Get Mystery Box with random crypto!

የፍቅር አለም LOVES WORLD

የቴሌግራም ቻናል አርማ silefikrr — የፍቅር አለም LOVES WORLD
የቴሌግራም ቻናል አርማ silefikrr — የፍቅር አለም LOVES WORLD
የሰርጥ አድራሻ: @silefikrr
ምድቦች: ያልተመደበ
ቋንቋ: አማርኛ
ተመዝጋቢዎች: 1.98K
የሰርጥ መግለጫ

"💞ፍቅር💞
❤ገደብ የሚባል ነገር❤
አያውቅም አይቀበልም
መሰናክል እና አጥር ዘሎ ግንብ ደርምሶ
መድረስ ያለበት ቦታ ይደርሳል
ምክንያቱም💕ፍቅር💕እውነት ነው
እውነትም አሸናፊ ነውና::”
ለማንኛውም ጥያቄ እና አስተያየት
@manda0 @silefikirbot
Twitter account @mandelafikre
For stickers
https://t.me/addstickers/Mandua

Ratings & Reviews

2.67

3 reviews

Reviews can be left only by registered users. All reviews are moderated by admins.

5 stars

0

4 stars

1

3 stars

0

2 stars

2

1 stars

0


የቅርብ ጊዜ መልዕክቶች 2

2022-01-31 11:23:07 እኔስ ግራ ገባኝ

ገጣሚ፡ ማንዴ የእጅጓ ልጅ

የኔ ፍቅር የኔ አለም ብዬ እንዳልጀምር
እንዴትስ ልመንሽ ከኔ እንደያዘሽ ፍቅር
ልጠላሽ አስቤ ልርቅሽ እልና
ፍቅርሽ አይሎብኝ ይሆናል ገናና

የኔ ፍቅር...........
እኔ አፈቅርሻለው በሱ ጥርጥር የለኝም
ካንቺ ሌላ ለኔ ከቶ አይታየኝም
ስበላ ስጠጣ ስተኛ ስነሳ ከሀሳቤ አትጠፊም
ማፍቅር መታደል ነው ከፈጣሪ የሚሰጥ ስጦታ
ደስተኛ አድርገሺኛል ይክበርልኝ ጌታ
ከማፈቅርሽ በላይ እጥፉን ላፍቅርሽ
ከምወድሽ በላይ እጅጉን ልውደድሽ
ከምሳሳልሽ በላይ በሀይል ልሳሳልሽ
አንቺ ነሽና ያለሽኝ የዚች አለም ምላሽ

ግን እኮ ፍቅር.........
ፍቅር ደስታ እንዳለው ሁሉ ፍቅር ስቃይ አለው
እንዴት ብለሽ ካሰብሽ እኔ እነግርሻለው
በጣም የሚያሰቃይ ከባድ ነበልባል ነው
እሳቱ ሲገርፈኝ ለብቻዬ የፍቅር ወላፈን
የሚያስታመኝ ሳጣ አይዞህ የሚለኝ ከጎን
ስቃዩ ሲበረታብኝ የምሆነውን ሲያሳጣኝ
አንቺን አስባለው ትንሽ እንዲያስታግሰኝ

እና የኔ ፍቅር.......
ምነው ዘገየብኝ ልትሆኚ ከጎኔ
ለነብሴ እርካታ ለህይወቴ ብርሀኔ
ይብቃህ ፍቅር ብለሽ አውጪኝ ከዛ እሳት
ፍቅርን ስጪኝና ህይወቴን ሙሉ አድርጊያት
አንቺ ምትሞዪበት ጎዶሎ አለባት
በደስታ ስካር እኔም ምድርን ልሙላት
እናም የኔ ፍቅር ሁሌም ሁሌም ከልቤ አፈቅርሻለው
ፍቅሬም ሳይጎልብሽ ሁሌም እጠብቅሻለው
አንድ ቀን እንደምትመጪ በርግጥም አምናለው
አምላክ አንቺን እንደሚሰጠኝ በልቤ በአትሜሻለው።

STAY WITH US @silefikrr FOR MORE!!
2.4K views08:23
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2021-12-09 20:05:50 ሰላም ቤተሰቦች
ታሪኬን የማካፍላችሁ M ነኝ ከሀዋሳ። በጣም የምወዳት ልጅ አለች በፍቅር መኖር ከጀመርን ቆየን በምንም ሁኔታ ላጣት አልፈልግም። እና አንዳንዴ የምታደርገው ንገር ግራ ይገባኛል አትወደኝም ብዬ እንዳልደመድም ትወደኛለች..ትወደኛለች ብዬ እንዳልደመድም ደሞ አንዳንዴ የምታደርገው ነገር እንኳን ለሚወዱት ሰው ለማይወዱትም ነው። እናም ግራ ገባኝ ምን እንደማደርግ ቤተሰቦቼ እናንተ በኔ ቦታ ብትሆኑ ምን ታደርጋላችሁ።

ሀሳባችሁን @silefikirbot ላይ አስቀምጡልኝ
2.5K views17:05
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2021-12-03 18:50:23 እርሶ ቢሆኑ ምን ያደርጋሉ ፕሮግራም ልንጀምር አስበናል ስንቶቻችሁ ትስማማላችሁ
2.5K views15:50
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2021-12-02 10:13:07
2.5K views07:13
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2021-06-28 22:59:03 ላበት በት

ንሽ ወጪ እኔን እቤቱ ወስዶ ቢያሳድገኝ ኖሮ እንደዚህ ዓይነት ህይወት
ውስጥ ባልተዘፈኩ ነበር። ስለዚህ ለኔ ና ለመሰልቼ ህይወት መበላሸት እያንዳንድሽ ተጠያቂ ነሽ።
አንተም ብትሆን ታሪኬን በሚጥም ቋንቋ ከሽነህ ፅፈህ እየፖሰትክ ዝናህን ትገነባለህ ፣ በመፅሐፍ
አሳትመህ ትሸቅልበታለህ እንጂ ምንም የምትፈይድልኝ ነገር እንደሌለ አውቀዋለሁ። እንዲያው
ቀለል ስለሚለኝ ነው ላንተ የምቀደደው "አለችኝና ለጥቂት ደቂቃ ዝም አለችኝ።
" የምናገረው ልክ ነው አይደል? አስከፍችሄ ከሆነም ሶሪ"
"ምንም የተሳሳትሽው ነገር የለም ልክ ነሽ! ታሪክሽን እየፖሰትኩ ላይክ እሰበስብብሻለሁ እንጂ ምን
እፈይድልሻለሁ? ኧረ ልክ ነሽ"
" እሺ....ከዛ በህክምናው አልሆን ሲለኝ ፣ በየፀበሉ ይዤው ተንከራተትኩ። ሌሎቹን በምህረት ዓይኑ
የተመለከተ የፈውስ ጌታ እኔና ልጄን ግን በጎሪጥ እንኳን ሊያየን አልወደደም። ታዲያ በየገዳማቱ
ደም ዕንባ ሳለቅስ ያዩኝ ሰዎች 'አይዞሽ ለበጎ ነው' ይሉኛል። ምንድነው ለበጎ ነው ማለት? እኔ
እንደዚህ አይነት አማርኛቸው አይገባኝም! ፍጠረኝ ሳልለው ፈጥሮኝ ልጅነቴን ሲኦል አደረገብኝ::
የአርባ ቀን ዕድሌ ላይ ሽርሙጥናን ፅፎ የማንም አተላም መጫወቻ አደረገኝ:: ምንም ያላጠፋውን
አንድ ልጄን በሽተኛ አደረገብኝ:: እውነት አሁን ይሄ ለበጎ ነው!?!? ደግሞ ለማፅናናት ብለው
አይዞሽ በፈተና የሚፀና ሰው እርሱ የተባረከ ነው ይሉኛል። ኧረ ኤዲያ እኔ ላላየኋት ገነት ብዬ ኑርዬን
ገሀነም ያደረገብኝን ጌታ አላመልከውም! ምነው ያኔ ለእስራኤላውያን ዳቦን ድንጋይ እያደረገ
አልነበር እንዴ ያበላቸው የነበረው ፣ አላዛርን ከሞት አስነስቶ አልነበር እንዴ እህቶቹን ያስፈነደቀው
ለኔ ሲሆን ምነው ጆሮው አልሰማ አለው? ኧረ እኔ አላመልከውም!! አልፈልግም ይቅርብኝ!! ከዚህ
በኋላ ህይወቴን ቢያንደላቅቀው እኔ ልደሰት ነው¡¿ ሰላሳ አምስት አመት ሙሉ አሰቃይቶኝ ፣ ዛሬ
ከሽርሙጥናዬ ቢያላቅቀኝ ፣ ልጄን አያደርገውም እንጂ ጤነኛ ቢያደርገው ማምሻ ዕድሜ ነው ብዬ
ደስተኛ ልሆንለት ነው! አይመስለኝም።
የፀበሉ አልሳካ ሲለኝ ደግሞ ወሎና አሩሲ ሄጄ አዘየርኩ ፣ ዲቤ አስደለኩ ፣ ጫት አስተፋሁበት
አሁንም ለሌሎቹ የሰራ ዝየራ ልጄ ላይ ገገመ! በየጠንቋዩ በየአውሊያው ፣ ቦረንትቻና ቃልቻ ባለበት
ቤት ሁሉ እየሄድኩኝ አፈነደድኩ......አራት ቀንድ ያለው በግ አምጪ በደሙ ከታጠበ ይድናል ሲሉኝ
ሀያ ሺ ብር በፍለጋ ወለጋ ድረስ ሄጄ ገዝቼ አመጣሁ ፣ እንዳሉት በደሙ ታጠበ። አሁንም ለሌላው
የተለመነ ሰይጣን ለኔ ሲሆን የፈውስ ምትሀቱ አቅም አጠረው! በየደብተራው ቤት መልክዐ
ሳጥናኤልን አስደገምኩበት እነዛ ሙታንን የሚያናግሩ የስንቱን ትምህርቱንና ንግዱን እንዳይሳካለት
ሲተበትቡ የከረሙ ሁሉ እኔ ልጅ ላይ ሲደርስ ጥቁር አስማታቸው አልሰራ አላቸው። በፓስተር
አፀለይኩለት ፣ የሱ በሽታ ግን ወይ ፍንክች አለ! እኔም ተስፋ ቆረጥኩኝ " አለችኝና ዕንባዋ እየወረደ
በድጋሚ መጦዝ ጀመረች።
አማልክቱ ይቺን ምስኪን ሴት ከሰዶምና ከገሞራ ህዝቦች በላይ ከካህኑ ኤሊ ልጆች በላይ ሒትለር
በእሳት ከቀቀላቸው ስድስት ሚሊዮን አይሁዳውያን በላይ የዘር ጭፍጨፋ ከደረሰባቸው ከሬድ
ኢንዲያንና ከቀደምት የአውስትራሊያ ህዝቦች በላይ በነጮች ና በአንኮ መሪዎቹ ደሙ
ከሚመጠጠው ከአፍሪካ ህዝብ በላይ የወያኔና የቻይና አሻንጉሊት ከሆነው ከመከረኛ የሀገሬ ህዝብ
በላይ ብዙ ስቃዮችን አድርሰውባታል።
"ወንዴ"
"አቤት"
"ምን ላይ ነበር ታሪኬን ያቆምኩት?"
"ትዳር ውስጥ እንዳልገባ ኤልያስ ደካማ ጎን ነበረው ብለሽ"
"አዎ ምን መሰለህ? የሱ ትልቁ ችግር እኔም እንዳላገባው ያስፈራኝ የነበረው...............
:
:
:
ይቀጥላል

╔═══❖• •❖═══╗
@silefikrr
╚═══❖• •❖═══╝
4 any comment
@silefikirbot
❥❥________⚘_______❥❥
4.7K views19:59
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2021-06-28 22:57:26 ባሌ በ50 ብር ሸጠኝ !

ክፍል 10

==========================
አፏ ውስጥ የአፍ ጠረን ማጥፊያ ስፕሬይ ነፋችና በሩን ከፈተችው፡፡በሩ ላይ አንዲት አሮጊት ሴትዮ
ቆመዋል "አቢስ?!" አለቻቸው ፣ ለጥቂት ሰከንዶች ዝም አሏትና "ራሱን ሲስትብኝ ነው ወዳንቺ
የመጣሁት" ሲሏት እየከነፈች ወጣች። ሴትዮ ጭስ ባጨናበሰው አይናቸው እኔን ገርመም
አድርገው አይተውኝ ከቅንድባቸው እስከ አገጫቸው ባለው ሙሉ የፊታቸው አካል አሽሟጠጡና
ተከትለዋት ሄዱ።( ሴትዮዋ ሲያዩኝ ለምን አሽሟጠጡ? ) እኔ ምን ማድረግ እንዳለብኝ ግራ ገባኝ።
ተከትያት ልሂድ ወይስ ቤቱን ልጠብቅ? የተፈጠረውን ነገር ለማየት ልቤ ስለቋመጠ እግሬ ሳይታዘዝ
ከተቀመጠበት ብድግ ብሎ ከቤት ለመውጣት ተጣደፈ፡፡ በሩን መለስ አደረኩት።
ራሔል ከፊት ከፊት ፣ ሴትዮዋ ከኋላ ከኋላ ፣ እኔ ደግሞ ከሁለቱም ኋላ ሆኜ ከባልደራስ
ኮንዶሚኒየም በስተምሥራቅ በኩል ወደ ሚገኘው ሞቃዲሾ ወደ ሚባለው ሰፈር ሄድን። ከፍርዬ ሱቅ
ወደዚህ ያለ ቆርቆሮ ግቢ ውስጥ ዘለቅን።( ይቺ ፍርዬ ከድሮም ጀምሮ ሳውቃት እንዲሁ እብድ
እንደነበረች ነው። አሁንም ልጆች ወልዳም እዛ ሶስት ዕቃ ብቻ የተደረደረበት ሱቋ ውስጥ
እየለፈለፈች አለች። ድሮ ኮኮበፅብሐ ተማሪዎች እያለን በሷ ሱቅ ጋር ስናልፍ ጆተኒ ስለነበራት
ከቢትወደድ ተማሪዎች ጋር እጃችን እስኪጠቁር ድረስ ቁማር እንጫወት ነበር )
የቆርቆሮ ግቢዋ ውስጥ እንደገባን አንዲት ግድግዳዋም ፣ መሬቷም ፣ ኮርኒሷም ፣ ዕቃዎቹም
ከአፈር የተሰሩባት ቤት ውስጥ ወደ ውስጥ ዘለቅን። ቤት ውስጥ የምትበራው ቢጫዋ አምፖል
በጥላሸት ደብዝዛ ቤቱን ለማጨለም እንጂ ብርሀን ለመስጠት የተቀመጠች አትመስልም። ከበሩ
ትይዩ ባለው የጥጥ ፍራሽ የተነጠፈበት የሽቦ አልጋ ላይ የራሔል ልጅ የአፉ ለሀጭ አየር ላይ
ተንጠልጥሎ ራሱን ስቶ በፀጥታ ተጋድሟል።
ራሔል እቅፍ አድርጋ አነሳችው። "አቢ......አቢ.....ባባዬ....ባባ...." አቤት እንዴት
እንደምትንሰፈሰፍ ብታዩዋት! ያ ስንት ሜካፕ የለመደ ፊቷ በንፍጥና በዕንባ ጨቅይቶ ብታዩት
ሳትወዱ በግድ እንድታዝኑ ታደርጋችኋለች። ሁሏም ሴት ለካ እናት ስትሆን አንጀት ትበላለች። ፊቷ
ላይ ያለው የመረበሽ ፣ የመጨነቅ ፣ የመደናገጥ ስሜት ሴት በመሆን ብቻ የሚገኝ ሳይሆን እናት
ሲሆኑ ብቻ የሚሰጥ ልዩ ፀጋ ነው። ስለዚህ እናቱ የሄደችበትም እናቱ የሞተችበትም ህፃን እኩል
ያለቅሳሉ ብቻ ሳይሆን መባል ያለበት ልጇ የታመመባትም ፣ ልጇ የሞተባትም እናት እኩል
ይደነግጣሉ! የሚል አባባልም ሳያስፈልገን አይቀርም።
ወፍራሙ ልጇ ቀስ ብሎ ዓይኖቹን ገለጣቸው። የደስታ ዕንባ ከዓይኖቿ እየወረደ ሰፊ ፊቱን
እየደጋገመች ሳመችው። ልጇ ግን አሁንም ከአፉ ለሀጭ እንደተቀቀለ የተልባ ውሀ እየተምዝለገለገ
ይወጣል። እዚች አፈር ቤት ውስጥ በቆየንባቸው ወደ አንድ ሰዓት ገደማ አንዲትም ቃል
አልተነፈሰም። ወፍራምና ሰፊ ፊቱ ላይ ምንም አይነት ስሜት አይነበብበትም። ዓይኖቹ አንድ ቦታ ላይ
ብቻ ፍጥጥ ብለው ካዩ አይንቀሳቀሱም።
"ወንዴ ብር ይዘሀል እንዴ?" አለችኝ ራሔል.....ለካርድ መሙያ ብዬ የያዝኩትን ሀምሳ ብር
አውጥቼ ሰጠኋት። ለሴትዮዋ እየሰጠቻቸው
"ማዘርዬ ይሄ የትናንት ነው የዛሬውን ደግሞ ወደ ማታ መጥቼ እሰጥዎታለሁ" ሴትዮ በቀረባቸው
ሒሳብ በስጫ ብለው ነው መሰለኝ ፊታቸውን ከሰከሱት። ብሩን ለመስጠት ከተዘረጋው እጇ ላይ
መንጭቀው ወሰዱት።
"..አ...ይ .....እንዲያው ያንቺ ጣጣ ማብቂያ የለውም.....ለማንኛውም ምግቡም እያለቀ ነው
እሱንም በዛው ይዘሽ ነይ" አሏት። ራሔል ሴትዮዋን በእሺታ መልክ አይታቸው ፣ ልጇን ፊቷ ለሀጭ
በለሀጭ እስኪሆን ድረስ ስማው ከቤት ወጣን። ወደቤቷ እየሄድን መሬት የሚበሳ ዕንባዋን
ታዘንበው ጀመር። ላባብላት ስሞክር ስለባሰባት ዝም አልኳት።
ቤቷ እንደ ደረስን እየተጣደፈች ከቁም ሳጥኗ ውስጥ በሮል የተጠቀለለች አንዲት እስቲክ ጋንጃ
አወጣችና እየተክለፈለፈች መጦዝ ጀመረች። ጦዛ ስትጨርስ ቀስ በቀስ ተረጋጋች። እኔ ሙሉ
ስሜቷን ለመረዳት እሷ እስክታወራ ድረስ ዝም ብዬ ጠበኳት።
"ረበሽኩህ አይደል ወንዴ?"
"ምን አደረግሽኝና!"
"ሁሌም አቢን ካየሁት እንዲህ ነው የምሆነው ቅድም የተደነባበርኩት እሱን ይዛው የመጣች
መስሎኝ ነው። ወንዴ መቼም ብዙ ታሪኮቼን ዘክዝኬልህ ይሄንን ልዋሽህ አልፈልግም ፣ ሌላዋ
የታደለች እናት ልጇ ከአጠገቧ እንዲርቅ አትፈልግም። እኔ ግን ልጄ አጠገቤ ሆኖ ለአንዲት
ሰከንድም ሠላም ስለማላገኝ ይቺ ያየሀትን ሞግዚት ሴትዮ ጊዮርጊስ ሲለምኑ አግኝቻቸው ቤት
ተከራይቼላቸው ፣ ቀለብ እየቆረጥኩላቸው ፣ በቀን 50 50 ብር እየሰጠኋቸው ከሳቸው ጋር እንዲኖር
ነው ያደርኩት። ለሰው እንዲህ አደረኩ ተብሎ ባይወራም ከዛ ህይወት ያወጣኋቸው ሴትዮ የአንድ
ቀን ሒሳብ ሳሳስልፍባቸው ሊበሉኝ ነው የሚደርሱት። ቅድም የመጡት የአቢ ራሱን መሳት
አሳስቧቸው እንዳይመስልህ ፣ የትናንቱን ሒሳብ ስላልሰጠኋቸው እግረ መንገዳቸውን ሊቀበሉኝ ነው
የመጡት እንጂ የሱ ራሱን መሳትማ የለመዱት ነገር ነው።
እንዳየኸው የአእምሮ ህመምተኛ ነው። በሽታው ደግሞ የአእምሮ ብቻ እንዳይመስልህ አምስቱም
የስሜት ህዋሳቶቹ ምንም ነገር ሴንስ ማድረግ አይችሉም። ዓይኖቹ የሚያዩ ይመስላሉ ግን አያዩም
፣ ቆዳውን ብትቆነጥጠው ብትመታው ምንም አይሰማውም ፣ ጆሮው አይሰማም ፣ ምላሱ ምንም
ነገር አያጣጥምም አይናገርም ፣ አፍንጫው ምንም ዓይነት ሽታን መለየት አይችልም......ታዲያ
የእናትነት አንጀቴ አስችሎኝ እንዴት አብሬው ልቀመጥ? አንቺም እንደእናትሽ ያው ጨካኝ ነሽ ብሎ
ታሪኬን የሚያነቡ ሰዎች ሊፈርዱብኝ ይችላሉ። መቼም ያልተነካ ግልግል ያውቃል ፣ በሰው ላይ
መፍረድ በጣም ቀላል ነው። እኔ ግን ከሱ ጋር ስሆን ልቤ እንዴት እንደሚቆስል አምላክ ብቻ ነው::
ከኔ ሲለየኝም ሰላም ስለማላገኝ የማልጠቀመው የሱስ ዓይነት የለም ፣ ራሴን ለመርሳት ብዙ ነገር
ውስጥ ለመደበቅ እጥራለሁ። መፅመፍቶች ውስጥ እመሸጋለሁ ፣ ያንተ ድድ ማስጫ ላይ ተጥጄ
እውላለሁ ፣ ፌስቡክ ላይ ያሉ ፀሀፊዎችን እያሳደድኩ አነባለሁ። በዚህ የተነሳም ነው የማንበብ ሱስ
የያዘኝ።
"ህክምና ለምን አልሞከርሽለትም?"
"ወይ አንተ......ለሱ ስል ምን ያልሞከርኩት ነገር አለ ብለህ ነው? ዶክተሮቹ ብሬን ሊግጡኝ
ይድናል ሲሉኝ ብዙ ገንዘብ ለማግኘት ስል ከከቤ ዲያስፖራዎች ጋር ሌዝቢያን ሸሌ ሆኜ ሰርቻለሁ::
ዶክተሮቹ ከበዙ ጊዜያት በኋላ ብሬ ማለቁን ስነግራቸው 'ሪች አትልፊ ልጅሽ የመዳን ተስፋ
የለውም' አሉኝ። ታዲያ ለምን መጀመሪያ አልነገራችሁኝም ብዬ ሆስፒታሉን አፍጋኒስታን አደረኩት ፣
ግን ሰሚ አላገኘሁም። አየህ ሀበሻ ይሄን ያህል መሰሪ ፍጡር ነው! እሱ ጥቅም እስካገኘ ድረስ
በነፍስህ ሳይቀር ቁማር ይጫወትብሀል!! እነዚህ ስግብግብ ዶክተሮች ልጄን ለገንዘብ ብለው
የሆነውንም ያልሆነውንም መርፌ እየወጉት የባሰ አጀዘቡብኝ። ያንን ጊዜ ሳስታውሰው የኢትዮጵያን
ህዝብ በሙሉ በጋዝ አርከፍክፌ እያነደድኩ በወላፈኑ ብሞቅ ደስ ይለኛል። ይሄንን ህዝብ
አልወደውም። ህይወቴን በሙሉ ነው የነጠቀኝ። ደግሞ እነዚህ ሰውን እየደለሉ ሀብታም የሆኑ
ከርሳም ዘፋኞች ሀበሻ ኩሩ ነው ደግና ሩሩሁ ሲሉ ይገርመኛል። ይሄ ህዝብ ደግ አይደለም! ደግ
ነውም ከተባለ የሚቀምሰው አጥቶ ደጃፉ ላይ ለሚያድር ምስኪኑ ወገኑ ሳይሆን ለማያውቀው
ሀብታምና ለውጭ ዜጋ ነው የሚያሽቃብጠው!!! ያኔ በጨቅላነቴ መንገድ ላይ ስለምን አዳሜ
ገንዘቡን በድራፍት ከሚጨርሰው ፣ ጮማ
ና ቁርጥ ከሚበ
3.9K views19:57
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2021-03-09 10:08:03 እየደረደርኩ ውስጤ
ያቆጠቆጠውን ሚስት የመሆን ምኞቴን ለማጥፋት እሞክራለሁ። ብቻዬን ስሆን ያዳፈንኩት ምኞቴ
እሱን ሲያገኝ በፍቅሩ ነፋስ ተቀጣጥሎ "የመጣው ይምጣ ውበትሽ ተመጦ ታኝኮ ሳያልቅ: ጡቶችሽ
ሳይሟሽሹ: ዳሌሽ ቅርፅ አልባ ከመሆኑ በፊት:ወገብሽና ሆድሽ በቦርጭ ሳይሞላ: ዕድሜ ጠላትሽ
በጠረባ ዘርጥጦ ሳይጥልሽ: ቶሎ አግቢውና ለአንድ ቀንም ቢሆን የሚስትነትን ወጉን እይው"
ይለኛል። ሌላኛው ውስጤ በመወሰንና ባለመወሰን ውቅያኖስ ላይ ነፍሴ ማረፊያ አጥታ
ትዋልላለች።
በሌላ በኩል ደግሞ 'አሟልቶ አይሰጥም ጌታ ወይ አፈጣጠር' እንድትል ሀመልማል አባተ
ኤልያስንም አምላክ ልቦናውን ንፁህ አድርጎ ቢፈጥረውም ፣ እንደኛ ከጭቃ ነውና የተሰራው ትዳር
ውስጥ እንዳልገባ የሚያደርገኝ ደካማ ጎን ነበረው " ይህንን እያለችኝ እያለ የቤቷ በር ተንኳኳ።
ከተቀመጠችበት ፍራሽ ላይ ተደነባብራ ስትነሳ ሺሻው ላይ ያለውን የከሰል ፍም ደፋችው። ሁኔታዋ
ግራ አጋባኝ። በር ስለተንኳኳ ይሄን ያህል ለምንድነው የምትደነባበረው? የሺሻ ዕቃዋን ቁምሳጥኗ
ውስጥ ከትታ ደበቀችው። የደፋችውን መዋሰልና የከሰል ፍም ጠራርጋ አነሳችው። በድጋሚ በሩ
ተንኳኳ። ቤቱ ውስጥ ኤር ፍሬሽነር ነፋች።
"ምን ሆነሽ ነው?"
"እሱ ነው" አለችኝ ድምጿን ቀነስ አድርጋ
"እሱ ማን?" አልኳት ድርጊቷ እያወዛገበኝ አፏ ውስጥ የአፍ ጠረን ማጥፊያ ስፕሬይ ነፋችና በሩን
ከፈተችው፡፡

ይቀጥላል....

╔═══❖• •❖═══╗
@silefikrr
╚═══❖• •❖═══╝
4 any comment
@silefikirbot
❥❥________⚘_______❥❥
5.8K views07:08
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2021-03-09 10:06:31 ባሌ በ50 ብር ሸጠኝ !

ክፍል 9
.
.
.
ሚሚ ቂጦ ቤት አመት ከምናምን እንደሰራሁኝ ፣ አንድ ኤልያስ የሚባል በሱስ ሰውነቱ ያለቀ ፣
እንኳን ልብሱ ቀርቶ ቆዳው የሰፋው ፣ ረዥም ፣ ቀይ ፣ ቂጡ እንደጣውላ የተጠፈጠፈ ልጅ ቤቱ
ደንበኛ መሆን ጀመረ። ያንን ቤት ከረገጠበት ቀን አንስቶ በመጣ ቁጥር ከኔ ውጪ ሌላ ሴት ጋር
አይሄድም ነበረ። ሁልጊዜም ልክ ወደ ውስጥ ሲገባ በጥናንጥ አይኖቹ እኔን ከዛ ሁሉ ከሰው ጫካ
ውስጥ ፈልጎ ይመነጥረኝና ጥግ ላይ ተቀምጦ ሜንቱን አዝዞ በሲጋራው ጭስ እየተጫወተ ፍሪ
እስክሆን ድረስ ይጠብቀኝና ለአዳር በሀይሲ ታክሲው ወደ ቤቱ ይዞኝ ይሄዳል። ቤቱን ቤት ብዬ እኔ
ልጥራት እንጂ በጣም አስቂኝ ነበረች። መሬት ላይ ከተነጠፈችው አንሶላ ከምታህለው ፍራሽ ይልቅ
እንደ ተራራ የተከመሩት የሲጋራ ቡሾች ፍራሽ ይመስላሉ። ሌላ ዕቃ ከተባለ አንድ ሽንት ሽንት
የሚሸት ሰባራ ማስታጠቢያ አለ ፣ ከዛ ውጪ እንደ ቄጤማ የጫት ገረባ በብዛት ተጎዝጉዟል። የራሱ
ታክሲ ያለው ሰውዬ ቤቱ እንዲህ ይሆናል ብሎ ማንም አይገምትም። ባለ አንድ መኝታ
ኮንዶሚኒየም ቤት ውስጥ አንድ ፍራሽ ና ማስታጠቢያ ይዞ ቤት አለኝ ብሎ ማውራት ያሳፍር
ይሆናል። እውነታው ግን ይሄ ነበር።
እቤቱ ከወሰደኝ በኋላ እንደሌሎቹ ወንዶች አያመነጫጭቀኝም። ልክ እንደ አዲስ ሙሽራ
ይንከባከበኛል። ወደ ኦና ቤቱ እንደደረስን አንድ ስቲክ ጋንጃ ይስብና ሙድ ውስጥ ሆኖ ገላዬን እንደ
ህፃን ልጅ ያጥበኛል።። ወሲብ ማድረግ መፈለጌንና አለመፈለጌን በጨዋ ቋንቋ ይጠይቀኛል።
ጥቂት ቀናቶች እየፎገረኝ ከሆነ ብዬ 'ዛሬ ማረፍ ነው የምፈልገው' ስለው እንደ እህቱ እቅፍ
አድርጎኝ ይተኛል። Sex ያደረግን ቀንም ምኔን ምኔን እንደሚነካካኝ እሱ አንድዬ ይወቅለት በዘመኔ
ሁሉ ቀምሼው የማላውቀውን እርካታ ይሰጠኛል። ወንዴ ሴት ሆነህ ስትፈጠር ትልቁ ችግር ምን
መሰለህ? ያንተን እርካታ ጠብቆ የሚረካ ወንድ አለማግኘት ነው። አብዛኛው የሀበሻ ወንድ ገጣጣ
ሆዱን አንከርፍፎ ሴቷ ላይ ከላይ ሆኖ ያለከልክና ገና እሷ መጋል ስትጀምር እሱ ቀድሞ ጨርሶ
'እንዴት ነበር?' እንኳን ብሎ ሳይጠይቃት ጀርባውን ሰጥቷት ያንኮራፋል።አቤት ይሄንን ስቃይ ሴት
ሆነህ ካልቀመስከው በወሬ ብቻ ለማስረዳት በጣም ከባድ ነው። በዚህ የተነሳ በትዳራቸው ላይ
በግልፅ የሚወያዩ ጥቂት የሀበሻ ሴቶች ብቻ ናቸው ከወሲብ ሙሉ በሙሉ እርካታን የሚያገኙት ፤
ሌሎቻችን የወንዶች ስሜታቸውን ማስታገሻ ፓራሲታሞሎቻቸው ነን።
ኤልያስ ግን የሴት ልጅ የsex ባህሪን በደንብ የተረዳ ሰው ነው። እኔ በመርካቴ ነበር እሱ
እርካታውን የሚጎናፀፈው ፤ብታየው'ኮ ቆይ እንደውም ፎቶውን ላሳይህ( የሱ ፎቶዎች ብቻ ያለበትን
አልበም ሰጠችኝ) አየኸው አይደለ? የሆነ ሲምቢሮ አንጀት የራቀው ልጅ'ኮ ነው። ግን እዛ ነገር ላይ
ምንም ብቀጥን ጠጅ ነኝ እንደሚሉት ዓይነት ሰው ነው። ደግሞ'ኮ በጣም የሚገርመኝ ነገር
ማንኛዋንም ሴት ማርካት ይቻል ይሆናል ፣ ግን በቀን ከአስሩ ወንድ ጋር የምጋደመውን እኔን
ሸሌዋን ማርካት ከባድ ነው ፤ ምክንያቱም ወንድ ልጅ ማለት ለኔ በብልቱ የሚያስብ ዋሌት ብቻ
ነው። እኔ ብሩን እንጂ ሌላ ነገሩን ፈልጌ አላውቅም። እሱ ግን አሸነፈኝ። ይቺን ዓለም እዛ አትክልት
ተራ ገንዳ ስር ተጥዬ ከተቀላቀልኩበት ዕለት አንስቶ ማንም ሰጥቶኝ የማያውቀውን እውነተኛ ፍቅር
ሰጠኝ።
እንደምታየኝ ከሆነ ቆንጆ አይደለሁም። ፉንጋ ከመባል ለጥቂት የተረፈ መልክ ነው ያለኝ ፣ ትንሽ
ሰውነቴ ሞላ ያለ ስለሆነና በጭፈራ ቤት መብራት ሁሏም ሴት ቆንጆ ስለሆነች ያኔ አምሬው ይሆን?
ብዬ ቀን ቀን የሚይዘው ታክሲ ውስጥ ጋቢና አብሬው ተቀምጬ መዋል ጀመርኩ። እሱ
እንደጠበኩት አመሉ እንደቂጣ ሊገለባበጥ አልቻለም። አንዴ ታዲያ እሱ ቤት እየቃምን ለምን
እንዲህ እንደሚንሰፈሰፍልኝ ጠየኩት ያው የሀበሻ ወንዶች ስትባሉ ስትጠጡና ስትቅሙ ፈላስፋ
ፈላስፋ ያጫውታችሁ የለ? እንዲህ አለኝ፡፡ "ሰውን ለመጥላት እንጂ ለመውደድ ምን ምክንያት
ያስፈልገዋል? ክርስቶስ ዓለምን እንዲህ እንደወደድኳት እርስ በርሳችሁ ተዋደዱ አይደል ያለው?
ስለዚህ አንቺን ለመውደዴ የምደረድረው ምንም ዓይነት ምክንያት የለኝም! እንዲሁ እወድሻለሁ!!
እንዲሁ አፈቅርሻለሁ!!! እንዲሁ የግሌ ጣኦት አድርጌሽ አመልክሻለሁ!!!! ምን መሰለሽ ሪችዬ እኔ
ሴት ብርቄ አይደለም ኢትዮጵያ ውስጥ የታክሲ ሹፌርና የቪዲዮ ቤት ባለቤት መሆን ትርፍሽ
የሚሆነው እውነቱን ንገረኝ ካልሽኝ እ*ስ ብቻ ነው። በዚህ የተነሳ ብዙ ሴቶችን አውጥቼያለሁ።
እነርሱ ግን በልቤ ውስጥ ያንቺን የሩብ ሩብ ቦታ ያህል አላገኙም። ሁሉም የስሜቴን ውጥረት
ማስተንፈሻ ተራ ቀዳዳዎች ብቻ ናቸው። አንቺ ግን ከነዛ ትለይብኛለሽ። በምን ብለሽ ብትጠይቂኝ
መልስ ላልሰጥሽ እችል ይሆናል ፣ ግን በቃ ለኔ አንደኛዬ ነሽ" አለኝ። ከልምዴ በመነሳት የወንዶችን
ስሜት መረዳት አይከብደኝም። ወንድን ልጅ ዓይኖቹን ሳላይ ማጅራቱን ብቻ ተመልክቼ
እንደሚፎግረኝና እንደማይፎግረኝ በቀላሉ መለየት እችላለሁ። ኤልያስ ከልቡ እንዳለኝ የነፍሴ ጆሮ
ሰምቶ አረጋግጦልኛል፡፡
እንዲህ እንዲያ እያልን ተላመድን ፣ በደንብ ተዋወቅን ፣ በፍቅር ወደ ላይ ፀባኦት ድረስ ከነፍን
ወደታችም እንጦሮጦስ ድረስ ዘልቀን በሲኦል የነበልባል ባህር ውስጥ ምስክር ሳያሻን እርስ
በርሳችን ተጠማምቀን ፣ ከሰይጣን የፊት ጥርስ የተሰራ ቀለበት አጥልቆልኝ ፣ እኔም አጥልቄለት
የቃልኪዳናችንን ሰማንያ በዲያቢሎስ ጭራ ማህተም አስመትተን አንድ አካል አንድ አምሳል ሆንን!
እሱ ጨርቁን ጥሎ ሊያብድልኝ ደረሰ ፣ እኔም ዓለም ሁሉ ከእሱ ውጪ እስኪያስጠላኝ ድረስ ልቡ
ላይ እንደተባይ ተጣበኩበት። የሱን ሀይሲ ታክሲ ቀን ቀን መፈረሺያ ማታ ማታ ቤርጎአችን
አደረግናት። እኔም አንገት ማስገቢያ ላመል ያህል አንድ ሁለት ሾርት ከሰራሁኝ ጉያው ስር
ለመሸጎጥ ፣ ጎረምሳ ጎረምሳ የሚል ለኔ ግን ከከርቤ በላይ ለአፍንጫዬ መልካም መዓዛ
የሚሆንልኝ ጠረኑን ለመታጠን ፣ ሌላ ቦታ ሰምቼያቸው ፈገግ እንኳን ያላስባሉኝን ቀልዶች እሱ
ሲያወራ ስሰማው ግን ጥርሶቼ እስኪረግፉ ድረስ ለመሳቅ ፣ ስንቱን ወንድ በብልጠቴ ገመድ ጠልፌ
የጣልኩት ሴትዮ ከርሱ ጋር ለመጃጃል ፣ ለመላፋት በክብር ለመሳም ወዳለበት ቦታ እየበረርኩ
እሄዳለሁ። ርግጠኛ ነኝ አስፋልት ላይ እንዲያ ስከንፍ ትራፊክ ቢያየኝ ቤልት አላሰርሽም ብሎ
ይቀጣኝ ነበር፡፡
ማታ ማታ በጋንጃ ጦዞ ሚሚ ቂጦ ቦት የኔ ሲምብሮ ሲመጣ ፣ እኔ ከማንም ሆዱም ማሰቢያውም
በአምቡላ ከተሞላ ለፍዳዳ ሰካራም ጋር ለገንዘብ ብዬ ሴትነቴን ሳራክስ እሱ ጥግ ላይ ተቀምጦ
በሲጋራው ጭስ እየተጫወተ ቅናቱን ውስጡ ቀብሮ ሜንት እየጠጣ ሲመለከተኝ ሳይ ሆዴ
ይንቦጫቦጭብኛል። ስፍስፍ እልለታለሁ። አፍቃሪው አንጀቴ ሌላ ወንድ እቅፍ ውስጥ ለመግባት
አቅሙ ይከዳዋል። እርሱን የሚሰማው የቅናት ቁስል አጥንቴ ድረስ ዘልቆ ይሰማኛል። ሲብስብኝ
'ሌላ ቦታ ጠጣ እዚህ አትምጣ' አልኩት።
"ሁለታችንም እንዲህ ከምንሰቃይ ለምን አታገቢኝም?" አለኝ።
ለዚህ ጥያቄው መልስ ለመስጠት ምላሴ አቅሙ ያጥረዋል። ብዙ የማውቃቸው ሸሌውች
አግብተው የተፈራረሙበት የስኪብርቶ ቀለም ሳይደርቅ ሲፋቱ ስላየሁ ትዳርን እፈራለሁ። ሙሉ
በሙሉ በቁጥጥሩ ስር ሲያደርገኝ አመሉ ቢቀየርስ? እያልኩ እሰጋለሁ። እንዲህ እንደጣኦቱ
የሚያመልከኝ ልክ እንደ ታክሲው ሁሉ የራሱ ንብረት ስላላደረገኝ ቢሆንስ? ራሔልን የግሌ
አደርጋታለሁ ብሎ ከራሱ ጋር እልህ ተያይዞ ቢሆንስ? እያልኩኝ

ሌሎች 'ቢሆንስ'
5.3K views07:06
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2021-01-09 21:21:19 ባሌ በ50 ብር ሸጠኝ !

ክፍል 8
.
.
.
የተኛሁበት ብርድልብስ ሲገለጥ ብንን ስል የጠፋው መብራት በርቶ ራሔል መጠጡ አፏ ውስጥ
የተጠመቀ ይመስል ጋን ጋን እያለች ወንፊት የሆነ ፒጃማ ለብሳ ፊት ለፊቴ ቆማለች። ዓይኖቿ
ደፈራርሰው ከእኔ የፈለጉትን ነገር ለመቀበል አፍረው እየተለማመጡኝ ሲቁለጨለጩ አየኋቸው።
ጡት ማስያዢያ ስላላደረገች ውበቷ ሊረግፍ አንድ ሐሙስ እንደቀረው የሚያሳብቁት ዘልዛላ ጡቶቿ
ፊቴ ላይ አፈጠጡብኝ። አውቃ ይሁን ሳታውቅ( የማውቀው ነገር የለም)ፒጃማዋ ላይ ውሀ ወይም
መጠጥ ስለደፋችበት ደረቷና ዳሌዋ ላይ ተለጥፎ ሳየው ወንድነቴ ይፈታተነኝ ጀመር። የተፈጠረብኝን
ስሜት ለመሸፋፈን እየሞከርኩ (ኡኡቴ አልቀረብኝም እንኳን የኔን ቀርቶ የስንቱን ወንድ ስሜት
በአንድ እይታ ብቻ ስታነብ ከከረመችው ሴት ስሜቴን ለመደበቅ መሞከሬ ለራሴም ሳይቀር አሳቀኝ)
"ሪችዬ ችግር አለ እንዴ?"
ዝም አለች ከታገደምኩበት ተነስቼ አጠገቤ ቁጭ አደረኳት።
"ምን ሆነሻል ለምን አትናገሪም?"
"ልጄ?!"
"ልጅሽ ምን ሆነ?"
"ምንም አልሆነም እስከዛሬ ድረስ ሙሉ ሴት መሆኔ የሚሰማኝ በገንዘቡ እንደ ሸቀጥ ገዝቶኝ
ከሚጋልበኝ ሰው ጋር ሳድር ሳይሆን ከንፁህ ልጄ ጋር ሳድር ነው። ታዲያ አሁን አንተ እንደምትመጣ
ስትነግረኝ እየጮኸና እየተሯሯጠ እንዳይረብሸን
ብዬ ሞግዚቱ ጋር ስላሳደርኩት ብቻዬን መተኛት ፈራሁ"
" እና "
"እናማ ቅር የማትሰኝ ከሆነ አብሬህ ልተኛ" አለችኝ።
"አአአኧኧኧ ኧረ ችግር የለውም" በቅንዝረኛ ዓይኖቼ እያየኋት ስለሆነ አፌ ተያያዘብኝ። እርሷ ደገፍ
ብላኝ በእህትነት ስሜት አንገቴ ስር ሽጉጥ ስትል እንደ ዋሽንት ዜማ ያለው ትንፋሿ ማሰቢያዬን
ፐወዘብኝ ፣ እንኳን ነክተውት አይደለም ጮክ ብለው ሲያዩት እንኳን የሚቀደድ የሚመስለው ለስላሳ
ገላዋ ገላዬን ሲነካኝ ሰውነቴ መጋል ጀመረ።
የሴት ልጅ ጠላቷ የሆነው ዕድሜ እያሟሸሻቸው ያለውን ከንፈሮቿን ልስማት አንገቷን አቅፌ ቀና
ሳደርጋት ፣ ዓይኖቿ በቅንዝረኝነት ስሜት ሳይሆን በእንቅልፍ ተዳክመው ገርበብ ብለው ተከፍተው
አዩኝ። ጥቁሩ ብሌኗ ውስጥ ለኔ ያላትን ንፁህ የወንድምነት ስሜት አነበብኩኝ። ቀስ ብዬ ስሜቴን
ለማኮማሸሽ ሞከርኩ። እላዬ ላይ እንደለስላሳ ሀረግ ተጠምጥማብኝ ተኛች።
ጠዋት እነፊት መታጠብን እነ ቁርስ መብላትን ምናምን ምናምን ካደረግን በኋላ ሺሻዋን
እያንደቀደቀች ወደ ቀድሞ ጨዋታችን ተመለስን።(አሁን ብፅፋቸው ከአደግንበት ባህል ጋር
የሚጣረዙ ፣ መረን የሆኑ የራቁት ቤት ሚስጥሮችን ነግራኛለች። ወዴት እየሄድን እንዳሉ
የሚጠቁሙ ሚስጥራዊ ክሽፈቶቻችንን አጫውታኛለች። ለምሳሌ ስለ ሴት ለሴት ወሲብ/
Lesbians ፣ ጋጠ-ወጥ ባህሪ ስላላቸው ታዋቂ ሰዎቻችን ፣ ስለ ሸሌዎችና ስለ ጠንቋዮቻቸው ፣
18 ዓመት ሳይሞላቸው በዝግ ቤት ስለሚጠጡት የባለስልጣኖቻችን ልጆች ብቻ ብዙ
አውርታኛለች።)
ወንዴ ያ ራቁት ጭፈራ ቤት ሲዘጋ ደዘደዟ ያጠራቀምኩትን ወደ መቶ ሀያ ሺ ብር የሚጠጋ ገንዘቤን
ሰጠችኝ። እሱን ብር ይዤ ከዚህ ከገሃነም ህይወት መውጣት ስችል የሚያልቅ አልመስል ብሎኝ
ስመነዝር ስመነዝር በስድስት ወራት ውስጥ ዶግ አመድ አደረኩት። እንደገና ዲካርት ገባሁ።
የአመታት ልፋቴን ሁሉ በዜሮ አባዛሁት። ሳይታሰብ ከሚመጣ ሀብት ይልቅ አብሮ የኖረ ድህነት
የሚሻል መሆኑን ያኔ ኖሬበት ተረዳሁ። ከዛልህ የስራ ቦታዬን ወደ ቺቺኒያ ቀየርኩ። ወንዴ ‘’ ሚሚ
ቂጦን ቤት ታውቀዋለህ አይደል?" አለችኝ። (እንደዛሬ በቺቺኒያ ምድር club H2O ከመንገሱ በፊት
የቺቺኒያ አድባር የሚሚ ቂጦ ቤት ነበር። ይሄ ቤት ዝናው ከሀገር አልፎ አውሮፓና አሜሪካ ድረስ
ስለሚወራለት አብዛኛው ዲያስፖራ ወደ ሀገር ቤት ሲመጣ ሳይጎበኘው አይሄድም። በዚህ ቤት
ውስጥ ብዙ የከተማችን ባለሀብቶች ካዝናቸውን አራቁተው በሸሌዎች ድግምት ተተብትበው
አብደውና የነሱን ፓንት አጣቢ የቀሩ ሰዎችን አውቃለሁ። ለነገሩ ሙሉ የቺቺኒያ ምድርን
የሚያሽከረክሯት በሸሌዎቹ የሚገበርላቸው የዛርና የአውሊያ መናፍስቶች እነ አዳል ጠቋር ፣
የአርሲዋ እመቤት ፣ የደብረዘይቱ ቆሪጥ ፣ እነ ወሰን ገላ ፣ የወለጋው ሞቴ እነ እውሪት
ብርሀኔ......እና ሌሎች መሆናቸውን የአንድ ሰሞን የቺቺኒያ ተሳላሚ ስለነበርኩ በደንብ
አውቀዋለሁ። አብዛኞቹ ጠባብ ፐቦች ውስጥ ወንድ እንዲስብላችሁ እየተባሉ በጠንቋዯቻቸው
የሚሰጣቸው እጣን ይነዳል ፣ ከ1:00-3:00 ባለው ጊዜ ውስጥ እየተቃመ ይዘየራል ፣ ጥቂት
የማይባሉት ቤቶች ውስጥ ጥጃ ከነነፍሱ ተቀብሯል ፣ ደጃፋቸው ላይ ደንበኛቸው ከቤቱ
እንዳይላቀቅ ድፍን እንቁላል ይቀብራሉ ፣ የጥቁር ፍየልና የጥቁር ዶሮ ደም ያፈሳሉ። ስለዚህ ጉዳይ
ሌላ ቀን በሰፊው እንጨዋወታለን።)
"እንዴታ ሪች! ድድ ማስጫ ተወልጄ ሚሚ ቂጦ ቤት ሰክሬ ካልተለፋደድኩኝ ምኑን ወጣትነቴን
ቀጨሁት" አልኳት። እዛ ገሀነም ጭፈራ ቤት ውስጥ ያባከንኳቸውን ጊዜያቶች እያስታወስኩ።
( ከሹገር ማሚዋ ጋር ነው አይደል ቺቺንያ ስትጨፍር የከረምከው? ስትሉ ሰማኋችሁ ልበል!?)
"ወንዴ መቼም ቺቺንያ እንዲህ እንደዛሬው እንደሰካራም ፊት ቡድስድስ ከማለቷ በፊት የሀጢያት
ዘውዷን ከአሮጊቷ ካዛንችስ ከተረከበች በኋላ ብዙ ተአምር ተሰርቶባታል። ብዙ ባለሀብቶችን
አደህይታለች ፣ እልፍ ደሀዎችን ደግሞ ሀብታም አድርጋለች ፣ በመቶ ሺዎች የሚቆጠሩ ሴቶችን
ቅርጥፍጥፍ አድርጋ በልታለች ፣ ብዙዎቻችንን ከሲጋራ እስከ ኮኬን ድረስ ከትባናለች ይሄንንም
የታዘቡ እንዳንተ ዓይነት ቸክቻኪዎች የፈጠራ ታሪካቸውንና እውነታውን አደበላልቀው ብዙ ገድሎቿን
በመፅሃፍ አሳትመው ሀብታም ሆነውባታል። ስለ ሸሌ የተፃፉ መፅሐፍት በሙሉ የብዕራቸው አሞራ
የሚያንዣብበው በዚች ቅዱስ ሚካኤል የጣለው ሳጥናኤል በታሰረባት በተአምረኛዋ ቺቺኒያ በኩል
ነው። እኔ እንኳን ያነበብኳቸው መሀልየ መሀልየ ዘ ቺቺኒያ ፣ የቺቺኒያ ሚስጥራዊ ለሊቶች ፣ ሰአት
እላፊ ላይ ያሉ ታሪኮች ፣ ሮዛ ብቻ ሌሎችም የማላስታውሳቸው ብዙ ተሞንጭረዋል። እናልህ እዚህ
ሚሚ ቂጦ ቤት ገቢዬ እንደደዘደዟ ቤት ባይሆንም እሱ የከፈተውን እ*** እሱ ሳይዘጋው አያድርም
ነበር። እንግዲህ እዚህ ቤት ነው በሀምሳ ብር የሸጠኝን ባሌን የተዋወኩት
"እንዴት?" አልኳት ለወሬ የቋመጡ ጆሮዎቼን ቀጥ አድርጌ
"ሚሚ ቂጦ ቤት አመት ከምናምን እንደሰራሁ

ይቀጥላል..

╔═══❖• •❖═══╗
@silefikrr
╚═══❖• •❖═══╝
4 any comment
@silefikirbot
❥❥________⚘_______❥❥
6.5K views18:21
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2020-11-21 10:09:35 "አዎ" አልኳት።
"መቼም በዚህ ሰዓት ወደቤትህ አትሄድም እዚው ታድራታለህ እንጂ" አለችኝ በምርቃና በፈጠጡ
አይኖቿ እያየችኝ በሀሳቧ ተስማምቼ ሶፋው ላይ ብርድልብስ አምጥታልኝ ተኛሁ።
እሷም የሳሎኑን መብራት አጥፍታ ወደ መኝታ ቤቷ ሄደች። ‘’ልጇ እስከዚህ ሰዓት ድረስ የት ሄዶ
ነው?’’ ብዬ እያሰብኩ እንቅልፍ ሊወስደኝ አልቻለም። ካለችበት መኝታ ቤት ውስጥ የብርጭቆና
የጠርሙስ ድምፅ ይሰማኛል ምርቃናዋን ለመስበር እየጠጣች ይሆናል ብዬ አሰብኩ ሳላውቀው
እንቅልፍ ወሰደኝ። የተኛሁበት ብርድልብስ ሲገለጥ ብንን ስል የጠፋው መብራት በርቶ

ይቀጥላል...

╔═══❖• •❖═══╗
@silefikrr
╚═══❖• •❖═══╝
4 any comment
@silefikirbot
❥❥________⚘_______❥❥
7.9K views07:09
ክፈት / አስተያየት ይስጡ