Get Mystery Box with random crypto!

በፕርሜር ሊጉ ለኮከብ ጎል አግቢነት የሚፎካከረው አጥቂ ቤቲንግ በመጫወቱ ለስምንት ወራት ከስፖርት | ሰሌዳ | Seleda

በፕርሜር ሊጉ ለኮከብ ጎል አግቢነት የሚፎካከረው አጥቂ ቤቲንግ በመጫወቱ ለስምንት ወራት ከስፖርት ታገደ

እንግሊዛዊዉ የብሬንትፎርዱ አጥቂ ኢቫን ቶኒ የኤፌውን ህግ በመተላለፍ በእግር ኳስ ጨዋታ ውርርድ በማድረጉ (ቤቲንግ በመጫወቱ) ለስምንት ወራት ከምንም አይነት የእግር ኳስ ውድድር እንዲገለል እና 50ሺ ዩሮ እንዲቀጣ ተወስኖበታል።

ወጣቱ ተስፈኛ በዘንድሮ የውድድር ዓመት ድንቅ አቋማቸውን ካሳዩ ጥቂት የሊጉ አጥቂዎች አንዱ ሲሆን በ20 የፕርሚዬር ሊግ ጎሎች ከሀላንድ እና ሀሪ ኬን በመቀጠል ሶስተኛው የሊጉ ኮከብ ግብ አግቢም ነበር።

የበርካታ አምራች ወጣቶችን አእምሮ በበረዘው የቤቲንግ ውድድር ሱስ ምክንያት ከዚህ ቀደም በሃገራችንም የኢትዮጵያ ቡና ተጫዋች ናትናኤል በርሄን የራሱ ክለብ ይሸነፋል ብሎ መጫወቱን ተከትሎ ከክለቡ መባረሩ አይዘነጋም።