የሕዳሴ ግድብ ግንባታ 90 በመቶ ተጠናቋል፦ የታላቁ ሕዳሴ ግድብ ማስተባበሪያ ፕሮጀክት ጽ/ቤት **** የታላቁ ሕዳሴ ግድብ ግንባታ 90 በመቶ መጠናቀቁን የታላቁ ሕዳሴ ግድብ ማስተባበሪያ ፕሮጀክት ጽ/ቤት አስታወቀ። የሕዳሴ ግድብ መሠረተ ድንጋይ የተጣለበት 12ኛ ዓመት የቦንድ ሳምንትን አስመልክቶ ጽ/ቤቱ፣ የኢትዮጵያ ልማት ባንክ፣ ሴት ነጋዴዎች ማኅበር እና ሌሎች ማኅበራት የጋራ ጋዜጣዊ መግለጫ ሰጥተዋል። ለግድቡ ሲደረግ የነበረው ድጋፍ የፖለቲካ ልዩነት፣ ዕድሜ እና ጾታን ሳይገድብ የተደረገ መሆኑን የታላቁ ሕዳሴ ግድብ ማስተባበሪያ ፕሮጀክት ጽ/ቤት የሕዝብ ግንኙነት ዳይሬክተር አቶ ኃይሉ አብረሓ ገልጸዋል። 937 viewsAnt B, 18:01