የአዲስ አበባ ከተማ መስሪያ ቤቶች አገልግሎት የሚሰጡበትን ጊዜ፤ ወደ 16 ሰዓት ለማራዘም የሚያስችል ጥናት እየተደረገ ነው ተባለ። ጥናቱ የመስሪያ ቤቶቹን የስራ ሰዓት ከጠዋቱ 2፡30 አስቀድሞ ለማስጀመር እና ከ11፡30 በኋላ እስከ ምሽት ለማስቀጠል ያቀደ ነው መባሉን ኢትዮጵያን ኢንሳይደር ዘግቧል። ይህም “በአንዳንድ ተቋማት ላይ ከሰዓት ጋር ተይይዞ ተገልጋዮች ተገፍተው የሚወጡበትን” ሁኔታ ለማስቀረት ያለመ ነው ተብሏል። 5.9K views11:03