Get Mystery Box with random crypto!

በአገልጋይ ዮናታን አክሊሉ ስም በተመዘገቡ ንብረቶች ላይ የሃራጅ ማስታወቂያ ወጣ፡፡ በአገልጋይ ዮ | Skyline media

በአገልጋይ ዮናታን አክሊሉ ስም በተመዘገቡ ንብረቶች ላይ የሃራጅ ማስታወቂያ ወጣ፡፡

በአገልጋይ ዮናታን አክሊሉ ስም በተመዘገበ ንብረት ላይ የሃራጅ ማስታወቂያ ያወጣው ንብ ኢንተርናሽናል ባንክ ነው፡፡

ባንኩ ሰኔ 13 ቀን 2015 አመት በአዲስ ዘመን ጋዜጣ ላይ ባወጣው የሃራጅ ማስታወቂያ፣ በአገልጋይ ዮናታን አክሊሉ ስም የተመዘገቡ ንብረቶች በሃራጅ እንደሚሸጡ አስታውቋል፡፡

በዚህም መሰረት በዮናታን ስም የተመዘገበ ሃዋሳ ከተማ ላይ የሚገኝ 400ካሬ ሜትር ይዞታ ላይ ያለው ባለ ሶስት ወለል መኖሪያ ቤት አንደኛው ሲሆን፣ በ22 ሚሊዮን ብር የሃራጅ መነሻ መሸጫ ዋጋ ተቀምጦለታል፡፡

እንዲሁም በዮናታን አክሊሉ አንጄሎ ዜብራ ግሪል ሃላፊነቱ የተወሰነ የግል ማህበር የተመዘገበ ሃዋሳ ከተማ ምስራቅ ክፍለ ከተማ የሚገኝ 1ሺህ 271 ካሬ ሜትር ላይ ያረፈ ህንጻ ሌላኛው በሃራጅ እንዲሸጥ ጫረታ የወጣበት ሲሆን 30 ሚሊዮን ብር የሃራጅ መነሻ ብር ተቀምጦለታል፡፡

ሌላኛው በሃራጅ እንዲሸጥ ጨረታ የወጣበት ደግሞ በዮናታን አክሊሉ አንጄሎ ዜብራ ግሪል ሃላፊነቱ የተወሰነ የግል ማህበር የተመዘገበ በአዲስ አበባ ከተማ ቦሌ ክፍለ ከተማ የሚገኝ በካርታ ቁጥር የተመዘገበ 500 ካሬ ሜትር ይዞታ ያለው መኖሪያ ቤትም ይገኝበታል፡፡