ማስተካከያ ዛሬ ማለዳ ሳፋሪኮም ኢትዮጵያ "20ሺህ ሰራተኞችን ሊቀጥር ነዉ"በሚል የሚል መረጃ አድርሰ ነበር። ምንም እንኳን መረጃውን ጠዋት ዋዜማ ራዲዮ ከሰራው ዘገባ የወሰድን ቢሆንም የሳፋሪኮም ኢትዮጵያ የኮሚኒኬሽን ሀላፊ ወ/ሮ ተወዳጅ እሸቱ መረጃው የሀሰት እንደሆነ ለብስራት ራዲዮ ከሰጡት ቃለመጠይቅ መረዳት ችለናል። በኩባንያዉ ስም ከተከፈቱ ሀሰተኛ የማህበራዊ ሚዲያዎች አማካኝነት የተሰራጨ መሆኑን ጨምረዉ ተናግረዋል። ሰሌዳም ለተፈጠረው የተሳሳተ የመረጃ ስርጭት ይቅርታ ትጠይቃለች 4.0K views08:59