ዜጎችና ተወላጆች በሃዋላ ከውጪ በሚልኩት ገንዘብ ላይ የሚጠየቀው የአገልግሎት ክፍያ እንዲቀነስ ተጠየቀ የኢጋድ አባል ሀገሮች የብሄራዊ ብንኮች ገዢዎች በኬንያ ናይሮቢ በነበራቸው ስብሰባ ላይ በቀረበ ጥናት በአባል ሃገራቱ ላይ የሚጠየቀው ያገልግሎት ክፍያ ከአለማቀፉ አማካኝ ክፍያ በእጅጉ የበለጠ ነው መባሉን ቢዝነስ ዴሊ ጽፏል። ለኢጋድ አባል ሀገሮች የሚጠየቀው ክፍያ በአማካኝ 8.9 በመቶ ሲሆን በአለም አቀፍ ደረጃ ደግሞ አማካኙ 6.5 በመቶ እንደሆነ ተመላክቷል። ኢጋድም ይህ ያገልግሎት ክፍያ እንዲቀነስ ጠይቋል። 5.3K views11:23