በቀጣይ ዓመት ሁሉም ዩኒቨርስቲዎች ወደ ኤሌክትሮኒክስ የግዢ ስርዓት እንደሚገቡ ተነገረ በፀጥታ ችግር ሳቢያ ከመደበኛ አገልግሎታቸው ተስተጓጉለው ከነበሩ ዩኒቨርስቲዎች ውጪ ያሉት ዩኒቨርስቲዎች ወደ ኤሌክትሮኒክስ የግዢ ስርዓት እንዲገቡ እንደሚደረግ የመንግስት ግዢና ንብረት ባለስልጣን አስታውቋል። እስካሁን 44 ከሚሆኑ ከፍተኛ የትምህርት ተቋማት ውስጥ የኤሌክትሮኒክስ የግዢ ስርዓትን ተግባራዊ ያደረጉት የአዲስ አበባ ዩኒቨርስቲ እና የአዲስ አበባ ሳይንስና ቴክኖሎጂ ዩኒቨርስቲ ብቻ መሆናቸውንም ባለስልጣኑ ለኢትዮ ኤፍ ኤም ገልፀዋል፡፡ 4.4K views07:51