃€𝐘𝐒, 18:00
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-08-31 20:59:50 "ሀዋን ማን ገደላት"

( አብዲ ኢኸላስ)

ክፍል አስር(10)

እትዬ መርየም እና ኻሊድ የሀዋ ስልክ ላይ የተመለከቱትን ነገር በፍጹም አላመኑም።ከተመለከቱት ረጅም ሰአታት ቢቆጠርም እኩለ ለሊት ቢያልፍም እንኳን እንቅልፍ አልወስድ ብሏቸዋል።ግና የሆነውን ሳያጣሩ በመደዋወል ብቻ አይታመንም እና ምንም ማወቅ አልቻሉም።ለሀዋ የተደወለላት የመጨረሻ ቁጥር የሙና በመሆኑ ግራ ተጋብተዋል። ለሀዋ የተደወለላት ቁጥር ነው እንጂ የመጨረሻ እሷ ግን ከሙና ቀጥሎ ለሰሚር ደውላለት ነበር ግና ምንም የተመዘገበ ደቂቃ የለም ምክንያቱም የዛን ቀን የሰሚር ስልክ ዝግ ነበርና። እትዬ መርየም ይበልጥ ውስጣቸውን እየበላቸው እና እያስጨነቃቸው ያለው ነገር ሙና ልጃቸው ነች።ነገ ፖሊሱ ሲመጣ ለፖሊስ ግርማ ምን ብለው ነው ጥርጣሬያቸውን ሚነግሩት።የሀዋ ስልክ ቤት እንዳለ ከነገሩት ተቀብሎ ምን አልባትም ይሄ የግድያ ወንጀል ስለሆነ እስከ ቴሌ ድረስ ሄዶ የተነጋገሯቸውን ንግግሮች ለማጣራት ቢሞክር ምን አልባት ሙና በዚ ጉዳይ ወንጀለኛ ብትሆን ግራ ገባቸው።

እሳቸው የእንጀራ እናት በመሆናቸው በፍጹም በመሀል የመከፋፈል የመለያየት ስሜት የላቸውም።ነገር ግን ለአንደኛዋ ልጃቸው ብለው ሌላኛዋ ልጃቸውን ማስቀጣት አይፈልጉም ግን ኻሊድ ይህን ተመልክቷል ።ኻሊድን ዝም ማስባል በጣም ከባድ ነው እናቱ የት እንዳለች አያውቅም አባቱ ሆስፒታል ተኝቷል በዚህ ጭንቀት ውስጥ ሆኖ ከፖሊስ ያየኸውንም ሆነ የሰማኸውን ደብቅ ቢባል ነገሮች ከባድ ይሆናሉ ።ብቻ በራሳችን መንገድ እስከምናጣራ ድረስ ለሰሚር አጠገቡ መሆን ያለባት ልክ እንደዛሬው እየሄደች የምታድር አንዲት ሴት ሙና ብቻ ነችና እሷንም ካሰሩብን ችግር ይፈጠራል ብለውት ለጥቂት ቀናት ዝም እንዲል አሳመኑት።በዚህ ተስማምተው የነገን ነገ ያውቃል አላህ ያለውን እንቀበላለን ሲሉ ወደ መኝታቸው ተጓዙ።


ጠዋት ነግቶ ወፎች መንጫጫት ከጀመሩ ሰአታት ተቆጥረዋል።ሙና ከተኛችበት ነቃች እሷ ሳትሆን ሰሚር አስታማሚ ይመስል ከፍተኛ እንቅልፍ ውስጥ ተኝታ ለሊት እንኳን ምን ተፈጠረ ብትባል በማታውቅበት ሁኔታ ጭልጥ ብላ ከገባችበት እንቅልፍ ስትነቃ ሆስፒታል ውስጥ እራሷን ስታገኘው ማታ የነበረውን ሁሉ አስታወሰች ትንሽ ግር ብሏት ነበር። ካለችበት ክፍል ውጪ ብዙ ድምፆች አሉ።

የተለያዩ ዶክተሮች አስታማሚዎች ታማሚዎች እና ነርሶች እንዲሁም ሌሎች ሁሉ የሚጮሁት ጩኸት በደንብ ይሰማል።ሆስፒታሉ ብዙ ሰው የሚጨናነቅበት ነውና ገበያ መስሏል።ይህ ሁሉ ጩኸት ባለበት ለሽ ብላ መተኛቷ ለራሷም ገረማት።ወደ ሰሚር ተጠጋች "እንዴት አደርክ?" አለችው መልስ አይሰጣትም ይህን ታውቃለች ነገር ግን መልስ እንደተሰጠው ሰው "አልሃምዱሊላህ እኔም ደና አድሬያለሁ ካንተ ጋ" አለችው ።

ሀፍረት ቢሷ ሙና ከሱ ጋር እንዳደረ ሰው ለራሷ አሳመነች በጀግንነትም ፈገግ አለች።ግን እኳ ሙና የከፋ ቅናት ቢኖርሳትም ሰውኛ ማንነቷ አይለቃትም።ሰው እንደመሆኗ መጠን የዚህን ያህል ጨካኝ ናት ብሎ ማሰብ እጅጉን ከባድ ነው።ምን አልባት በ ሀዋ ላይ እጆን ሰንዝራ ይሁን እንዴ የሚለው ግራ ያጋባል።ምክንያቱም ብትፈልግስ በምን አቅሟ በምን ሁኔታዋ እንደዛ በተጠና መልኩ ከበድ ያለ ወንጀል ለመፈፀም እንዴት ትችላለች። ሀዋ ከቤት ከራቀች ቡሃላ ሙና ለአንድም ቅፅበት የተለየ ስልክ አላወራችም ወደ ደጅም አልወጣችም ምን አድርጋስ ይሁን !!እንዴትስ አልፈራችም?! በፖሊስ ግርማ መምጣትም እንዴት አልተደናበረችም?!ግራ ያጋባል።

ግን አንድ ነገር አቅዳለች ሙና ቤተሰቡን አሳምና ለሰሚር ቅርብ መሆን ሰሚር ሰሚር ከህመሙ ነቅቶ ሲመለስ የመጀመሪያ የሚመለከተው ፊት የሷን እንዲሆን በእጅጉ ተመኝታለች።እሷን እንዳያት አጠገቡ ሆና ልትንከባከበው ባለ ውለታው ሆና ወደራሷ ልታመጣው ልቡን ልታሻፍት ክፉ እቅድ አቅዳለታለች። ነገር ግን ለዚ እቅዷ እንዲስማሙ ቤተሰቦቿ ማመን አለባቸው አለበለዚያ ሊከሽፍ ይችላል።ከጥቂት ቆይታ ቡሀላ ሱመያ ኻሊድ እና እትዬ መርየም ተከታትለው ገቡ። ከነሱ በፊት አንድ ነርስ እና የሰሚርን ጉዳይ የያዘው ዶክተር ሰሚርን መርፌ ሰተውት ሁኔታውን ተመልክተው ወተዋል።እትዬ መርየም ሙናን ሲመለከቷት የፍርሀት ስሜት ውርር አደረጋቸው። ምን አልባት ያ ክፉ ቅናቷ የዚህን ያህል ክፉ ስራ እንድትሰራ ሸይጣናዊ ግፊት ገፍቷት ይሁን እንዴ ሲሉ ተጨነቁ።ከዛም አልፈው ምን አልባት ሰሚር ላይ ጉዳት አድርሳ መጥፎ ነገር ፈፅማ ይሁን እንዴ በማለት ወደ ሰሚር ጠጋ ብለው ትንፋሹን አስተዋሉ ደህና መሆኑን ሲመለከቱ በእርጋታ ተንፍሰው ከወንበሩ ላይ ተቀመጡ።

ሙና የእትዬ መርየምን ወደ ውጪ መውጣት አብዝታ ትጠብቃለች ምክንያቱም ከሳቸው በፊት ኻሊድን እና ሱመያን በእኩይ አላማዋ ልታሳምናቸው የምትላቸውን አዘጋጅታ ቆርጣ እየጠበቀች ነው።ሙና እኮ መጥፎ ምኞት ተመኘች እንጂ ሰሚር በምንም ተአምር ምድር ብትገለበጥ ድጋሜ ቢፈጠር ታሪክ እንዳልነበር ቢሆን ተአምር ቢወርድ ሀዋን ጠልቶ የሙና ሊሆን አይችልም።እንኳን ሀዋን ጠልቶ ሀዋ በሌለችበት ስለ እሷ እያሰበ ይኖራል ሂወቱን አቶ ይሞትላታል እንጂ ሌላ ገላ ማቀፍ ሌላ ሴት ማፍቀር ሌላ ትዳር ማሰብ የማይሆን ነገር ነው። ሰሚር "ሀዋ ለኔ የተሰራችው ልክ በልኬ እንደሚያምርብኝ ሱፍ ውበቴ ናት ይላል"። "የልጆቼ እናት እኔ ከሷ ውጪ ምንም አልፈልግም አንዳች አይጨመርልኝ ምንምም አይቀነስብኝ ሌላ ደስታ ሌላ ምኞት የለኝም" ይላል።ሰሚር ሀዋን የሚወዳት ከልቡ አብዝቶ ከልቡ ነው ለሷ ሲል የትኛውን አይነት የህይወት መሰዋእትነት ለመክፈል ሁሌም ዝግጁ ነው። ዝምብ እንኳን ላይዋ ላይ እንድታርፍ አይፈልግም የሷን ደስታ የሷን ሳቅ የሷን ፍቅር አብዝቶ ይናፍቃል።ሰሚር ከሀዋ ውጪ ሴት አያውቅም ከሷ ውጪ ማንንም ምንንም እንደ ምንም አይቆጥርም።ሌላ ሴት ፍቅርን ምትችል ሌላ ሴት ትዳር የምታውቅ ሌላ ሴት የምትወደደው መስሎ አይሰማውም።ለሱ ሀዋ ልክ እንደ አደም ለሱ ሀዋው ነች ሌላ ሴት አያውቅም ሌላ ፍጥረት ለሱ የሌለች ያህል የብቸኝነት ይወዳታል ያፈቅራታል ይንከባከባታል።

በርግጥ ሙና ይሄንን ሳታውቅ ቀርታ ነው ወይ ለማለት በእጅጉ ያዳግታል ምክንያቱም የሀዋ እና የሰሚር ፍቅር ግልፅ ነው አይደለም እቤት አይደለም ቤተሰብ መስሪያ ቤት እንኳን አምልጧቸው ይወጣል።ከአናት እንዳለ ኮፍያ ከየትኛውም ርቀት የሚታየው ፍቅራቸው ለማንም ያስቀናል። ከአይን ያውጣቸው የሚባለውን ውዴታቸውን የማያውቅ እነሱን የማያውቅ እንጂ አንድ ቀን የሚያውቃቸው ሰው የነሱን ፍቅር ሳይመለከት ሳይቀና ፈገግ ሳይልና ሳይገረም አያልፍም።ትናንሽ ህፃናቶች ተዋደው እየተራራጡ እንጂ የልጆች እናት እና አባት እንኳን አይመስሉም። ይሄን ፍቅር ለመቀማት ጓግታ ለራሷ ለማድረግ ሙና በሞኝነቷ ተመኝታለች ።ሁሉም በጭንቀት እና በስስት ሰሚርን ይመለከታሉ። ዶክተር በር አንኳክቶ ገባ ከመካከላቸው አንድን ሰው ማናገር እንደሚፈልግ ነግሯቸው እትዬ መርየምን ይዞ ወደራሱ ክፍል ሄደ።ይሄኔ ሙና ምትፈልገው ተሳካላት ሱመያ እና ኻሊድን በብቸኝነት በግላጭ አገኘቻቸው።እነሱን ልታወራ ሀሳቧን ልታሳምን ጉሮሮዋን በመጠራረግ ላይ ሳለች ድንገት ሰሚር ነቃ ሁሉም ደነገጡ ከተቀመጡበት ቆም አሉና ወደ ዶክተር መሯሯጥ ያዙ ዶክተር ዶክተር ሰሚር ነቅቷል።


ክፍል አስራ አንድ (11) ይቀጥላል .....

#ልዩ_ምስጋና ZU23 እና ለሰኪና ራህመቶ

@Strong_iman
1.3K views𝐒̧𝐔𝐃€𝐘𝐒, 17:59
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-08-31 20:59:39 #ሀዋን ማን ገደላት ልብ አንጠልጣይ ታሪክ

#ክፍል 10

#ደራሲና_ተራኪ:– አብዲ ኢኽላስ

@Strong_iman
1.0K views𝐒̧𝐔𝐃€𝐘𝐒, 17:59
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-08-31 20:58:19 "ሀዋን ማን ገደላት "
( አብዲ ኢኽላስ)

ክፍል ዘጠኝ(9)

ሙና እራሷን ይበልጥ ወደ ሰሚር አስጠግታ ከአጠገቡ አረፍ አለች። በጣም አስታዋለችው። ፊቶቹን በትዝብት በግርምት እና በስስት ተመለከተችው። ሳታስበው ፈገግ ትላለች ልታናግረው ሞከረች:: ቃላቶች አልተባበር አሏት። የምታጣው ቃል ሲከብዳት<< የልቤ ጀግና እንዴት ነህ? አሁን ምን እያሰብክ ይሁን? ሀዋ ትዝ እያለችህ? ስለሷ እየተጨነክ ነው? ቆይ ምን እያሰብክ ነው? ስለ ሀዋ እንድነግርህ ትፈልጋለህ? ምንድ ነው ግን እያሰብክ ያለኸው? ስለማን ላውራልህ? የኔ ጀግና አንዲት ቃል እንኳን መልስልኝ እኔ እኮ ወድሀለው።>> ብላ ቃላቶችን ተነፈሰች። ይሄኔ ያሉበት ክፍል ተንኳክቶ ነርሶቹ ብቅ አሉ። ገነር ግን ገና እንደገቡ በጣም ደነገጡ። ሙና የራሷን አልጋ ትታ የታማሚ አልጋ ላይ በመተኛቷ እጅግ በጣም ተናደው በሀይል ጮሁባት አመናጨቋት። ገላመጣትም። በጣሙን እየተቆጡ ድጋሚ እንደዚ አይነት ድርጊት እንዳፈፅም አስጠነቀቋት። ምክንያቱም ታማሚ አጠገብ መተኛት በእጅጉ ክልክል እና ነውር ነውና እነሱ እጅግ ልክ ናቸው። ሙና በድርጊቷ አፈረች:: አጎነበሰችም:: በጣም ደንግጣ ይቅርታ ጠየቀቻቸው። ጥፋቷን ለማቅለል ስትልም<< እኔ እኮ ባለቤቱ ነኝ የልጆቹ እናት ነኝ እጅግ ስለናፈቀኝ እንጂ ለክፋት አደለም።>> ብላ ዶክተሮቹን አባበለች እነሱም ተረዳት። ለምሽት ሚያስፈልገውን መርፌ ወግተውት መልሰው ወጡ። በሩን ዘጉላት:: ሙና ድጋሚ ስህተት መስራት ስላልፈለገች ከርቀት ሆና ታስተውለው ጀመር።

እትዬ መርየም ኻሊድ እና ሱመያ እቤት ውስጥ እንቅልፍ አሎስድ ብሏቸው ይንቆራጠጣሉ። ግራ ይጋባሉ። የሚያወሩት ጠፍቷቸው እርስ በርስ ይተያያሉ። ማንም ለማንም ምንም ማለት አልቻለም። የሚሉት ግራ ገብቷቿል እቤቱን ሀዘን ወረረው: በጣም ይጨንቃል:: በጣም ያስፈራል። ሁለት ሰው ጠፍቶበታል ድንገት ምን እየተፈጠረ ነው? እዚ ቤት ውስጥ ምን እየሆነ ነው
? ያ ሁሉ ሰላም ያ ሁሉ ጨዋታ ያ ሁሉ ደማቅ ፍቅር በሙሉ ለማነው ያስቀናው? ከማን ጉሮሮ አሎርድ ብሎ ነው? እንደዚ አይነት አስቀያሚ ድባብ የጋበዛቸው? መጥፎ ስሜት ያወለላቸው ምን አጥፍተው ነው? ይህ ቤተሰብ ማንም ላይ ደርሶ አያቅም ጎሮቤት አክባሪ ጮሆ እንኳን ማይጫጫህ እጅግ ሰላማዊ የሰፈሩ ሰው ሁሉ ያመሰገነው ሰላማዊ በጣም ለዘብተኛ የሆነ ቤተሰብ አልነረምን? ምን ነክቶት እንደዚ ፍርስርሱ ወጣ። የሀዘን ድባብ ከመቼውም ጊዜ በላይ ለምን እዚ ቤት ላይ አጠላ? ክፉ ያሰበላቸው መጥፎ ያቀደላቸው ሀዘናቸውን የተመኘው ይህ እኩይ አካል ማን ይሁን? ግራ ገብቷቸዋል እስኪ ደግሞ

..... ወደዛን ጊዜ ወደ ሀዋ ስሜት እንመለስ ሀዋ የዛን ቀን ምን ነበር የሆነችው? በሷ ላይ የተፈጠረው ምን ነበር? ሀዋ እንደዛ ፈርታና ተጨንቃ የነበረችው ግራ የተጋባችው በመብራቱ መጥፋት፣ በዝናብ መዝነብ፣ በመብረቁ ጩኸት፣ በጨለማው፣ በሁኔታዎቿ፣ በስልኳ መጥራት በሙሉ ስትርበተበት ስትደነግጥ እና እንደዛ ስቶን የነበረው ምን ሆና ይሁን? የጭንቀቷ የመፍራቷና የመረበሿ ምንጭ ካሌብ ነው። ካሌብ የሀዋ የድሮ እጮኛ ነው። ከሰሚር በፊት ያወቀችው አብራው ብዙ የሆነች የነበረ ነገር ግን ሀገር በመክዳት ከባድ ወንጀል ተጠርጥሮ በአሜርካ ወስጥ ለረጅም ጊዜ ከትቦ የነበረ በመንግስት ለውጥ ደሞ ይቅርታ ተደርጎለት ድንገት ወደ አዲስ አበባ ብቅ አለ። የድሮ ፍቅረኛዋ ነው። ከፍቅረኛም በላይ ለመጋባት ቀን ቆርጠው ጥሪ ካርድ በማሰራት ላይ ሳሉ ድንገት አላስፈላጊ ወንጀል ውስጥ ገባ። ካሊብ ሀዋን አብዝቶ ሚወዳት ለሷ ሂወቱን አሳልፎ ይሰጥ የነበረ ነው። ካሊብ እሷን ብሎ እስልምናን ተቀብላል። እሷን ካየ በኃላ እስልምናውን በተማርኩት ወደ መንገዱም ገብቶ ነበር።

ካሊብ የተደበቁ ማንነቶች ቢኖሩትም እሷ ግን ስለየትኛውም ማሰብ አትፈልግም። <እሱ ለኔ የልቤ ጀግና ብቻ ነው ሌላው የሌላ ነው እኔ ሚያገባኝ የኔ ድርሻ ነው።> ትል ነበር። ሀዋ እኮ ፍቅር ጉዳይ አትደራደርም። ልቧን ያሸነፈ ሁሉ ለሷ የምን ጊዜም ጀግና ነው የምን ጊዜም ልዩ ሰው ነው። ሁሌም በሷ ከለላ ስር ነው ትከራከርለታለችም <ምንም መጥፎ ቢሰራ መጥፎ እንዳለው ሁሉ ጥሩው የጎላ ነው።> ትላለች። ታዲያ ካሊብ ለረጅም አመታት አሜርካ ሰንብቶ ምን እንደደረሰ የት እነደነበረ እንኳን ሳያሳውቃት ደብዛውን አጥፍቶ ወንጀሉን ሰርቶ ስላመለጠ የት እንደሄደ በምንም ሳታውቅ ከቆየች በኃላ ድንገት ብቅ ብሎ ነበር። እሱ ሲመለስ ከምቶደው ውዱ ባሏ ሰሚር ሁለት ልጆችን አፍርታ ነበር። ታዲያ ሂወቷን ገብቶ ሊበጠብጥ እንዳሰበ ወደ እሱ ካልመጣች አንድ በአንድ ልጨርሳቸው ብሎ ዛቻ ዝቶባት ነበር። ይሄ ለሀዋ በጣም አስፈርቷት ነበረ። የዛን ቀን ምሽት ከሌሎቹ ቀናት በላይ የተጨነቀችው <<ጠዋት እጅግ ጠዋት መጥቼ አገኝሻለው ስመጣ ላይሽ ፈልጋለው አብሬሽ መሆን ፈልጋለው ከዛም ተያይዘን ወደ አሜርካ እኔዳለን። ልጆሽን ለአያትሽ እና ለባልሽ መተው ትችያለሽ። እኔ ስነሱ ግድ የለኝም ይህ ካልሆነ ሂወትሽ ይመራል።>> ይህ የካሊብ ዛቻ ነበር። ታዲያ ካሊብ ይሄንን ዛተ እንጂ የዛን ቀን መጣለው አላለም። የዛን ቀን ምን አስፈራት? የዛን ቀን ሀዋን ምን ነካት? ካሊብ ነገ መጥቼ አገኝሻለው ብሏት ሳታንገራግር በፍርሀት እና በጭንቀት እሺ ብላው ጠዋትን አየጠበቀች እየፈራች ነበር እንጂ የዛን ቀን ምሽት ድንገት ምን ልቶን ትችላለች?

ኻሊድ ሱመያን አባብሎ አስተኛት። አባታቸው ሆስፒታል በመሆኑ በጣም አልቅሳ የነበረችው ሱመያ ድክምክም ስላላት ተኝታለች። እትዬ መርየም እና ኻሊድ ብቻቸውን ተቀምጠዋሉ። እሳቸው ሁሌም ስለ ኻሊድ ሲጠየቁ <<እሱ ትንሽ ልጅ አደለም እሱ እኮ ትልቅም ጭምር ነው።>> ይላሉ እውነት ናቸው አልተሳሳቱም ኻሊድ ትንሽ ብቻ አደለም። እውስጡ ትልቅም ጭምር ነው ለዚህም ነው ድንገት ሳያስቡት አንዳች መፍትሄ ያመጣው። ኻሊድ ሀዋ ምን እንደሆነች ለማወቅ የሀዋን ስልክ የመጨረሻ ቁጥሮች የተቀዳም ሪከርድም ካለ ማወቅ እንደሚችሉ ሀሳብ አመነጨ። ይሄኔ እትዬ መርየም ከኻሊድ ሀሳብ የመነጨ መሆኑን ማመን አልቻሉም። በጣም ደነገጡ። እየሮጡ የሀዋ ስልክ ከተቀመጠበት አውጥተው በርጋታ በጥንቃቄ ስልኩን አበሩት። ይሄኔ መጨረሻ ላይ የተደወሉ ስልኮችን ሲመለከቱ ዝቅ ብለው ሲያዩ የካሊብን ተደጋጋሚ ስልኮች ተመለከቱ መጨረሻ ላይ የመጨረሻ ስልክ ሲያዩ ግን አላመኑም። ከሀዋ ጋር የተደዋወለው የመጨረሻ ስልክ አጭር ደቂቃ አውርቶ የዘጋው ይህ ቁጥር እህቴ ሙና ብሎ ተመዝግባል።

ክፍል አስር ይቀጥላል,,,,,,,,,

#ልዩ_ምስጋና ለፌሩዝ (ቅመም) እና ለሰኪና ራህመቶ

@Strong_iman
1.1K views𝐒̧𝐔𝐃€𝐘𝐒, 17:58
ክፈት / አስተያየት ይስጡ