Get Mystery Box with random crypto!

7 ቁጥር

የቴሌግራም ቻናል አርማ sebat_kutr — 7 ቁጥር 7
የቴሌግራም ቻናል አርማ sebat_kutr — 7 ቁጥር
የሰርጥ አድራሻ: @sebat_kutr
ምድቦች: ያልተመደበ
ቋንቋ: አማርኛ
ተመዝጋቢዎች: 1.98K
የሰርጥ መግለጫ

፯ ቁጥር ሰው የመሆን ሚስጥር መፍቻ
✔በመፅሀፍ ቅዱስ ውስጥ 7 ቁጥር 735 ጊዜ የተጠቀሰ ሲሆን በዚህም ቻናል ጠቅለል ተደርጎ የሚዳሰስ እንዲሁም ኢትዮጵያና ሰባት ቁጥርን ከቀደምት አባቶቻችን እውቀት በመጨለፍ ምን እንደሚያገናኛቸው በስፋት የሚዳሰስበት በተጨማሪም ስለ አውሬው ቁጥር፣ስለ መናፍስቶች ድብቅ ሴራ የሚቀርብበት ቻናል በመሆኑ ይህን ቻናል በመቀላቀል በቂ ግንዛቤን ይያዙ !

Ratings & Reviews

2.33

3 reviews

Reviews can be left only by registered users. All reviews are moderated by admins.

5 stars

0

4 stars

1

3 stars

0

2 stars

1

1 stars

1


የቅርብ ጊዜ መልዕክቶች 2

2022-03-28 08:24:33 ​​​​"ጾምን አጋመስነው አትበሉ"

ገብረ እግዚአብሔር ኪደ
ብዙ ሰዎች ደስ ተሰኝተውና እርስ በእርሳቸው፡- ግማሹን ጾም ፈጽመናል፤ የጾሙ እኩሌታ አለፈ ሲባባሉ ተመልክቻለሁ፡፡

እኔ ግን እነዚህ ሰዎች በዚሁ ምክንያት ደስ ሊላቸው እንደማይገባ እመክራቸዋለሁ፤ የጾሙ እኩሌታ ማለፉን ሳይኾን የኃጢአታቸው እኩሌታ መኼዱን መወገዱን ያስቡ፤ እንደዚያ ከኾነም ሐሴት ያድርጉ፡፡

ደስ ልንሰኝበት የተገባው ነገር ይኼ ነውና፡፡ ሊታይ የሚገባው ይኼ ነው፤ ጥንቱም እነዚህን ኹሉ ነገሮች የምናከናውናቸው ስሕተቶቻችንን እንድናስተካክል፣ ጾሙ ሲጀምር እንደ ነበርንበት ሳይኾን እንድንነጻበት፣ ክፉ ልማዶቻችንን ወደ ጎን አድርገን የተቀደሰውን በዓል በዓለ ትንሣኤን እንድናከብር ነውና፡፡

እንደዚህ ካልኾነ ግን ጾሙን መጨረሳችን በራሱ ለእኛ ታላቅ ጉዳትን ይዞ ከመምጣት ውጪ ሌላ ምንም ረብ ጥቅም አይሰጠንም፡፡

ስለዚህ ብዙ ጊዜ መጾማችንን ብቻ አንመልከት፤ ይህ ምንም ትልቅ ነገር አይደለምና፤ ይልቁንስ በዚህ ጾም ራሳችንን አሻሽለን እንደ ኾነ፣ ጾሙ ከተፈታ በኋላም የዚሁ ፍሬ ጎምርቶ ይታይብን እንደ ኾነ ሐሴት እናድርግ፡፡

የክረምት ጥቅሙ ይበልጥ የሚታወቀው ወራቱ ካለፈ በኋላ ነውና፡፡

የዚያን ጊዜ የአበባው ማበብ፣ የአዝመራው ማፍራት፣ ሌሎች ዕፅዋትም በቅጠላቸውና በፍሬያቸው በወርሐ ክረምት ያገኙትን ጥቅም ግልጽ አድርገው ይናገራሉና! በእኛም ዘንድ ልክ እንደዚህ ይኹን፡፡

በወርሐ ክረምቱ በብዛትም በዓይነትም የተለያየ ዓይነት የዝናብ ጠብታዎችን ተቀብለናል፤ ብዙ ተከታታይ ትምህርቶችን ተምረናል፤ መንፈሳዊ አዝርእት ተዘርተዉብናል፤ የቅምጥልነት እሾኽም ቈርጠን ጥለናል፡፡

ስለዚህ ጾሙ በተፈታ ጊዜ የጾሙ ፍሬ ይከብበን ዘንድ፣ ከጾሙ የሰበሰብናቸውን መልካም ነገሮችም ጾሙን ራሱን እናስታውሰው ዘንድ የሰማነውን ነገር አጽንተን በመያዝ እንትጋ።

በእንተ ሐውልታት፣ ፲፰፥፩-፪
2.0K viewsNatnael, 05:24
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-03-13 11:38:09
#ሰው_እንደ_ዘር_ነው!!

አባቶቻችን ሊቃውንት ሰው እንደ ዘር ነው ይላሉ። ሰው እንደ ዘር ነው ማለት ዘር ተዘርቶ የሚያድገው በሁለት መሠረታዊ ነገር ነው። በብርድ እና በጸሐይ። ዘር ዝናምና ጸሐይ ያስፈልገዋል። ዝናም ብቻ ከሆነ ሽባ ይሆናል ጸሐይ ብቻም ከሆነ ይደርቃል።

ሰውም እንደ ዝናሙ የእግዚአብሔር ቸርነት ያስፈልገዋል፤ እንደ ጸሐዩም መከራ ያስፈልገዋል። ዘር በዝናሙ እየለዘበ፣ በጸሐዩ እየበሰለ እንደሚያድገው ሁሉ ሰውም በመከራ እየጠነከረ በተስፋና በእግዚአብሔር ቸርነት እየተጽናና ያድጋል።

ሁልጊዜ የእግዚአብሔርን ቸርነት ብቻ ከሆነ የሚያስበው ሽባ ይሆናል። መከራ ባገኘው ጊዜ ወዲያው ተስፋ ይቆርጣል። ሃይማኖትን ሊክድ ይችላል። መከራ ብቻ ከሆነበት ደግሞ ወዲያው ደግሞ እንደዚሁ ተስፋ ቆርጦ ሊሠበር ይችላል።

ስለዚህ ዘር ዝናምና ጸሐይ እንደሚያስፈልገው ሁሉ ሰውም መከራና የእግዚአብሔር ቸርነት ያስፈልገዋል።

#አባ_ገብረ_ኪዳን (የብሉያት እና የሐዲሳት መምህር)
2.0K viewsNatnael፲፪, 08:38
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-03-05 15:20:47 #አብረን_ዝም_እንበል!!

አባ በምዋ ዓለምን ትቶ ወደ በረሃ በሄደ ጊዜ፣ ለዚህ አዲስ ሕይወቱ የሚጠቅመውን ምክር ይሰጡት ዘንድ ወደ አንድ ቅዱስ አረጋዊ ቀርቦ ምን ላድርግ? ሲል ጠየቃቸው፦ እኒህም አረጋዊ ንግግራቸውን የጀመሩት "በአንደበቴ እንዳልስት መንገዴን እጠብቃለሁ" በሚለው በቅዱስ ዳዊት የመዝሙር ቃል ነበር። መዝሙር 39፥1 አባ በምዋም ይህንን የመጽሐፍ ቃል በሰማ ጊዜ "ይበቃል አባቴ፣ ይህን ተምሬ እስክፈጽም ድረስ ሌላ ምንም አዲስ ትምህርት አይንገሩኝ!" በማለት ወደ በዓቱ ሄደ። ከዚያም ቀን ጀምሮ ለብዙ ጊዜያት ወደ አረጋዊው አልተመለሰም ነበር።

ከዕለታት በአንዱ ቀን አረጋዊው ጻድቅ አባ በምዋን አግኝተው ለምን ለሌላ ተጨማሪ ትምህርት መልሶ ወደ እርሳቸው እንዳልመጣ ጠየቁት። እርሱም "እመኑኝ አባቴ፣ ገና የመጀመሪያውን ትምህርት በሚገባ አልተማርኹትም" ሲል መለሰላቸው። ከረጅም ዓመታትም በኋላ ወዳጁ የሆነ አንድ መነኩሴ የሰማውን የነቢዩ የዳዊትን ቃል እስከ አሁን አጥንቶ ጨርሶ እንደሆነ አባ በምዋን ጠየቀው። ቅዱሱም "በዚህ የነቢዩ ቃል ላይ ለማሰላሰል እና በሚገባ ወደ ተግባር ለመቀየር አርባ አምስት ዓመታት ወስዶብኛል" ሲል በትሕትና መለሰለት።

የአባ በምዋን ታሪክ የጻፈልን ቅዱስ ጰላድዮስ እንደሚናገረው አባ በምዋ በሕይወቱ ሁሉ ፍጽምት የሆነች የዝምታን ሕይወት የመራ ሲሆን፣ በሞቱም ጊዜ "ምነው ይህን ባልተናገርኩ" የሚል አንድም የሕሊና ወቀሳ ሳያገኘው በሰላም አርፏል።

ቅዱስ እንጦንስም በአንድ ወቅት ደቀ መዛሙርቱን እንዲህ ሲል መክሯቸው ነበር፦ "ዝም በሉ፤ ዝምተኛን ሰው እግዚአብሔር በፊቱ ካሉት ሠራዊተ መላእክት እንደ አንዱ ይቆጠረዋልና!"

#ዲያቆን_አቤል_ካሳሁን
2.0K viewsNatnael, 12:20
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-03-02 12:04:51
ውድ የ7 ቁጥር ቤተሰቦች እንኳን ለ126ኛው የአድዋ ድል መታሰቢያ በዓል በሰላም አደረሳችሁ ።

አድዋ- የጥቁር ህዝቦች ድል
A GLORY OF AFRICA
1.8K viewsNatnael፲፪, 09:04
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-02-17 12:25:09
#እግዚአብሔርን_መጠበቅ!!

“እግዚአብሔር አንድ ነገር ለምነኸው ቶሎ ቢፈጽምልህ እምነትህን ያጠናክርልሃል፤ ካዘገየብህ ደግሞ ትዕግስትን እያስተማረህ ነው፤ ጭራሽ ከከለከለህ ግን አንተ የለመንከው ነገር ላንተ እንደማያስፈልግህ እርሱ ስለሚያውቅ ሌላ አዲስ ነገር እያዘጋጀልህ ነውና ጠብቀው።“
2.4K viewsNatnael፲፪, 09:25
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-02-13 10:24:39
#በትህትናም_መናገርን_ልመዱ...!

"ክርስትና ሰዎችን በተወሰኑ ሀሳቦች ማሳመን አይደለም። ይልቁንም ከክርስቶስ ፍቅርና ታላቅነት ይካፈሉ ዘንድ መጋበዝ ነው፡፡ ሰዎችን በጥዑም ንግግር ለመማረክ ብላችሁ ወጥመድ ውስጥ እንዳትወድቁ ጸልዩ፡፡ በትህትናም መናገርን ልመዱ! ሰዎችንም በራሱ በክርስቶስ መማረክ ይገባችኋል፡፡"

#ቅዱስ_አግናጥዮስ_ዘአንጾኪያ
2.2K viewsNatnael፲፪, 07:24
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-02-11 10:23:01
ተጠንቀቁ: ይህንን ጌም በፍፁም እንዳትጫወቱ ! በዚህ ሰሌዳ ተጫውተው የተረፉ ሁሉ የሞት የመጨረሻው ጨዋታ እያሉ ሲጠሩት ይደመጣሉ! ያልተፈታው የOUIJA BOARD ሚስጥር ሙሉ መረጃውን ከስር ባለው ሊንክ ገብታቹ ተመልከቱ






1.9K viewsNatnael፲፪, 07:23
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-02-06 08:29:59
#አታረጅም_ነገር_ግን_ዘወትር_ታበራለች!

ከቤተ ክርስቲያን የሚበልጥ ብርቱ (ጠንካራ) ምንም የለም። ይህችውም ከሰማይ ከፍ ያለች ከምድርም ይልቅ የሰፋች ናት። አታረጅም ነገር ግን ዘወትር ታበራለች።ቤተ ክርስቲያን በዘመናት ሁሉ ትሰፋለች። መታሰቢያዋም የሚጠፋ (የሚሞት) አይደለም። … ቤተ ክርስቲያን በስንቶች ውጊያ ተደርጎባት ነበር? አልተሸነፈችም እንጂ። የተዋጓት አላውያን፣ የጦር መሪዎች፣ ነገሥታቱስ ምን ያህል ናቸው? የተማሩና ኃይልን የተሞሉ ጎበዞች ሐዲሲቷን ቤተ ክርስቲያን በብዙ ጎዳናዎች ተዋግተዋት ነበር። ሊነቅሏት ግን አልቻሉም።

ነገር ግን እርሷን የተዋጉ ጥቂቶች ለዝምታና ቶሎም ለመረሳት ተላልፈው ተሰጥተዋል። የወጓት ቤተ ክርስቲያን ግን ከሰማይ በላይ ከፍ ከፍ ብላለች። ቤተ ክርስቲያንን ድል ከማድረግስ ፀሐይን ማጥፋት (ማጨለም) ይቀላል። ሰው ሆይ! ከቤተ ክርስቲያን የሚበልጥ ኃያል ምንም የለም። ከሰው ብትጣላ ወይ ታሸንፋለህ አልያም ትሸነፋለህ። ቤተ ክርቲያንን ግን ብትጣላ፣ ታሸነፍ ዘንድ የሚቻልህ አይደለም። እግዚአብሔር ከሁሉ ይልቅ ኃያል ነውና። እግዚአብሔር መስርቷታል፤ እንግዲህ ማን ሊነቀንቃት ይችላል?

#ቅዱስ_ዮሐንስ_አፈወርቅ!
2.1K viewsNatnael፲፪, 05:29
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-01-29 11:11:18
#አዳምና_ሔዋን_ዛሬ_ደስ_አላቸው!!

"ልጃቸው ተሰብስበው ወዳሉበት መጥታለችና አዳምና ሔዋን ዛሬ ደስ አላቸው። በዚህች ቀን ታላቁ ዳዊት በራሱ ላይ የተዋበ አክሊል የደፋችለትን ሴት ልጁን አይቶ ደስ አለው። በዚህች ቀን ነቢዩ ኢሳይያስ ትንቢት የተናገረላት ድንግል ወደ ሙታን ሥፍራ ልትጎበኘው መጥታለችና ደስ አለው። በዚህች ቀን ብርሃን ሲበራባቸው አይተዋልና ነቢያት ሁሉ ከመቃብራቸው ራሳቸውን ቀና አደረጉ። አርያም በጣፋጭ የመላእክት ዝማሬ ተሞላ፤ ምድር ደግሞ ኀዘንን በተሞሉ በሐዋርያት ለቅሶ ተሞላች፡፡ ሙታንም ሕያዋንም ትርጉሙን ሊገልጹት በማይችሉት የተለያየ ዜማ ሰውና መላእክት በዚያች ዕለት አብረው ጮኹ።"

#ቅዱስ_ያዕቆብ_ዘሥሩግ
2.0K viewsNatnael, 08:11
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-01-25 10:04:08
ያልተፈታው ጭንቅላት የሌላቸው ሰዎች ሸለቆ- በካናዳውያን ዘንድ እጅግ የሚፈራው ቦታ ( እውነተኛ ታሪክ ) የዚህን እውነተኛ ታሪክ የመረጃ ምንጭ ለምትፈልጉም primary source አስቀምጠናል ሙሉ መረጃውን ከስር ባለው ሊንክ ገብታቹ ተመልከቱ






2.0K viewsNatnael፲፪, 07:04
ክፈት / አስተያየት ይስጡ