የዒድ ውሎ - [በእውነተኛ ታሪክ ተመርኩዞ የተፃፈ] : (ᴛᴇᴀᴍ ʜᴜᴅᴀ) . የአመቱ ምርጥ ቀን ኢድ ለመንጋቱ ማስረጃ የሱብሒ አዛን ከአቅራቢያችን መስጂድ ተሰማ። አስማ ውድ ልጄንና ባለቤቴን ከቀሰቀስኩ በኋላ ወደመታጠቢያ ቤት ገባሁ። ተጣጥቤ ከሰገድኩ በኋላ የልጅነት ማስታወሻዬን ለአፍታ ስከፍት የያዘኝ ከሕፃንነቴ በአንዱ ያሳለፍኩት የአረፋ ውሎዬን የከተብኩበት ገፅ ነበር። * * አርብ 16/02/2005 ቤቱ ውስጥ በሚሰማው ጫጫታ ብቻ የኢድ ቀንን የሚለይ ሰው ካለ እኔ ነኝ። ኢድ ለኔ የአዘቦት ቀን ነው። ከተራው ቀን የሚለየው በብዛት ፎቶ በመነሳቴ ብቻ ነው። ካለንበት የወንዶች ክፍል በተቃራኒ ያለው የሴቶች ማደሪያ ክፍል ከወትሮው በተለየ ይናወጣል። > ሁሉም ያለ መሰማማት ይጮሀል። ኢድ እስክንሰግድ እንጂ ከዛ በኋላ ቀና አሳቢ መሳዮች ሲዘይሩን በተራቸው እነሱ ያውኩያ እኛ ተመልካች እንሆናለን። እዚህ ማሳደጊያ አራት ወንዶች ና ሰባት ሴቶች አለን። እናት ሐፍሳ የሁላችንንም መሻት ለመሙላት ትጥራለች። እጅ አጥሯት ስታዝን ሳይ ምነው ኢድ ባልኖረ እላለሁ። ልጆቿም ለመመፃደቅ ካልሆነ ዞር ብለው አያዩንም እንዲያም ሆኖ እናታችን ናት። የወንዶች መሔጃ ባስ ሲመጣ ከሴቶቻችን ጋ መለያየት ግድ ሆነ። እስከ መሐል ከተማ በባስ ሔደን ከዛ ተልቢያ እያልን በእግር ጉዞ ጀመርን። አትዋሽ አትበሉኝና ከኢድ ብቸኛው የሚስበኝ ቦታ ይሔ ነው። የሙት ልጅ ሳልባልና ከንፈር ሳይመጠጥልኝ ከሰው እኩል ተስተካክዬ አላሁ አክበር የምልበት። የኢድ ሰላትን ከሰገድን በኋላ ኹጥባ ለማድመጥ ዘግየት አልን። ዙሪያዬን ቃኘሁ እንደተለመደው ሁሉም ኹጥባውን ትቶ ወደቤቱ መሽቀዳደም ያዘ። ይለኛል ታላቅ ወንደሜ ሐሰን። የሚያርዱትም ባይኖር መሔዳቸው አልቀረ። ኹጥባውን አድምጠን ወደ ባሳችን ተመለስን። > ሲል የሁላችንም ታላቅ የሆነው ሐምዛ ነገረን። እናት ሐፍሳና ቤተሰቦቿ እስኪመጡ ቤት(ማሳደጊያው ውስጥ) ያዘጋጀነውን ዳቦ አቅርበን አፈጠርን። ግቢ ተንኳኳ። ቀኑን ሙሉ እንዴት አረፈዱ ስንል የጠበቅናቸው ዘያሪዎቻችን... ከፊት ያለው ሰልፊ ስቲኩን ይዞ ቀድሞ ገባ። ሌሎቹ ዳቦ ለስላሳና ሌሎች ነገሮችን ተሸክመዋል። ሴቶቹ በእናት ሐፍሳ በኩል ሲደረደሩ ወንዶቹ ያለችን አዳፋ ሶፋ ላይ ተደረደሩ። ከኛ ይልቅ እነሱ የተራቡ ይመስላሉ። ገና ከመግባታቸው ሱፍራ ዘርግተው ምግቡን በሰሐን ካቀራረቡ በኋላ መብላት ጀመሩ። የረሐብ ስካራቸው ሲበርድ ካመጡት ለስላሳ ያስቀሩትን በአይኔ ቃኘሁ። ሶስት ያልተከፈተ ና አንድ የተጀመረ ጠርሙስ። ግቢውን ከፍቼ ወጣሁ። በሩ ላይ የመመገቢያ አዳራሽ ይል እንደሁ ብዬ። የለም! የእናት ሐፍሳ ማሳደጊያ እንደሆነ የሚገልፀው ወረቀት ከዝናብ ብዛት በስብሶ ቀለሙን ለቋል። ሌላ የለም! ተመልሼ ስገባ በር ላይ ሐምዛን አገኘሁት። አይኑን እያየሁ ጠየቅኩት። የሴቶቹ ሳቅ ሙሉ ግቢውን እያወከ ስለነበር ወደአንድ ጥግ ጎተት አድርጎኝ እንዲህ አለኝ እጄን ይዞኝ ወደ ቤት ገባን። ስንገባ ግን ጭራሽ ቪዲዮ ላይ ናቸው፣ የስልኩ ፍላሽ (መብራት) አህላም ላይ እየበራ ስለነበር እንባዋ ይፈሳል። የsolar አለርጂኳ እንደተነሳ ስለገባኝ እንደምንም እያራመድኳት ወደ መኝታ ክፍል ገባሁ። የዛሬ አመት በር ላይ ተጥላ ካገኘኋት ጀምሮ እየተባባሰ የመጣ የአይን ሕመም አለባት። በጠብታ እያስታገስን ነው እስካሁን ያቆየነው። እንቅልፍ ሸለብ ሲያደርጋት ወደ ሳሎን ተመልሼ መጣሁ። ሊወጡ አካባቢ ነው መሰለኝ፣ የመጨረሻ ፎቶ ብለው ደረደሩንና አበሩብን። የባለካሜራውን እጅ ነክሼ ተመልሳችሁ አትምጡ ማለትን ወደድኩ። ተንኮሌ የገባው ሐሰን በአይኑ ጎሸም ባያረገኝ ኖሮ...! እናት ሐፍሳ ልቧ ቀና ነው። እስከበር ድረስ የምስጋና ናዳ እያወረደች ከሸኘቻቸው በኋላ የበሉበትን የሰሐን ክምር ከሴቶቹ ጋር ለማጠብ ወደጓሮ ሔደች። ወንዶቹ ደሞ እንደ ፈረቃችን ቤቱን ስንጠርግ መግሪብ ደረሰ። ከሐሰን ጋ ወደ መስጂድ ወጥተን ስንመለስ እንዲህ አለኝ፦ ከልቤ ደስ እያለኝ ነበር ያልኩት። ሊመፃደቁ እጃቸውን ሲዘረጉላቸው ላዘኑት መፅናኛ ሆናለሁ። * * * ከማለቴ ባለቤቴ ወዳለሁበት ተጠግታ ስትል ግንባሬን ሳመችኝ። ኢድ ሙባረክ በድጋሚ @Re_ya_zan 198 views11:25