....መናፈቅ (ሚካኤል.አ) በማደግ ተራቀቅን... ልባችን ተዋጠ በፍራንካ ተመን ማወቅ ክፉ ሆኖ ለሀሳብ ሞሸረን ይኸው ባክነን ቀረን ! ግብ ግብ ከህይወት ዘወትር ሩጫ... በዚህ መሀል ሳትን የትናንቱን ብልጫ። ጎዳናው ተሞልቷል በወጣት ባዛውንት እድሜ ባደረሰው ... ከልቡ የሚስቅ ብቻ ነው ማላየው ! ፈገግታው የውሸት ከአፍ የሚቀዳ ሀዘኑ የእውነት ነፍስን የሚጎዳ። ይሄ ነው የሞላው በዚህ እድሜ ዘመን ታድያ ትናንትና እንደምን ይተመን? ያ ሳቅ በመጣልኝ የክረምቱ ሞገስ ደጄ በዋለልኝ.. . ወጥቼ ባቦካሁ የመንደሬን ጭቃ ፍሬ በደረደርኩ ለአዝናኝ እቃቃ ዘልዬ ደስ ባለኝ በገመድ ቡረቃ። ያ ሳቅ በመጣልኝ.. . በውድ አልባሳቶች በሚያምር ቁመና በሀብትና ዝና... መሀል ተጋርጄ ካልደላኝ መኖሬ ምናለ ልጅ በሆንኩ ከትናንት በርሬ አልጣመኝም ዛሬ ! ።።።።።።።።።። ንባብ ፡ ፀባዖት ሶልአኪያ 67 views🅢🅞🅛 🅺🅸 Tsebaot, edited 16:00