ለሶስተኛው የቴሌኮም አገልግሎት ሰጭ ተቋም ፈቃድ ለመስጠት ጨረታ ሊወጣ ነው ተባለ። በኢትዮጵያ ለሶስተኛው የቴሌኮም አገልግሎት ሰጭ ተቋም ፈቃድ ለመስጠት በሰኔ 2015 ዓ.ም ጨረታ ሊወጣ መሆኑን የኢትዮጵያ ኮሙኒኬሽን ባለስልጣን አስታውቋል። ከዚህ ቀደም ለሁለት አዳዲስ የቴሌኮም ተቋማት ፈቃድ ለመስጠት ቀደም ሲል ጨረታ ወጥቶ ሳፋሪኮም ኩባንያ በ2013 ዓ.ም የመጀመሪያውን ፈቃድ መውሰዱን የጠቀሰው ባለስልጣኑ በጨረታው ላይ ተሳትፎ የነበረው ኤምቲኤን ግሩፕ በወቅቱ አቅርቦት የነበረው ገንዘብ ከሳፋሪኮም አንጻር ልዩነቱ በመስፋቱ የሁለተኛው ፈቃድ ሳይሰጥ መቅረቱንም አስታውሷል። 6.6K views12:22