የመንግሥት ሠራተኞች ደመወዝን በቴሌ ብር እንዲከፈል መታቀዱ ተገለጸ በባንኮች በኩል ተከፋይ የሚሆነውን የመንግሥት ሠራተኞች ደመወዝ ወደ ቴሌ ብር የሞባይል ገንዘብ ሥርዓት ለማሸጋገር ዝግጅት እየተደረገ መሆኑን የገንዘብ ሚኒስትሩ አቶ አህመድ ሽዴ የተቋማቸውን የዘጠኝ ወራት የሥራ አፈጻጸም ለፓርላማ ባቀረቡበት ወቀት ተናግረዋል፡፡ ኢትዮ ቴሌኮም የመንግሥት የኤክትሮኒክስ ክፍያ ድርሻ ለመወጣት እንዲያስችለው የሪፎርም ሥራዎችን እየሠራ እንደሆነና ለአብነትም የታክስ ክፍያ አሰባሰብ ሥርዓቱ በቴሌ ብር እንዲከፈል የሚያስችል ሥርዓት መዘርጋቱን አቶ አህመድ እንደጠቆመው ሪፖርተር ፅፏል፡፡ 6.6K views11:24